Abrehot Library

Abrehot Library Abrehot library is a public library. It is located in Arat Kilo, Addis Ababa, Ethiopia.
(1)

በአብርሆት ቤተመጻሕፍት የደም ልገሳ ፕሮግራም :- አብርሆት ቤተመጻሕፍት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሃግብር  ዛሬ በቤተመጻሕፍቱ  አካሂዷል። በዚሁ ዝግጅት ...
30/05/2026

በአብርሆት ቤተመጻሕፍት የደም ልገሳ ፕሮግራም :-

አብርሆት ቤተመጻሕፍት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሃግብር ዛሬ በቤተመጻሕፍቱ አካሂዷል። በዚሁ ዝግጅት ላይ የቤተመጻሕፍቱ ተጠቃሚዎች በመሳተፍ ደም የለገሱ ሲሆን፣ የተሰበሰበው ደም አስቸኳይ የሕክምና ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖቻችን ሕይወት መታደጊያ የሚውል ይሆናል።
አብርሆት ቤተመጻሕፍት የንባብና የጥናት ማዕከል ከመሆኑ ባለፈ፣ ለማኅበራዊ አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚሰጥ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል።

የአብርሆት ቤተመጻሕፍት የዘወትር ቅዳሜ የልጆች ክፍል ፕሮግራም በምስል! 👆👇ዛሬ ቅዳሜ በቤተመጻሕፍታችን በልጆች ክፍል ደስ የሚልና ፍሬያማ ጊዜ አሳልፈናል። በዕለቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ዝግጅ...
30/05/2026

የአብርሆት ቤተመጻሕፍት የዘወትር ቅዳሜ የልጆች ክፍል ፕሮግራም በምስል!
👆👇

ዛሬ ቅዳሜ በቤተመጻሕፍታችን በልጆች ክፍል ደስ የሚልና ፍሬያማ ጊዜ አሳልፈናል። በዕለቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ዝግጅቶች፡-

ለልጆች ግንዛቤ፦ ልጆች ጊዜን በአግባቡ እንዲጠቀሙ የሚያደርግ ትምህርት ተሰጥቷል።

አዝናኝ የስፖርት እንቅስቃሴ፦ ልጆችን ንቁ የሚያደርጉ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተካሂደዋል።

የቀለም ቅብ (Painting)፦ ልጆች የፈጠራ ችሎታቸውን ያሳዩበትና የተዝናኑበት የቀለም ቅብ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

ልጅዎን ሁልጊዜ ቅዳሜ ወደ አብርሆት ይዘው ይምጡ!

በአብረሆት ቤተ መጻሕፍት ለሠራተኞች የተሰጠ የካይዘን (Kaizen) ሥልጠና በምስልና ገለፃ 🚀ካይዘን (ዘላቂነት ያለው መሻሻል) ከጃፓን የመነጨ ጠንካራ የሥራ እና የሕይወት ፍልስፍና ሲሆን፣ ...
29/05/2026

በአብረሆት ቤተ መጻሕፍት ለሠራተኞች የተሰጠ የካይዘን (Kaizen) ሥልጠና በምስልና ገለፃ 🚀

ካይዘን (ዘላቂነት ያለው መሻሻል) ከጃፓን የመነጨ ጠንካራ የሥራ እና የሕይወት ፍልስፍና ሲሆን፣ በአብረሆት ቤተ መጻሕፍት ውስጥ ይህንኑ መልካም ተጽዕኖ ለማምጣት ስልጠናው በተለያየ ዘርፍ ላይ ለሚገኙ ሠራተኞች በመሰጠት ላይ ይገኛል። ስልጠናው በካይዘን ፍልስፍና ውስጥ ያሉ የተለያዩ ሀሳቦች ይዳስሳል ከነሱም :-

🧩 አራቱ የለውጥ ምሰሶዎች
የሁልቀን (Every Day)፦ ማሻሻል የዕለት ተዕለት ተግባር ነው።
የሁሉም ሰው (Everyone)፦ እያንዳንዱ ሠራተኛ ይሳተፋል።
የሁሉም ቦታ (Everywhere)፦ በሁሉም የቤተ መጻሕፍቱ ክፍሎች ይተገበራል።
የሁሉም ነገር (Everything)፦ እያንዳንዱ የሥራ ሂደት እና አገልግሎት ይሻሻላል።

