Prosperity Party Yeka Woreda 02 Branch-ብልፅግና

Prosperity Party Yeka Woreda 02 Branch-ብልፅግና ይሄ የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፌስቡክ ገፅ ነው!!
(1)

መጪውን የአዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ተከፈተ።በየካ ክፍለ ከተማ መጪውን የአዲስ ዓመት በዓል አስመልክቶ  "መሠረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ...
03/09/2026

መጪውን የአዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ የንግድ ትርኢት እና ባዛር ተከፈተ።

በየካ ክፍለ ከተማ መጪውን የአዲስ ዓመት በዓል አስመልክቶ "መሠረታዊ የግብርናና የኢንዱስትሪ ፍጆታ ምርቶችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማኅበረሰባችን በማቅረብ ገበያን እናረጋጋለን!" በሚል መሪ ሀሳብ የበዓል ባዛር ተከፍቷል።

በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ኢንዱስትሪ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኤፍሬም ግዛው ባዛሩ ሻጮችንና ሸማቾችን በቀጥታ ለማገናኘት ያለመ የግብይት መድረክ መሆኑን ገልጸዋል።

ውጤታማና አጥጋቢ የግብይት ሥርዓት እንዲሰፍን የሁሉም አካላት ሚና ወሳኝ መሆኑን ያመለከቱት ዶ/ር ኤፍሬም ባዛሩ በሰላማዊና ሥርዓት በተሞላበት መልኩ እንዲጠናቀቅ የጸጥታ አካላት በቅንጅት መሥራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የየካ ክፍለ ከተማ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው አስራት በበኩላቸው፣ ባዛሩ ለነዋሪዎችና ለአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት የሚያግዝ፣ የግብይት ሥርዓቱን የሚያሻሽልና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የሚያበረክት መሆኑን ገልጸዋል።

የባዛሩ ዓላማ በሸማቾች እና በአምራቾች መካከል ቀጥተኛ የግብይት ሥርዓትን በማጠናከር የምርት አቅርቦትን ማሳደግና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማኅበረሰቡ ማቅረብ መሆኑን ያመለከቱት አቶ እንዳልካቸው፣ ለባዛሩ ስኬታማ አፈጻጸም የተረባረቡ አካላትን በአስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።

ባዛሩ በቀጣይም በቅንጅትና በተቀናጀ አሠራር እንዲጠናከር አስፈላጊው ሥራ በየደረጃው መከናወን እንዳለበትም ጠቁመዋል።

የተከፈተው የበዓል ባዛር እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ የሚቆይ ሲሆን፣ የክፍለ ከተማው ንግድ፣ ኢንዱስትሪ ልማት፣ ህብረት ሥራ፣ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና እንዲሁም ሥራና ክህሎት ተቋማት በጋራ በመሆን የባዛሩን አገልግሎት እያስተባበሩ ይገኛሉ።
#የካ

ለአዲስ ዓመት፣ የተጠናከረ የግብርና ምርት አቅርቦት!በየካ ወረዳ 02 በእሁድ ገበያ ለአዲስ ዓመት በዓል የሚሆን በቂ፣ ጥራት ያለውና ተመጣጣኝ የግብርና ምርት አቅርቦት ተጠናክሮ ቀጥሏል።መጪው...
03/09/2026

ለአዲስ ዓመት፣ የተጠናከረ የግብርና ምርት አቅርቦት!

