Amhara Media Network

Amhara Media Network ብሄርን በብሄር ላይ ማነሳሳት የግጭት መልክት ክልክል ነዉ ህዝበ ኢትዮጵያ ዘላለም አብሮዎ ኑአሪ ነዉ!!

ታጋይ ማርሸት ለመንግሥት ሃይሎች እጅ ሰጡ!!ማርሸት እጂ መስጠት ጋር በተያያዘ ብዙዎች አጀንዳ አድርገውታል ።
30/08/2026

ታጋይ ማርሸት ለመንግሥት ሃይሎች እጅ ሰጡ!!
ማርሸት እጂ መስጠት ጋር በተያያዘ ብዙዎች አጀንዳ አድርገውታል ።

ሰበር ዜና!በአማራ ክልል ዋና ከተማ በባህር ዳር ከተማ፣ በዘመነ ካሴ የሚመራው ኃይል (አፋብን)በቁጥጥሩ ስር አውሏል። ኃይሉ በአሁኑ ሰዓት የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን መገናኛ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙ...
20/07/2026

ሰበር ዜና!
በአማራ ክልል ዋና ከተማ በባህር ዳር ከተማ፣ በዘመነ ካሴ የሚመራው ኃይል (አፋብን)በቁጥጥሩ ስር አውሏል። ኃይሉ በአሁኑ ሰዓት የሬዲዮ እና የቴሌቪዥን መገናኛ ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር የከተማዋን ሰላም ለመመለስ እየሰራ መሆኑ ተረጋግጧል። ይህ ክስተት ዛሬ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ መፈጸሙ ታውቋል።

አክቲቪስት ሰለሞን ቦጋለ  የግድያ ሙከራ ተደረገበት ዝርዝር መረጃውን ከሰዓታት በሗላ ይጠብቁን።
11/07/2026

አክቲቪስት ሰለሞን ቦጋለ የግድያ ሙከራ ተደረገበት ዝርዝር መረጃውን ከሰዓታት በሗላ ይጠብቁን።

 #ችሎትየበረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲታይ ተወሰነ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረ...
25/06/2026

#ችሎት

የበረከት ወርቁ (በረከት ገበሬዋ) የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲታይ ተወሰነ።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት "በገበያ ላይ የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት አድርገዋል" የተባሉ የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር(ዲባራ ፉፋ) እና የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር (አቶ ሹምአለም ብርሃኔ) ጨምሮ የከባድ ሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ግለሰቦች ጉዳይ እየተመለከተ መሆኑ ይታወቃል።

ተጠርጣሪዎቹ ከመመሪያ ውጪ የነዳጅ ግዥና አከፋፋይነት ፈቃድ በመስጠት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ሊትር ናፍጣ በኮንትሮባንድ እንዲሸጥ በማመቻቸት እና ከጅቡቲ የሚመጣ ድጎማ የተደረገበትን ነዳጅ ከቁጥጥር ውጪ በማድረግ ወንጀል የተከሰሱ 13 ተከሳሾች ውስጥ የ 4 ተከሳሾች እና የአንድ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ክስ እንዲቋረጥ በመደረጉ ክሳቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተከሳሾች ቁጥር 9 ሆኗል።

ከእዚህ ቀደም በነበረው የችሎት ውሎ ከ1ኛ እስከ 10 ኛ ተከሳሾቹ የተከሰሱበት የክስ መዝገበ ከ 10 ኛ እስከ 13ኛ ተከሳሾች ከተከሰሱበት ክስ ተሻሽሎና ተለይቶ እንዲቀርብ እና ለበረከት ወርቁ(በረከት ገበሬዋ) የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግ ችሎቱ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር።

በረከት ወርቁ ሰኔ 8/2018 በታተመው የአዲስ ዘመን እና Jun 18/2026 በታተመው Ethiopian Herald ጋዜጣ ጥሪ ቢደረግላትም በችሎቱ አልተገኘችም።

በመሆኑም ከእዚህ ቀደም በነበረው የክስ መዝገብ በሰባተኛ ተከሳሽነት በተሻሻለው የክስ መዝገብ ደግሞ በ 5 ኛ ተከሳሽነት የተቀመጠችው በረከት ወርቁ የክስ ሂደት በሌለችበት እንዲካሄድ ተወስኗል።