⚙️ 5ቱ መሠረታዊ ባህሪያት
ተሳትፎአዊ፦ ሁሉንም ሠራተኛ ያሳትፋል።
ዘላቂነት ያለው፦ የማይቋረጥ አዎንታዊ ለውጥ ነው።
የጥቂት በጥቂት ድምር፦ በጥቃቅን እርምጃዎች ትልቅ ስኬት ያመጣል።
ያለ ከፍተኛ ወጪ፦ ከፍተኛ የገንዘብ ኢንቨስትመንት አይጠይቅም።
ተለዋዋጭ፦ በማንኛውም የሥራ ሁኔታ ውስጥ የሚተገበር ነው።

በአጠቃላይ የአመራር እና የሠራተኛ ትኩረት ምን መሆን እንዳለበት ማለትም ነባራዊ ሁኔታን መረዳት ፣ የሥራ አካባቢን ማሻሻል(ምቹ እና ቀልጣፋ የሥራ ቦታ መፍጠር) ፣ የሰውን ኃይል በአግባብ የሥራ ቦታ ማዋል ፣ ሠራተኛውን የለውጥ ዋና አንቀሳቃሽ ማድረግ ተጠቃሽ ናቸው ።

ሳምንታዊ ጥያቄ አብርሆት ቤተ-መጻሕፍትን በምን ያህል ጊዜ ልዩነት ይጠቀማሉ?🤔 መልሳችሁን በኮመንት ላይ አስቀምጡ 💫1. በየቀኑ! 📖2. በየሳምንቱ! 🎒 3. በየወሩ! 📚
29/05/2026

ሳምንታዊ ጥያቄ

አብርሆት ቤተ-መጻሕፍትን በምን ያህል ጊዜ ልዩነት ይጠቀማሉ?🤔 መልሳችሁን በኮመንት ላይ አስቀምጡ 💫

1. በየቀኑ! 📖
2. በየሳምንቱ! 🎒
3. በየወሩ! 📚

ርዕስ፦ ምንትዋብ  ደራሲ፦ ህይወት ተፈራየገጽ ብዛት፦ 270የኅትመት ዘመን፦ 2012 ዓ.ም.አድራሻ (ለአንባቢያን)፦ በአብርሆት ቤተ መጽሐፍት፣ 4ኛ ፎቅ፣ የልቦለድ ክፍል ይገኛልአጭር ገለፃ በ...
28/05/2026

ርዕስ፦ ምንትዋብ
ደራሲ፦ ህይወት ተፈራ
የገጽ ብዛት፦ 270
የኅትመት ዘመን፦ 2012 ዓ.ም.
አድራሻ (ለአንባቢያን)፦ በአብርሆት ቤተ መጽሐፍት፣ 4ኛ ፎቅ፣ የልቦለድ ክፍል ይገኛል

አጭር ገለፃ

በደራሲ ሕይወት ተፈራ የተዘጋጀው "ምንትዋብ" የተሰኘው ታሪካዊ ልብወለድ መጽሐፍ፣ በ18ኛው ክፍለ ዘመን የነበሩትን ጠንካራዋን መሪ እቴጌ ምንትዋብን ታሪክ መሠረት ያደረገ ነው። እቴጌ ምንትዋብ የአፄ በካፋ ባለቤት ሲሆኑ፣ ከባላቸው ሞት በኋላ የልጃቸውንና የልጅ ልጃቸውን አልጋ ወራሾች በሞግዚትነት በመምራት ለ40 ዓመታት አገሪቱን አስተዳድረዋል። በዘመናቸው በጎንደርና በጣና ሐይቅ ላይ የገነቧቸውና ያደሷቸው አብያተ ክርስቲያናት፣ የነበራቸውን የዲፕሎማሲ ችሎታ፣ እንዲሁም ለኪነ-ሕንጻና ለሥነ-ሥዕል የነበራቸውን ከፍተኛ ፍቅር መጽሐፉ ያሳያል። መጽሐፉ እውነተኛ ታሪካዊ ሰዎችን (እንደ እቴጌ ምንትዋብ) ‘ጥላዬ’ ከተባሉ በፈጠራ ከተጨመሩ ምናባዊ ገጸ-ባህሪያት ጋር በማስተሳሰር ፣ የእቴጌይቱን ሰውኛ ማንነትና የወቅቱን የሥነ-ሥዕል ትምህርትና ሥርዓት አጉልቶ ያሳያል።