በየካ ወረዳ 02 በእሁድ ገበያ ለአዲስ ዓመት በዓል የሚሆን በቂ፣ ጥራት ያለውና ተመጣጣኝ የግብርና ምርት አቅርቦት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

መጪውን በዓል አስመልክቶ የወረዳው አስተዳደር ከአምራቾች ጋር በመቀናጀት ያዘጋጀው ይህ ገበያ፣ ከአምራች ወደ ሸማች የሚደርሰውን የምርት ሰንሰለት በማሳጠር ህብረተሰቡ ግዢውን በአቅራቢያው፣ በቀላሉና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲፈጽም አስችሏል።

በገበያው ከሸማች ፍላጎት በላይ በቂና ጥራት ያላቸው ምርቶች መቅረባቸው ተረጋግጧል። በዚህም የበዓሉን የግዢ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገው የአቅርቦት፣ የጥራትና የዋጋ ቁጥጥር ስራ በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል።

ይህም በበዓሉ ሰሞን ሊከሰት የሚችለውን ያላግባብ የዋጋ ጭማሪ በመከላከል፣ ሸማቹ ማህበረሰብ የበዓል ግዢውን በምቹ ሁኔታ እንዲፈጽም እያገዘ ይገኛል።

የየካ ወረዳ 02 አስተዳደርም የአዲስ ዓመት በዓል በደስታና በሰላም እንዲከበር፣ በቂ የምርት አቅርቦትን ከጥራትና ከዋጋ ቁጥጥር ጋር በማስተሳሰር ስራውን አጠናክሮ ይቀጥላል።

እሁድ ገበያ — ከአምራች ቀጥታ ወደ ሸማች!

በቂ አቅርቦት • ጥራት • ተመጣጣኝ ዋጋ

የወል ትርክታችን ለህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን!​የጋራ ታሪካችን፣ እሴቶቻችንና የነገ ተስፋችን የተጣመሩበት የወል ትርክታችን የህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን ጠንካራ መሰረት ነው። ባለፉት ዘመናት ...
02/09/2026

የወል ትርክታችን ለህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን!

​የጋራ ታሪካችን፣ እሴቶቻችንና የነገ ተስፋችን የተጣመሩበት የወል ትርክታችን የህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን ጠንካራ መሰረት ነው። ባለፉት ዘመናት ያሳለፍናቸውን ፈተናዎችና ያስመዘገብናቸውን ድሎች በበጎና በጋራ እይታ በመቃኘት፣ ለነገዋ ሀገራችን ብሩህ መንገድ የመክፈት ሀገራዊ ኃላፊነታችንን እንወጣለን።

​ልዩነቶቻችን የውበታችንና የጥንካሬያችን ምንጭ እንጂ የመለያየታችን ምክንያት አይደሉም። በጋራ መከባበር፣ በፍቅርና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ህብረት በመፍጠር የጥልና የጥርጣሬ ትርክቶችን በይቅርታ በመተካት የህብረ-ብሔራዊ አንድነታችንን እናጸናለን።

​በዚህም አላማ በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 05፣ 06፣ 07 እና 08 አስተባባሪነት "የወል ትርክታችን ለህብረ-ብሔራዊ አንድነታችን" በሚል መሪ ቃል የገዢ ትርክት መድረክ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

ሀገር የምትገነባው በሁሉም ዜጎቿ ታሪካዊ አሻራ ነው!​የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የደግነት ጥንታዊ እሴቶቻችን የኅብረተሰባችን ጠንካራ መሠረቶች ናቸው። እነዚህን በጎ እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውል...
02/09/2026

ሀገር የምትገነባው በሁሉም ዜጎቿ ታሪካዊ አሻራ ነው!

​የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የደግነት ጥንታዊ እሴቶቻችን የኅብረተሰባችን ጠንካራ መሠረቶች ናቸው። እነዚህን በጎ እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ በማሸጋገርና በዕለታዊ ሕይወታችን ውስጥ በተግባር በመግለጽ፣ የሕዝባችንን ዘመናትን የተሻገረ ብዝሃ-አብሮነትና ወንድማማችነት ይበልጥ እየተጠናከረ እንገኛለን።

​ብልፅግና ፓርቲ ሰው-ተኮርና አሳታፊ እሳቤዎችን መመሪያ በማድረግ፣ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተለመደው ወቅታዊ እንቅስቃሴ ወደ ተቋማዊና ዘላቂ ሥራ እንዲሸጋገር አድርጓል። ይህም አገልግሎቱ በተደራጀ፣ በተቀናጀ እና ውጤታማ በሆነ መንገድ ለወገኖቻችን እንዲደርስ የማስቻል አቅሙን አሳድጎታል።

