11/11/2025
#የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አርሶአደርና ከተማ ግብርና ፅ/ቤት በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 9 አርሶአደርና ከተማ ግብርና ፅ/ቤት በመገኘት የልምድ ልውውጥ አካሂዷል።
ወረዳ 9 ፓርቲ ሚዲያ
የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አርሶአደርና ከተማ ግብርና ፅ/ቤት ልዑክ ቡድን በወረዳ 9 አርሶአደርና ከተማ ግብርና ፅ/ቤት እየተከናወነ የሚገኘውን የሌማት ቱሩፋት ከተማ ግብርና የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም ተሞክሮ የሚሆኑ ተግባራት ምልከታ ማድረግ ችለዋል።
በልምድ ልውውጡ ላይ ሁለንተናዊ ብልፅግናን በማረጋገጥ ሁሉም ዜጋ የተመጣጠነ ምግብ እንዲኖረው የሚያደርገውን የሌማት ቱሩፋት እና የከተማ ግብርና ፕሮግራሞች ውጤታማ ለማድረግ ወረዳው በልዪ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ማየት እንደተቻለ የተገለፀ ሲሆን ተያይዞም
እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶችን ልምድ ከመቅሰም በተጨማሪ ተሞክሯቸውንም በማካፈል ለጋራ ብልፅግ ማስቀጠል ወሳኝነት እንዳለው የተጀመረው የሌማት ቱሩፋት ፕሮግራም ከንቅናቄ ስራዎች ተሻግሮ በወረዳው በመደበኛነት እየተከናወነ መሆኑንና የበርካታ ነዋሪዎችን ህይወት እየደጎመ እንደሚገኝ መመልከት እንደተቻለ ተገልጿል።
በመጨረሻም በዶሮ እርባታ፣ በንብ ማነብ፣ በከብት ማድለብ፣ በወተት፣ በእንቁላል እና በመሳሰሉት የሌማት ቱሩፋቶች እንዲሁም በጓሮ አትክልት እየተገኘ ያለው ስኬት በከተማችን በውስን ቦታ ላይ ለመተግበር ያስቸግራል የሚለው የአይቻልም መንፈስ በወረዳው የተሰበረበት መሆኑ ልዑኩ ጠቅሶ በልምድ ልውውጡም በርካታ ተሞክሮዎችን እንዳገኙ ገልፀዋል ።
2/3/18