በአጠቃላይ መጽሐፉ በስፋት ያልተወሳላቸውን የእቴጌ ምንትዋብን ታሪክ የሚተርክ ነው ይህም ለተቋማት ግንባታ፣ ለሥነ-ጥበብ ዕድገት፣ ለባለቅኔዎችና ለሰዓሊዎች "ክብር" በመስጠት ሥራዎቻቸው በተቋማዊ መልኩ እንዲቀርቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን።

Quiet minds, big ideas. ✨ Drop a 3-word review of your current read below!ረጋ ያለ አእምሮ ፣ ታላላቅ ሃሳቦች።  ✨ አሁን የሚያነቡትን መጽሐፍ በ3...
26/05/2026

Quiet minds, big ideas. ✨ Drop a 3-word review of your current read below!

ረጋ ያለ አእምሮ ፣ ታላላቅ ሃሳቦች። ✨ አሁን የሚያነቡትን መጽሐፍ በ3- ቃላት ብቻ ከታች በኮሜንት ይግለጽልን

📚 የአብርሆት ቤተመጻሕፍት የመጻሕፍት ስጦታ ለዳሪያን ማህበረሰብ!የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በቦታው ድረስ በመሄድ ለዳሪያን ማህበረሰብ ቤተመጻሕፍት (Communit...
26/05/2026

📚 የአብርሆት ቤተመጻሕፍት የመጻሕፍት ስጦታ ለዳሪያን ማህበረሰብ!

የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በቦታው ድረስ በመሄድ ለዳሪያን ማህበረሰብ ቤተመጻሕፍት (Community Library) 2,000 መጻሕፍትን አስረክቧል።
በእለቱም የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የቤተመጻሕፍት ኮሚቴ፣ የከተማው ከንቲባ እና የትምህርት ቢሮ አመራሮች በጋራ በመሆን ደማቅ የንባብ ቀን ፕሮግራም አክብረዋል። ማራኪ የሆኑ ግጥሞችና መነባንቦች ለታዳሚው ቀርበዋል። በ1ኛ እና 4ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል የንባብ ውድድር ተካሂዶ፣ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለወጡት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል። በመጨረሻም የዳሪያን ማህበረሰብ በአጠቃላይ የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ለትውልድ ግንባታ ላበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ ምስጋናቸውን በስጦታ አቅርበዋል።

📖 "ንባብ ለትውልድ ግንባታ!"

የልምድ ልውውጥ እና ስልጠና በአብርሆት! ✨📚የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ከ«ነገ ሌላ ቀን ነው» ተቋም ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የልምድ ልውውጥ እና የስልጠና መርሃ-ግብር በአብርሆት ቤተመጻሕፍት...
25/05/2026

የልምድ ልውውጥ እና ስልጠና በአብርሆት! ✨📚

የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ከ«ነገ ሌላ ቀን ነው» ተቋም ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የልምድ ልውውጥ እና የስልጠና መርሃ-ግብር በአብርሆት ቤተመጻሕፍት አከናውኗል። በዕለቱ የአብርሆት ቤተመጻሕፍት ባለሙያዎች ለ«ነገ ሌላ ቀን ነው» ተቋም አባላት ሰፊና ጠቃሚ ስልጠና ሰጥተዋል። በስልጠናውም፦
የቤተመጻሕፍት ዓይነቶች፦ የትምህርት ቤት፣ የኮሌጅ እና የዩኒቨርሲቲ ቤተመጻሕፍት አደረጃጀት ሥርዓት፣ ልዩ ልዩ የቤተመጻሕፍት ዘርፎች፦ በአንድ የትምህርት ሙያ ላይ ብቻ የሚያተኩሩ ልዩ ቤተመጻሕፍት (Special Libraries)፣ አገር አቀፍ ቤተመጻሕፍት፣ የሕዝብ (Public) እና የኮሚኒቲ ቤተመጻሕፍት ምንነትና አሠራር በዝርዝር ተዳስሰዋል። በመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ የ«ነገ ሌላ ቀን ነው» ተቋም አባላት የአብርሆት ቤተመጻሕፍትን አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በአካል በመዘዋወር ጎብኝተዋል።