​በዚሁ መሠረት በከተማችንና በየአካባቢያችን የተካሄዱት የበጎ አድራጎት ሥራዎች በርካታ አቅመ-ደካሞችና አነስተኛ ገቢ ያላቸው ወገኖቻችን ተከባካቢና ደጋፊ እንዲያገኙ አስችለዋል፤ ማኅበራዊ ፍትሕንም በተግባር አረጋግጠዋል። ይህም የበጎ አድራጎት አገልግሎት የዜጎችን ሕይወት በከፍተኛ ደረጃ የመቀየር አቅም እንዳለው በተጨባጭ ያሳየ ነው።

​ወደፊትም ቢሆን ይህን ተጀምሮ ተስፋ የፈነጠቀውን የልማትና የመደጋገፍ ጉዞ አጠናክረን እንቀጥላለን። በጎነትን የዘወትር ባህላችን፣ አገልግሎታችንን ደግሞ በጠንካራ ተቋማዊ አሠራር የተደገፈ በማድረግ፣ ይበልጥ የተሳሰረችና የበለፀገች ሀገርን በጋራ እንገነባለን።
#የካ

የአስተሳሰብና የተግባር አንድነታችንን በማጠናከር በተደመረ ትጋታችን ሀገራችንን እንገነባለን!ለሀገር ዕድገት፣  ለህዝብ ተጠቃሚነት የድርሻን መወጣት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ የዜግነት ሀ...
02/09/2026

የአስተሳሰብና የተግባር አንድነታችንን በማጠናከር በተደመረ ትጋታችን ሀገራችንን እንገነባለን!

ለሀገር ዕድገት፣ ለህዝብ ተጠቃሚነት የድርሻን መወጣት የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ የዜግነት ሀላፊነት ነው፡፡ ሀገራችን የምትገነባው በጠንካራ ተቋማቶቿ እንዲሁም በሁሉም ዜጎቿ ታሪካዊ አሻራ በመሆኑ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ሀገራዊ እሴቶቻችንን ማጠናከር ተገቢ ነው።

የተቸገረን መርዳት፣ የተራበን ማብላት፣ የወደቀን ማንሳት፣ የተስፋ ቃል መናገርና በችግር ጊዜ አብሮ መቆም የሰብዓዊነትና የዜግነት ትልቁ መገለጫ ሲሆን፣ ለኢትዮጵያዊያን ደግሞ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገሩ የመጡ ማህበራዊ እሴቶች ናቸው፡፡

በሀሳብ የበላይነት ማመን፣ ምክንያታዊነትን መላበስ፣ ለህግ የበላይነት ተገዢ መሆን፣ የሌሎችን መብት ማክበር፣ ለሰላም መቆም፣ ለማህበረሰባችን ብቻም ሳይሆን ለሚመጣው ትውልድ ፍትሀዊ ተጠቃሚነት አሻራን ማሳረፍም ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ ሀላፊነትና ግዴታ መሆኑን መገንዘብ ይገባል፡፡

የህዝባችን የጠነከረ ማህበራዊ ትስስር የተገነባው በደስታውም በሀዘኑም አንዱ ለአንዱ አለኝታ በመሆን ነው፡፡ የመረዳዳትን፣ የመደጋገፍን፣ የመተሳሰብንና የአብሮነትን እሴቶችን በተግባር መተርጎም ለጋራ እጣፈንታችን ወሳኝ ሚና አለው፡፡

ሀገራዊ ጉዳዮችን ከግል ፍላጎት የሚያስቀድም አስተሳሰብ ስንላበስ፣ እጆቻችንን አብሮ ለመስራት እና ለመረዳዳት ስናስተባብር፣ ጉልበታችንን፣ ገንዘባችንን፣ እውቀታችንን ለሀገር ግንባታ ስናስተባብር የምንጓጓላትን የበለፀገች ኢትዮጵያን በአጠረ ጊዜ ውስጥ እውን እናደርጋለን፡፡

