22/04/2026
#ኢራን ተወካይ አለመላኳን ተከትሎ ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የተጣለው የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲራዘም ወሰኑ።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የሚካሄደው ወታደራዊ ጥቃት ለጊዜው እንዲቆም እና የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንዲራዘም ትዕዛዝ አስተላለፉ።
ፕሬዝዳንቱ ባወጡት መግለጫ፥ውሳኔው የተላለፈው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ እና ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ትራምፕ ገለጻ የኢራን መንግስት አሁን ካለበት ውስጣዊ መከፋፈል ወጥቶ የተቀናጀ የሰላም ሃሳብ እስኪያቀርብ ድረስ ጥቃቱ ይዘገያል።
ይሁን እንጂ የአሜሪካ ጦር በኢራን ላይ የጀመረውን የባህር ላይ እገዳ (Blockade) አጠናክሮ እንዲቀጥልና ለማንኛውም ወታደራዊ እርምጃ ዝግጁ ሆኖ እንዲቆይ ታዟል፥ውይይቶች ተጠናቀው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ እስኪደረስ ድረስ የተኩስ አቁሙ ጸንቶ እንደሚቆይም ተጠቁሟል።
፦ World Daily News