Lafto woreda 05 Communication

Lafto woreda 05 Communication peace for Ethiopia

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነገ ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አስፈላጊው ዝግጅት ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነገ ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አስፈላጊው ...
31/05/2026

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነገ ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አስፈላጊው ዝግጅት ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነገ ለሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አስፈላጊው ዝግጅት ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።

በክፍለ ከተማው ስር በሚገኙ የተለያዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ለምርጫው ሂደት ስኬታማነት የሚያስፈልጉ የቁሳቁስና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶች ተጠናቀው ዝግጁ ሆነዋል።

ድምፅ መስጫ ጣቢያዎችን ምቹ የማድረግ፣ የድንኳን፣ የወንበር እንዲሁም አጠቃላይ ለምርጫው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን የማሟላት ስራ በተሟላ ሁኔታ ተከናውኗል።

በአዲስ አበባ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደራሽ በማድረግ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋልበአዲስ አበባ የሚገኙ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደ...
31/05/2026

በአዲስ አበባ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደራሽ በማድረግ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል

በአዲስ አበባ የሚገኙ የምርጫ ክልሎች የምርጫ የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ሥርጭት ተደራሽ በማድረግ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀዋል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነገ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መራጮች ድምፅ ይሰጣሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት 54 ሚሊየን 57 ሺህ 861 መራጮች መመዝገባቸውን አስታውቋል።

ነገ በሚካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ማስፈጸሚያ ቁሳቁሶች በየምርጫ ጣቢያዎች በመሰራጨት ዝግጁ እየሆኑ ይገኛሉ።

በዚህም የኢዜአ ሪፖርተር በመዲናዋ በምርጫ ክልል 2 እና 14 በአካል ተዘዋውሮ እንደተመለከተው፣ በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች የማስፈጸሚያ ቁሳቁስ ስርጭት ተጠናቋል።

በምርጫ ክልል 2 እና 14 ስር 14 የምርጫ ጣቢያዎች ያሉ ሲሆን የምርጫ ቁሳቁሶቹ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ተደራሽ በማድረግ ለምርጫው ሙሉ ዝግጅት መደረጉን መታዘብ ችሏል።
AMN

በምርጫ ብቻ!
31/05/2026

በምርጫ ብቻ!

ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ? 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል።በነገው ዕለት የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ጨምሮ የ...
31/05/2026

ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል።

በነገው ዕለት የሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ጨምሮ የጸጥታ ተቋማትና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገዋል፡፡

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ምርጫው በስኬት እንዲከናወን ያደረገው ዝግጅት እጅግ ጠንካራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫው የሚያስፈልገውን የምርጫ ቁሳቁስ በሁሉም አካባቢዎች በፍጥነት ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ለመሆኑ ከምርጫ ጋር ተያይዞ ችግሮች ሲፈጠሩ ዜጎች ማከናወን ያለባቸው ተግባራት የትኞቹ ናቸው ?

ምርጫ ቦርድ ዜጎች ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር የተያያዙ ችግሮችንና ክስተቶችን ደኅንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መንገድ ጥቆማ የሚያደርጉበትን ከምርጫ ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩ ችግሮች ሪፖርት ማድረጊያና ምላሽ መስጫ ሥርዓት ዘርግቷል።

በዚህም መሰረት ዜጎች ምን ምን ዓይነት ችግሮችን ጥቆማ ማድረግ ይችላሉ?

👉በምርጫ ሒደቶች ላይ የሚፈጠሩ መስተጓጎሎች፣

👉በድምፅ አሰጣጥ ወይም በቆጠራ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮች፣

👉በምርጫ ጣቢያዎች አቅራቢያ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮች፣

👉በመራጮች ላይ የሚደርስ ማስፈራራት ወይም ትንኮሳ፣

👉በምርጫ ቁሳቁስ ላይ የሚደርስ ጉዳት፣

👉ዐመፅ ወይም ዛቻዎች፣

👉ውጥረት የሚፈጥሩ የሐሰት መረጃዎች፣

👉እንዲሁም ምርጫውን ሊያስተጓጉል የሚችል ወይም ማንኛውም ሌላ አጠራጣሪ ድርጊት ጥቆማ ማድረግ ይችላሉ።

መቼ ጥቆማ መስጠትይኖርብዎታል?

