30/05/2026
በአብርሆት ቤተመጻሕፍት የደም ልገሳ ፕሮግራም :-
አብርሆት ቤተመጻሕፍት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሃግብር ዛሬ በቤተመጻሕፍቱ አካሂዷል። በዚሁ ዝግጅት ላይ የቤተመጻሕፍቱ ተጠቃሚዎች በመሳተፍ ደም የለገሱ ሲሆን፣ የተሰበሰበው ደም አስቸኳይ የሕክምና ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖቻችን ሕይወት መታደጊያ የሚውል ይሆናል።
አብርሆት ቤተመጻሕፍት የንባብና የጥናት ማዕከል ከመሆኑ ባለፈ፣ ለማኅበራዊ አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚሰጥ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል።