Tiratu Beyene Biltu ጥራቱ በየነ ቢልቱ

Tiratu Beyene Biltu ጥራቱ በየነ ቢልቱ Mayor of Hawassa City
(1)

ዛሬ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣባቸውን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ለከተማችን ተቋማት አስረክበናል!እነዚህ ማሽነሪዎች የመንገድና የመሠረተ ልማት ስራዎችን በፍጥነት ለማከናወንና ሌሎች አገ...
20/08/2026

ዛሬ ከ250 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣባቸውን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎች ለከተማችን ተቋማት አስረክበናል!

እነዚህ ማሽነሪዎች የመንገድና የመሠረተ ልማት ስራዎችን በፍጥነት ለማከናወንና ሌሎች አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍ ትልቅ ትርጉም ይኖራቸዋል። በተለይም ለማሽነሪ ኪራይ የሚወጣውን ወጪ በመቀነስ የከተማችንን ሀብት በተሻለ ሁኔታ ለልማት እንድናውል አቅም ይፈጥርልናል::

ይህን አቅም በመጠቀም የልማት ስራችንን በተሻለ አቅም፣ በተሻለ ፍጥነት እና በተሻለ ውጤት አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል!

የሀዋሳ አዲስ ውበትና አዲስ መልክ! ከተማችን ሀዋሳ በአዳዲስ የኮሪደር ልማቶቿ በየቀኑ መልኳን እያደሰች ትገኛለች። አረንጓዴ ልምላሜዋ፣ ከሀይቋ የሚነሳው ተስማሚ አየሯ፣ የመዝናኛ ስፍራዎቿ እ...
09/08/2026

የሀዋሳ አዲስ ውበትና አዲስ መልክ!

ከተማችን ሀዋሳ በአዳዲስ የኮሪደር ልማቶቿ በየቀኑ መልኳን እያደሰች ትገኛለች። አረንጓዴ ልምላሜዋ፣ ከሀይቋ የሚነሳው ተስማሚ አየሯ፣ የመዝናኛ ስፍራዎቿ እና ሰፋፊ ጎዳናዎቿ ሀዋሳን ይበልጥ ውብና ተመራጭ አድርገዋታል።

ብዙዎችም ለስብሰባና ለኮንፈረንስ፣ እንዲሁም የእረፍት ጊዜያቸውን በሀዋሳ ለማሳለፍ መርጠዋት እየመጡ ነው።

ከተማችንም “ዳዌ ቡሹ!” ብላ እንግዶቿን በደስታና በፍቅር ለመቀበል ተዘጋጅታለች!

03/08/2026
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!ዛሬ የዘንድሮውን የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በሀዋሳ ከተማችን እጅግ በድምቀት፣ በሰላምና በተዋበ ሥነ ሥርዓት አክብረናል!በዓሉን ለ...
26/07/2026

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ዛሬ የዘንድሮውን የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በሀዋሳ ከተማችን እጅግ በድምቀት፣ በሰላምና በተዋበ ሥነ ሥርዓት አክብረናል!

በዓሉን ለማክበር ከሩቅም ከቅርብም ወደ ከተማችን የመጣችሁ እንግዶቻችን በመካከላችን በመገኘታችሁ ለበዓሉ የጨመራችሁት ድምቀት ሀዋሳን ይበልጥ ውብና ደማቅ አድርጓታል።

በዓሉን ለማክበር ወደ ከተማችሁ ሀዋሳ ስለመጣችሁም ከልብ እናመሰግናችኋለን። ዛሬ እናንተን በከተማችን ተቀብለን በማስተናገዳችን እጅግ ደስ ብሎናል።