አቃቢ ህግ ክሱን ለይቶ እና አሻሽሎ በሁለት መዝገብ ያደራጀው ሲሆን በተሻሻለው ክስ መሰረት በመጀመሪያው የክስ መዝገብ እነ ዲባራ ፉፋን ጨምሮ 6 ተከሳሾች በሁለተኛው የክስ መዝገብ እስምአለም ምህረቱን ጨምሮ ሦስት ተከሳሾች ይገኛሉ።

በገበያ ላይ ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት በማድረግና ሥልጣንን ያለአግባብ በመገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል በድምሩ ከ 30 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት በመንግስት ላይ በማድረስ በሚል ክስ ጉዳያቸውን እየተከታተሉ የሚገኙት ተከሳሾች የክስ ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተወስኗል።

መዝገቡ በሌላ ችሎት እንዲታይ ተመርቶ የነበረ ቢሆንም ሳይታይ በመቅረቱ ተለዋጭ ቀጠሮው ቀን በዛሬው የችሎት ውሎ ሳይወሰን ቀርቷል።

መንግሥት ድጎማ ያደረገበትን ነዳጅ ከጅቡቲ በመጫን 17.8 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ጉዳት በማድረስና በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማይመች አኳኋን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ከ 11 እስከ 13 ኛ ያሉ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ ምስክሮችን የመስማት ሂደት በቀጠሮው መሰረት የሚቀጥል ይሆናል።

ፌዴራል ፖሊስ ይፈለጋሉ ካወጣባቸው እና እስካሁን በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን ተከሳሾች ጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለን በሚመለከት ፖሊስ በአድራሻቸው ፈልጎ እንዳላገኛቸው ለችሎቱ የተገለጸ ሲሆን የጋዜጣ ጥሪ እንዲደረግላቸው ታዟል።

የጌታቸው አሞኘ እና አቡሽ አየለ የጋዜጣ ጥሪ ለመጠባበቅ እና አቃቢ ህግ የሚያቀርባቸውን 24 ምስክሮችን የመስማት ሂደት ለማከናወን ከሐምሌ 21 እስከ 23/2018 ዓም ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ/ም

የቀጠናው ስጋት በኢትዮጵያ
24/06/2026

የቀጠናው ስጋት በኢትዮጵያ

''መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ውጊያ ሙሉ አቅሙን አልተጠቀመም'' ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬ''''የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል እያደረገ ባለው ውጊያ ላይ ሙሉ ወታደራዊ አቅሙንና ከባድ...
18/06/2026

''መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ውጊያ ሙሉ አቅሙን አልተጠቀመም'' ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬ''

''የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል እያደረገ ባለው ውጊያ ላይ ሙሉ ወታደራዊ አቅሙንና ከባድ የጦር መሳሪያዎቹን በሙሉ አቅም ጥቅም ላይ አላዋለም ብሏል።

ይህንንም ያደረገው ደግሞ የአማራ ክልል ወጣቶች ነገ ሀገራቸውን መጥቀም ይችላሉ፣ በሰላም እጅ ሰተው እንድገቡ ስለሚፈል ፣ መሞትና መገዳደል የለብንም ብሎ ስለሚምብ ነው ሲል ''እጅ የሰጠው ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬ ተሰምቷል።''

አክሎም መከላከያ ሙሉ አቅሙን ቢጠቀም እና ቢዋጋ ምን ያክል የአማራን ወጣት ህይወት ማጥፋት እና መማረክ ይችል ነበር ሲል ኮማንዶ ፍቅሩ ሙልዬ ተናግሯል።

ሰላም ለኢትዮጲያ
ሰላም ለህዝባችን
ወሎ አዲስ የህዝብ አድማስ

በኮማንዶ ፍቅሩ ንግግር ምን ትላላችሁ?
ሐሳባችሁን አካፍሉን?

