28/02/2026
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በአጭር ኮርስ ለ5ኛ ዙር ያሰለጠናቸው እስትራቴጂክ አመራሮች በዛሬ ዕለት አስመረቀ።
የካቲት 20/2018 ዓ/ም
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በአጭር ኮርስ ለ5ኛ ዙር ያሰለጠናቸው እስትራቴጂክ አመራሮች በዛሬ ዕለት አስመርቋል ።
በምርቃቱ በክብር እንግድነት የተገኙት ሌ/ጄኔራል በላይ ስዩም ናቸው ተማሪዎች ተመርቃቹ ወደ ስራ ገበታችሁ ስትመደቡ የሠራዊታችን የማድረግ አቅሙን የሚጨምር ዘመናዊ አሰራርን በመዘርጋት ዉጤታማ አመራር በመስጠት የሠራዊታችንን ልዕልና እንድታረጋግጡ እያሳሰብኩኝ በዛሬ ዕለት የተመረቃችሁ አመራሮች እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብሏል።
የመከላከያ ዋር ኮሌጅ በአለማቀፋዊ፣ አሁጉራዊ፣ ቀጠናዊ እንዲሁም ሀገራዊ የፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች በአጭር ኮርስ በረጅም ኮርስ እንዲሁም በተንቀሳቃሽ የትምህርት ፕሮግራም እያስተማረና እያሰለጠነ የወደፊት መሪዎች እያዘጋጀ ይገኛል።