በዚህ አጋጣሚ ከበዓሉ ስነ-ስርዓት ባሻገር ጥቂት ቀናት ቆይታችሁን አራዝማችሁ፤ የሀዋሳን ሐይቅ፣ የከተማችንን ውበት፣ የማይጠገበውን ንፁህ አየርና ከህዝባችን ፍቅርና እንግዳ ተቀባይነት ጋር እየተዝናናችሁ እንደ ቤታችሁ መልካም ጊዜ እንድታሳልፉ በክብር እጋብዛችኋለሁ።

በመጨረሻም ይህ ክብረ በዓል በዚህ ውበትና ድምቀት እንዲከበር የተባበራችሁ የቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት አመራሮች፣ ባለሀብቶች፣ ሆቴሎች; በጎ ፈቃደኞች ወጣቶች እና መላው የሀዋሳ ህዝብ ከፍ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።

መልካም በዓል!

22/07/2026

ሀዋሳ… እየፈካች ነው!

ይህን ሁሉ እንድናይ ላደረገልን ፈጣሪ ክብርና ምስጋና ይድረሰው!

የከተማችንን ለውጥ በየቀኑ ስንመለከት ትልቅ ተስፋ ይሰጠናል! የበለጠ እንድንሰራ ያነሳሳናል!

ይህ ውጤት የአንድ ሰው ወይም የአንድ ተቋም ስራ ሳይሆን፣ የህዝባችን፣ የመንግስት፣ የአመራር፣ የባለሙያዎች፣ የአማካሪዎች፣ የኮንትራክተሮችና የሁሉም የልማት አጋሮች በአንድ ልብ በመስራታቸው የተገኘ የጋራ ስኬት ነው።

4ኛውን ዙር የኮሪደር ልማት በ90 ቀናት ውስጥ አጠናቀን ለህዝብ ለማስረከብ ቀንና ሌሊት በትጋት ሰርተናል። በአሁኑም ወቅት ስራው በእቅዳችን መሰረት በመጠናቀቅ ላይ ነው። ሀዋሳ አዲስ ውበት ተጎናጽፋለች፤ በኮሪደር ልማቱም እየፈካች ትገኛለች።

ዛሬ የምናየው ሀዋሳ፣ ውብ፣ ንጹህ፣ ዘመናዊ እና ለነዋሪዎቿም ሆነ ለጎብኚዎች ምቹ የሆነች ከተማ የመሆን ራዕይዋ እውን እየሆነ መምጣቱን በግልጽ ያሳያል።

ለዚህ ታላቅ የለውጥ ጉዞ አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ ሁሉ ከልብ አመሰግናለሁ። ይህንን የመተባበር መንፈስ አጠናክረን ከቀጠልን፣ ሀዋሳ በቅርቡ የኢትዮጵያ የልማት፣ የውበትና የብልፅግና ተምሳሌት መሆኗ አይቀሬ ነው።

15/07/2026

ዛሬ በታሪካዊው የሀገራዊ ምክክራችን ዋዜማ፣ የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ የሆኑትን ክቡር ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን በጽሕፈት ቤቴ ተቀብያለሁ። በመጪው ሀገራዊ ምክክር ዙሪያ ለመወያየት እንዲሁም ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ተግባራት ጥበብ ለመቅሰም ችለናል፤ በተለይም የቢያፍራን የሰላም ሂደት በመምራት ያካበቱትን ልምድ አጋርተውናል። ይህም ኢትዮጵያ በምክክር ለምታረጋግጠው አንድነትና ዘላቂ የሰላም ጉዞ ላይ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ነው።

ኢትዮጵያ ለሚያበረክቱት አስተዋፅኦ ሁልጊዜም የላቀ ምስጋናዋን ታቀርባለች!