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት


ዛሬ 33ኛውን ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ “ብሩህ ነገን በዛሬ አዕምሮዎች” በሚል መሪ ቃል አስጀምረናል። ይህ ጉባኤ በየዓመቱ የምናካሂደው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ተደራሽነትን ለማስ...
01/09/2026

ዛሬ 33ኛውን ከተማ አቀፍ የትምህርት ጉባኤ “ብሩህ ነገን በዛሬ አዕምሮዎች” በሚል መሪ ቃል አስጀምረናል።

ይህ ጉባኤ በየዓመቱ የምናካሂደው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን ጤናማ እና ውጤታማ ለማድረግ፣ በዘርፉ የተሰሩትን ጠንካራ ስራዎች ልምድ የምንቀምርበት፣ የሚታረሙትንም ለይቶ በጋራ መፍትሄ የምንሰጥበትና በጋራ እቅጣጫ የምንይዝበት ጉባኤ ነው ።

የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በከተማ አስተዳደራችን በልዩ ትኩረት ሰርተን የተማሪዎች ውጤት እየተሻሻለ መጥቷል። ዛሬ በከተማችን የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤት ወደ 33 በመቶ መሻሻል አሳይቷል። ነገር ግን አሁንም ከፍ ያለ ውጤት እንጠብቃለን፤ ገና ብዙ መሥራት ይጠበቅብናል።

መምህራን፤ ባለድረሻ አካላት በእልህ ሰርተን መፍጠር የሚችሉ፣ ችግር የሚፈቱ፣ በሥነ ምግባር የታነፁ፣ እውቀት የታጠቁ ተማሪዎችን በብዛት ለመፍጠር መረባረብ ይጠበቅብናል።

ከተማ አስተዳደራችን ዋናውን ኢንቨስትመንት ትምህርት ላይ እናውል ብለን፣ ትልቁን በጀት ለትምህርት ዘርፍ እንዲሆን አድርገናል። ትውልድ ላይ ከመሰረቱ መስራት ወሳኝ በመሆኑ፣ ዋና የእዕምሮ እድገት በጨቅላ ህፃንነት ወቅት በመሆኑ ቀዳማይ ልጅነት ላይ እየሰራን እንገኛለን። በዚህ አግባብ ከመሰረቱ ጀምረን እየሰራን በአንደኛ ደረጃ እንዲሁም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ከፍተኛ ውጤት እና በዲሲፕሊን የታነፀ ትውልድ እንጠብቃለን።

እስካሁን በተገኘው ውጤት ሁላችሁንም ከልብ እያመሰገንኩ፤ በቀጣይም በእውቀት የበለፀጉ፣ በስነምግባር የታነፁ፣ አልቀው የሚሰሩ ተማሪዎች ለመፍጠር ከልብ፣ ዋጋ ከፍለን ተባብረን እንድንሰራ አደራ እላለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የአረንጓዴ አሻራ ቱሩፋቶች ለትውልድ ተሻጋሪ  ድሎች መሰረት ናቸው!የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመጠበቅ፣ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ለማልማት እና ለቀጣይ ...
01/09/2026

የአረንጓዴ አሻራ ቱሩፋቶች ለትውልድ ተሻጋሪ ድሎች መሰረት ናቸው!

