27/08/2026
የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብሩን በማረቆ ልዩ ወረዳ አከናወነ::
(GIE)
# # # # # # #
(ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብር አካል የሆነውን የአረንጓዴ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ በማከናወን ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች ድጋፍ አድርጓል።
በመርሃ ግብሩ የአረንጓዴ ችግኝ ተከላ የተከናወነ ሲሆን፣ ለአቅመ ደካማ ቤተሰቦች ልጆች የሆኑ 100 ተማሪዎች ከ800 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የመማሪያ ቁሳቁሶችና ቦርሳዎች ድጋፍ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢጃራ ተስፋዬ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ማዕከል ያደረገ የልማት ስራዎች የሚከተል መሆኑን ጠቁመው ይህ በተግባር የሚገለጸው ህዝብን በቀጥታ ተጠቃሚ በሚያደርጉ ሥራዎች መሆኑን አስረድተዋል።
አቶ ኢጃራ፣ ለአቅመ ደካማ ቤተሰቦች ልጆች የሆኑ 100 ተማሪዎች ከ800 ሺህ ብር በላይ የሚገመቱ የመማሪያ ቁሳቁሶችና ቦርሳዎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።
ተማሪዎችን መደገፍ የነገን ትውልድ መደገፍ መሆኑን ጠቁመው፣ አካባቢን መጠበቅም ለመጪው ትውልድ የተሻለ ሀገር ለማስረከብ የሚያግዝ ዘላቂ ሥራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብሩ አካል የሆነ የአረንጓዴ ችግኝ ተከላ በልዩ ወረዳው መከናወኑ የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ኢንስቲትዩቱ በማህበራዊ ኃላፊነቱ ለህብረተሰቡ የሚያበረክተውን ተግባር በቀጣይም እንደሚያጠናክር አስታውቀዋል።
የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ያደረገው ድጋፍ የሚደነቅና የሚመሰገን መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና አስተዳዳሪው ድጋፉ ተቸግረው ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ጉዟቸውን ለማገዝ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ጠቁመዋል።
በመርሃ ግብሩ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ የክትትል እና የእንክብካቤ ሥራ በትኩረት እንደሚከናወን አቶ ጀማል ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የማረቆ ልዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል አማሮ፣ የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢጃራ ተስፋዬን ጨምሮ የልዩ ወረዳውና የኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ኃላፊዎችና ወጣቶች ተሳትፈዋል።
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/GIE2023E
Website:- https:www.gie.gov.et/
Telegram: - https://t.me/ethiopiangeology
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.