Jalabultii Marii Biyyaalessaa keenya seena-qabeessaa kanatti har'a michuu Itoophiyaa guddaa kan ta'an, Pirezdaantii Naayjeeriyaa duraanii, Kabajamoo Olusegun Obasanjo Waajjirakootti simadheera. Marii Biyyaalessaa dhufu kanarratti kan marii'anne yoo ta'u, hojiiwwan kanaan dura hojjetan irraa ogummaa argachuus dandeenyeerra. Keessumaa adeemsa nagaa Biyafiraa hoogganuudhaan muuxannoo kuufatan nuuf qoodaniiru. Kunis adeemsa tokkummaafi nagaa waaraa Itoophiyaan mariidhaan mirkaneessituuf barumsa guddaa kan kennudha.

Itoophiyaan gumaacha olaanaa gatiidhaan hin tilmaamane gumaachitaniif yoomiyyuu galata guddaa isiniif qabdi!

Today, on the eve of our historic National Dialogue, I received Ethiopia's dear friend H.E. Oluṣẹgun Ọbasanjọ in my office to discuss the upcoming National Dialogue and to draw on his wisdom from such journeys, where he shared with us his experience leading the Biafra Peace process. This experience offers a great lesson for Ethiopia’s journey toward ensuring unity and lasting peace through dialogue.

Ethiopia remains profoundly grateful for your invaluable contributions!

15/07/2026
በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የ4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፊል ገጽታ!የ4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ሀዋሳን ወደ ዘመናዊ፣ ስልጡንና ተወዳዳሪ ከተማ የሚያሸጋግር ትልቅ የለውጥ ፕሮጀክ ...
13/07/2026

በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የ4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ሥራችን ከፊል ገጽታ!

የ4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ስራ ሀዋሳን ወደ ዘመናዊ፣ ስልጡንና ተወዳዳሪ ከተማ የሚያሸጋግር ትልቅ የለውጥ ፕሮጀክ ነው።

ፕሮጀክቱ የመንገድ ግንባታን ብቻ ሳይሆን፣ ዘመናዊ የደህንነት ካሜራዎችን፣ ዲጂታል ስክሪኖችን እና ሌሎች በቴክኖሎጂ የተደገፉ የከተማ መሠረተ ልማቶችን በማካተት ለነዋሪዎቻችን የተሻለ፣ ደህንነቱ የተጠበቀና ዘመናዊ የከተማ አገልግሎት ለማቅረብ የያዝነው ራዕይ አካል ነው።

የ4ኛው ዙር የኮሪደር ልማት ሥራችን በጥቂት ቀናት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለህዝባችን አገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ እየሰራን እንገኛለን::

07/07/2026

የሰላም ጥሪ ለትግራይ

‎በመጀመሪያ ደረጃ የሚያስፈልገን ሰላም፣ ትብብር እና አብሮ መስራት ነው። በትግራይ ክልል ዳግም ጦርነት እንዲቀሰቀስ ከፍተኛ ፍላጎት ያላቸው አካላት ቢኖሩም፤ ጦርነት አውዳሚና ትርፍ የለሽ በመሆኑ እምቢ ብለናል። አሁንም ቢሆን ለሰላም፣ ለንግግርና ለውይይት በራችን ምንጊዜም ክፍት ነው። የራሳችንን ጥቅም መስዋዕት አድርገንና ተጎድተን እንኳ በትግራይ ዘላቂ ሰላም የሚመጣ ከሆነ ዋነኛ ፍላጎታችን እርሱ ብቻ ነው። እርስ በርስ መጠላለፍና መውደቅ ማንንም አይጠቅምም።

‎ይሁን እንጂ ለትግራይ ሕዝብ እውነተኛ መፍትሔ የሚመጣው የሕወሓት አመራሮች በወጣቶቻቸው ላይ እምነት ጥለው ለተተኪው ትውልድ ዕድል መስጠት ሲችሉ ብቻ ነው። የመደመር መንግሥት ዋነኛ መሻትና ግብ በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ላይ የሚታየው ልማትና ዕድገት በትግራይም ተደራሽ ሆኖ ማየት ነው።

‎ #የጠሚሩምላሾች

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tiratu Beyene Biltu ጥራቱ በየነ ቢልቱ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share