የአረንጓዴ አሻራ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያን ከአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመጠበቅ፣ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ለማልማት እና ለቀጣይ ትውልድ ምቹ አካባቢ ለማስረከብ የተጀመረ ህዝባዊ መሰረት ያለው ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።

ይህ ሀገራዊ ፕሮግራም የደን ሽፋንን በማስፋፋት፣ የመሬት መራቆትን በመከላከል፣ የውሃ ሀብቶችን በመጠበቅ እና የብዝሃ ሕይወት ሀብትን በማሳደግ ለሀገራችን ዘላቂ ልማት ጠንካራ መሠረት መሆኑ በተጨባጭ መረጋገጥ ጀምሯል፡፡

የአረንጓዴ አሻራ የልማት ኢኒሸቲቭ ከአካባቢ ጥበቃ ባሻገር የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እና አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት ምቹ መደላድል እየፈጠረ ይገኛል።

ሁሉም ዜጋ ችግኞችን ከመትከል ባሻገር ለተተከሉ ችግኞች በቂ እንክብካቤ በማድረግ የለመለመች፣ በሁለንተናዊ መልኩ ብልፅግናዋን ያረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመገንባት የበኩሉን አሻራ በማሳረፍ ተስፋን መትከል ይገባዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

31/08/2026
31/08/2026
የየካ በጎነት መንደር — የኪነ-ጥበብ ምሽትበጎነት ትውልድን ይገነባል፤ ኪነ ጥበብ ተስፋን ያበራል!በጎነት የትውልድ መሠረት፣ የሰብአዊነት ማስተሳሰሪያና የሕብረተሰባችን ዘላቂ ሀብት ነው። ይህ...
30/08/2026

የየካ በጎነት መንደር — የኪነ-ጥበብ ምሽት

በጎነት ትውልድን ይገነባል፤ ኪነ ጥበብ ተስፋን ያበራል!

በጎነት የትውልድ መሠረት፣ የሰብአዊነት ማስተሳሰሪያና የሕብረተሰባችን ዘላቂ ሀብት ነው። ይህን ታላቅ እሴት በኪነ-ጥበብ ውበትና ማራኪነት አጅበን ስናከብረው፣ አብሮነታችን ይበልጥ ይጠናከራል፤ ለወደፊቱም ብሩህ ተስፋን በመሰነቅ ለአገራዊ አንድነታችን ጽኑ መሠረት ይጥላል።

በዚህ ልዩ ምሽት በሚቀርቡ ግጥሞች፣ ዜማዎችና ጥበባዊ ትዕይንቶች አማካኝነት የጋራ እሴቶቻችንን በማጉላት አዎንታዊና የወል ትርክት እንገነባለን። ኪነ-ጥበብ የሰዎችን ልብ የመሳብ ፣ ህሊናን የማንቃትና የታሪክ እጣፈንታችን የተሳሰረ መሆኑን የማስረጽ ታላቅ ኃይል አላት። ጥበብና በጎነት ተጣብቀው ሲሄዱ ልዩነቶቻችንን አስግጠው ሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንን የሚያጠናክር አዲስ ትርክት ይፈጥራሉ።

ይህ የበጎነት መንደር እንቅስቃሴ ከመደመር አስተሳሰብ እይታ ጋር በእጅጉ የተሰናሰለ ነው። መደመር ማለት በጎ ተሞክሮዎችን፣ አዎንታዊ አስተዋጽኦዎችንና የአካባቢ አቅሞችን አስተባብሮ ለአገር ግንባታ ማዋል ነው፤ እያንዳንዷ አነስተኛ የበጎ አድራጎት ተግባር በትልቅ ደረጃ ተደምራ የማህበረሰባችንን ሁለንተናዊ ገጽታ ትለውጣለች። የየካ በጎነት መንደርም ይህንኑ የሰው ተኮር አገልግሎትና የነገዋን ውብ ሀገር የመገንባት ራዕይ ሰንቆ በፅናት እየሰራ ይገኛል።

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1,2,3 እና 4 ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የህዝብ ግንኙነት አዘጋጅነት በየካ በጎነት መንደር በጎነትንና የኪነ-ጥበብን ድንቅ ውህደት የሚደምቁበት ልዩ የኪነ-ጥበብ ምሽት ተዘጋጅቷል።
#የካ

Address

Ferensay Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity Party Yeka Woreda 02 Branch-ብልፅግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share