ከሰዎች ጋር የመኖር ጥበብ እና ከሰው መጠበቅበአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዐት መግቢያ በፊት በሚዘጋጀው ወርቃማው ሰኞ የሰራተኞች መርሀ ግብር ላይ ``ከሰዎች ጋር የመኖር ጥበብ...
25/05/2026

ከሰዎች ጋር የመኖር ጥበብ እና ከሰው መጠበቅ

በአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዐት መግቢያ በፊት በሚዘጋጀው ወርቃማው ሰኞ የሰራተኞች መርሀ ግብር ላይ ``ከሰዎች ጋር የመኖር ጥበብ እና ከሰው መጠበቅ’’ በሚል ርዕስ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ሰራተኛ የሆኑት ወ/ሪት ቅድስት አራጋው ለሰራተኛው ግንቦት 17/2018 ቀን ማብራሪያ አድርገዋል፡፡ በገለጻቸውም ከሰው ጋር የመኖር ጥበብ ማለት ዕውቀትን፣ የስሜት ብልህነትን (EQ) እና ማኅበራዊ ግንኙነትን (SQ) በትክክል በመጠቀም ከሰዎች ጋር ሰላማዊ ሕይወት የመኖር ሥርዓት እንደሆነ አስረድተዋል። ይህ ጥበብ ሰራተኞች ግጭቶችን በሰላም እንዲፈቱ እና ሕይወትን በሚዛናዊነት እንዲመሩ ያደርጋል።
በተጨማሪም ከሰዎች ከመጠን በላይ መጠበቅ (Expectation) ማለት «ያልተነገረ ስምምነት» መሆኑን ገልጸው፣ ይህም ልማድ ለሥር ብስጭት፣ ጭንቀትና ለራስ ዋጋ መቀነስ እንደሚዳርግ አብራርተዋል። በመሆኑም በመጠበቅ የሚመጣን መጎዳት ለመቀነስ መፍትሄው የራስን ዋጋ መረዳት፣ የሰዎችን ውስንነት መቀበል እና «ከሰዎች ምን አገኛለሁ?» ከሚል ይልቅ «እኔ ለራሴ ምን እሰጣለሁ?» በሚለው መርህ ላይ ማተኮር እንደሆነ በማጠቃለያው አስገንዝበዋል። በጥበብና ከሰው ባለመጠበቅ ለሰው መልካም በማሰብ ደስተኛ የሥራና የኑሮ ግንኙነት እንዲኖረን እንደሚያደርግ በመግለፅ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

መልካም የስራ ሳምንት!

በአብርሆት ቤተመጻሕፍት የደም ልገሳ ፕሮግራም ተካሄደ :- አብርሆት ቤተመጻሕፍት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሃግብር  ዛሬ በቤተመጻሕፍቱ  አካሂዷል። በዚሁ ...
23/05/2026

በአብርሆት ቤተመጻሕፍት የደም ልገሳ ፕሮግራም ተካሄደ :-

አብርሆት ቤተመጻሕፍት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ደም ባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ መርሃግብር ዛሬ በቤተመጻሕፍቱ አካሂዷል። በዚሁ ዝግጅት ላይ የቤተመጻሕፍቱ ተጠቃሚዎች በመሳተፍ ደም የለገሱ ሲሆን፣ የተሰበሰበው ደም አስቸኳይ የሕክምና ዕርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖቻችን ሕይወት መታደጊያ የሚውል ይሆናል።
አብርሆት ቤተመጻሕፍት የንባብና የጥናት ማዕከል ከመሆኑ ባለፈ፣ ለማኅበራዊ አገልግሎቶች ቅድሚያ የሚሰጥ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል።

Address

Addis Ababa
Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 00:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Abrehot Library posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Abrehot Library:

Share

Category