ይመርመር ይጣራልን !!! ባለፉት ጥቂት ወራት Glow Ethio-Turkiye ወደሚባል  ድርጅት ሄጄ የክብደት መቀነስ ህክምና በመከታተል ላይ ነኝ  ብሎን በየጊዜው ያስመዘገበውን የክብደት ለው...
15/06/2026

ይመርመር ይጣራልን !!!

ባለፉት ጥቂት ወራት Glow Ethio-Turkiye ወደሚባል ድርጅት ሄጄ የክብደት መቀነስ ህክምና በመከታተል ላይ ነኝ ብሎን በየጊዜው ያስመዘገበውን የክብደት ለውጥ(weight loss progress) እያሳየን በርታ በሉኝ እያለ ድርጅቱንም በ Social Media ላይ promote ሲያደርግ ሲያስተዋውቅ የምናውቀው ሰውዬ ከእለታት በአንዱ ጠዋት ከመኝንታ ስንነሳ ህልፈተ ህይወቱን ሰማን።

እንዴት ሊሆን ይችላል?

ለክብደት መቀነስ የተጠቀመው መድሃኒት ሳይረዳው ቀርቶ ነው ወይንስ መድሃኒቱ ራሱ ጎድቶት ነው?

ነው ወይንስ በህመም ምክንያት እየተከሰተ የነበረውን የክብደት መቀነስ ነው ልክ በህክምና ክትትል የተገኘ achievement አስመስለው መስታወቂያ ሲሰሩበት ሌሎችንም ሊያጠምዱበት ሲሯሯጡ የከረሙት ?

ይህንን ነገር በቸልታ የምናየው አይሆንም።

ለሞት ያበቃው የጤና ችግር ይብራራልን!!

ዝም ብሎ በደፈናው ብቻ "ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ" የምትለው Generic ዜና ዕረፍት sense አትሰጥም።

ማብራሪያ እንጠብቃለን።
Amhara Media Network

ፍቅሩ ሙልዬ የሰላም አማራጭን ተቀበለ። ወሎ ዞን ላሊበላ እና አካባቢው በትጥቅ ትግል ሲንቀሳስ የነበረው  ፍቅሩ ሙልዬ የሰላም አማራጭን ተቀብሏል። ላለፉት ዓመታት በሰሜን ወሎ በላሊበላ እና ...
30/03/2026

ፍቅሩ ሙልዬ የሰላም አማራጭን ተቀበለ።

ወሎ ዞን ላሊበላ እና አካባቢው በትጥቅ ትግል ሲንቀሳስ የነበረው ፍቅሩ ሙልዬ የሰላም አማራጭን ተቀብሏል።

ላለፉት ዓመታት በሰሜን ወሎ በላሊበላ እና በአካባቢው በጫካ ሲንቀሳቀስ የነበረው ፍቅሩ ሙሉዬ የሰላም አማራጭን ተቀብሎ ለሰላም ገብቷል። ፍቅሩ ሙልዬ በታጣቂዎች አደረጃጀት እስከ ኮር አዛዥ የደረሰ ኀላፊነት ነበረው።

በአማራ ክልል ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ በመንግሥት እና በታጣቂ ኃይሎች መካከል ተደጋጋሚ ውይይቶች ሲደረጉ ቆይተዋል።

በተደረጉ ተከታታይ ውይይቶች በርካታ ታጣቂዎች የሰላም አማራጭን ተቀብለዋል። አሁንም በየአካባቢው የሰላም አማራጭን እየተቀበሉ የሚገቡት ታጣቂዎች በርካታ ናቸው።

ታጋይ ፍቅሩ ለመንግሥት ሃይሎች እስከ አባሎቹ እጂ መስጠቱ ይፋ መሆኑን መረጃዎች አመለከቱ ።
30/03/2026

ታጋይ ፍቅሩ ለመንግሥት ሃይሎች እስከ አባሎቹ እጂ መስጠቱ ይፋ መሆኑን መረጃዎች አመለከቱ ።

Adres

Uk
Lendelede

Website

Meldingen

Wees de eerste die het weet en laat ons u een e-mail sturen wanneer Amhara Media Network nieuws en promoties plaatst. Uw e-mailadres wordt niet voor andere doeleinden gebruikt en u kunt zich op elk gewenst moment afmelden.

Snelkoppelingen

Delen