👉የምርጫ ሒደቶች ሲስተጓጎሉ ሲመለከቱ፣

👉ከላይ የተጠቀሱትን ክስተቶች በቀጥታ ከተመለከቱ፣

👉የዐመፅ ወይም የግጭት ሥጋት ካለ፣

👉እንዲሁም አስቸኳይ ዕርምጃ የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ምርጫን የሚያውኩ ክስተቶች ከተመለከቱ።


እንዴት ጥቆማ መስጠት ይችላሉ? በሚከተሉት መንገዶች ጥቆማ መስጠት ይችላሉ፦

👉በነፃ የስልክ መስመር 6214 ላይ በመደወል

👉አጭር የጽሑፍ መልዕክት ወደ 7555 በመላክ

ሪፖርት ሲያደርጉ የሚከተሉትን መረጃዎች ለማካተት ይሞክሩ፦

👉ምን እንደተከሰተ ፣ የት እንደተከሰተ ፣ መቼ እንደተከሰተ ፣ ማን እንደተሣተፈበት (የሚታወቅ ከሆነ) ማን ጥቆማ መስጠት ይችላል?

የመገናኛ መንገዶች

👉ነፃ የስልክ መስመር 6214

👉አጭር የጽሑፍ መልዕክት 7555

👉አድራሻ: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ| አዲስ አበባ

ኢትዮጵያ ትመርጣለች !የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር ይረጋገጣል!!ምርጫ የሕዝብ ሉዓላዊነት እውነተኛ መገለጫ፣ የዜጎች የባለቤትነት እና የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር የ...
30/05/2026

ኢትዮጵያ ትመርጣለች !
የሕዝብ ሉዓላዊነት፣ የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር ይረጋገጣል!!

ምርጫ የሕዝብ ሉዓላዊነት እውነተኛ መገለጫ፣ የዜጎች የባለቤትነት እና የውሳኔ ሰጪነት መብት በተግባር የሚረጋገጥበት ወሳኝ መድረክ ነው።

እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚገነባውም፣ የሕዝብን ፍጹም ውሳኔ ሰጪነት በመቀበልና በማክበር ላይ ብቻ ነው። ሕዝብን "በምርጫ አትሳተፉ፣ አትምረጡ" በማለት ለማስፈራራት መሞከር፣ እንዲሁም “እኔ አውቅልሃለሁ" በሚል የተሳሳተ የሞግዚትነት መንፈስ የዜጎችን ነፃ ፈቃድ ለመቀማት መሻት ለሕዝብ ያለን ንቀት የሚያሳይ፣ ከዘመኑ የሕዝብ የፖለቲካ ንቃተ ሕሊና ጋር የማይሄድ ኋላ ቀር አካሄድ ነው።

ሕዝባችን ግን ከእነዚህ ሁሉ የተዛቡ የፖለቲካ አመለካከቶች እጅግ ልቆ የሄደ፣ የሚበጀውንና የማይበጀውን ጠንቅቆ የሚያውቅ፣ እንዲሁም የሀገሩን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በራሱ ሚዛናዊነት መወሰን የሚችል እጅግ አስተዋይና እውነተኛ ዳኛ ነው። ለዚህም አንዱና ዋነኛው ማረጋገጫ፣ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች ከወዲሁ በንቃት በመመዝገብ የሀገራቸውን ብሩህ መጻኢ ዕድል ለመወሰንና የሚበጀውን ለመምረጥ ያሳዩት ከፍተኛ ዝግጁነትና ታሪካዊ ቁርጠኝነት ነው።

ስለሆነም፣ የሕዝብን ነፃ ምርጫ ማክበር የዲሞክራሲያዊነታችን መለኪያ ብቻ ሳይሆን የሀገራዊ ሕልውናችን እና የአንድነታችን ፅኑ መሠረት ነው። ይህ 7ኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ለሀገራችን ብቻ ሳይሆን፣ በመላው የአፍሪካ አህጉር የእውነተኛ ዲሞክራሲንና የሕዝብን የውስጥ አቅም በተግባር ለማሳየት የሚኖረው አዎንታዊ አንድምታ እና ምሳሌነት እጅግ የላቀ ነው።

#ዲሞክራሲ
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ ሲባል…  የዴሞክራሲ ዋነኛ መገለጫው በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ሒደት መሳተፋቸው ነው። በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች እን...
30/05/2026

42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ ሲባል…

የዴሞክራሲ ዋነኛ መገለጫው በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ ሒደት መሳተፋቸው ነው።

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደሚወዳደሩ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

እነዚህ ፓርቲዎች የፖሊሲ አማራጭ ሃሳቦቻቸውን ለሕዝብ በስፋት ያስተዋወቁ ሲሆን፤ መራጮች ይበጃል የሚሉትን ለመምረጥ በርካታ አማራጭ አግኝተዋል።

ዜጎች ለሀገር ዕድገት ይበጃል የሚሉትን በድምጻቸው ወደ ሥልጣን ለማምጣት ከተለያዩ ፓርቲዎች የሚመጡ ፖሊሲዎችንና እሳቤዎችን እንዲያወዳድሩ ያስችላቸዋል።

በመጪውን ሰኞ በሚካሄደው ምርጫ ፓርቲዎች ነፃ እና ፍትሃዊ በሆነ መልኩ ተወዳድረው አሸናፊው ሕዝቡን ይወክላል።

የሃሳብ ነፃነት፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብቶች ሲከበሩ ብዝሃ ፓርቲ ስርዓት ስኬታማ ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሒደት ይህንን እያስተናገደች ትገኛለች።

"በምርጫ ቀን የሚወክለንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል" ነዋሪዎችላፍቶ፣ ግንቦት 21/2018:- በምርጫ ቀን የሚወክለንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነ...
29/05/2026

"በምርጫ ቀን የሚወክለንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል" ነዋሪዎች

ላፍቶ፣ ግንቦት 21/2018:- በምርጫ ቀን የሚወክለንን ፓርቲ ለመምረጥ ተዘጋጅተናል ሲሉ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ።

መጪው ግንቦት 24/2018 ዓ.ም 7ኛው ጠቅላላ ሃገራዊ ምርጫ የሚካሄድ ሲሆን ብዛት ያለው ህዝብም የምርጫ ካርድ ወስደው 'ይሆነናል ይበጀናል' ብለው ላመኑበት ፓርቲ ድምፃቸውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል።

የላፍቶ ኮሙኒኬሽንም በቅድመ ምርጫ የህዝቡን ዝግጁነት አስመልክቶ ከነዋሪዎች ጋር ቆይታ አድርጓል።

ነዋሪዎች እንደገለፁት የፓርቲዎችን ማኒፌስቶ በመከታተል በምርጫው እለት ለሃገር እድገት፣ ለሰላምና ለዲሞክራሲ የሚሰራ ፓርቲ ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

በምርጫው እለት የትኛውም የምርጫ ካርድ የወሰደ ሰው ሳይመርጥ ድምፁን ማባከን የለበትም ያሉት ነዋሪዎች ከራሳቸው አልፈው የአካባቢውን ነዋሪዎችና ጎረቤቶቻቸውን በመቀስቀስ ንቁ ተሳታፊ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።

29/05/2026

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ተዘጋጅቷል

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣3. አግባብ ባለው አካል ...
28/05/2026

ማንኛውም ተዘዋዋሪም ሆነ ተቀማጭ የዕጩ ወኪሎች ግዴታ

1. የምርጫ ኃላፊው የሚሰጠውን ትዕዛዞች ማክበር አለበት፣
2. የምርጫ ሂደቱን ከሚያውኩ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣
3. አግባብ ባለው አካል ሲጠየቅ መታወቂያውን ማሳየት አለበት፣
4. የምርጫ ሕጉን ማክበር አለበት፣
5. የምርጫውን ሂደት የመከታተል ተግባሩን ሲያከናውን መራጮች ማንን መምረጥ እንዳለባቸው አስተያየት ከመስጠት ወይም ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር የለበትም፣
6. የምርጫ ቁሳቁሶችን መያዝ፥ ማንሳት፤ መነካካት ወይም በቁሳቁሶቹ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ተግባራትን መፈጸም የለበትም፣
7. የምርጫ ጣቢያውን ኃላፊ ወይም ሠራተኛ ከማስፈራራት ወይም ሥራውን ከሚያደናቅፉ ተግባራት መቆጠብ አለበት፣
8. ወደ ድምፅ መስጫ ክፍሎች መግባት የለበትም፣
9. ቦርዱ የሚያወጣውን የሥነ ምግባር ደንብ መፈረም እና ማክበር ይገባዋል፡፡

ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 121

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lafto woreda 05 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share