Bole 05 communication

Bole 05  communication ፈጣን እና ተዓማኒነት ያለው መረጃ እናደርሳለን�

Permanently closed.
ከብዙ ወደ አንድ ፣ አንዱም ፣ ወደ-እያንዳንዱ ቤት!የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “በአዲስ መሶብ ዲጅታል የአንድ ማዕከል በተንቀሳቃሽ አውቶቢስ የሚሰጡ 8ቱ አገልግሎቶች “- የገቢ አገልግሎ...
23/04/2026

ከብዙ ወደ አንድ ፣ አንዱም ፣ ወደ-እያንዳንዱ ቤት!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር “በአዲስ መሶብ ዲጅታል የአንድ ማዕከል በተንቀሳቃሽ አውቶቢስ የሚሰጡ 8ቱ አገልግሎቶች “

- የገቢ አገልግሎት (አዲስ ቲን ማውጣት)
- የንግድ አገልግሎት (ንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ ማደስ)
- የጤና (ለመንጃ ፈቃድ አካላዊ የጤና ምርመራ)
- የሲቪል ምዝገባ (መታወቂያ፣ ልደት እና ሌሎች)
- የአሸከረካሪ ተሽከርካሪ (የመንጃ ፈቃድ እና የቦሎ ዕድሳት)
- የኢትዮ ፖስታ (የመንገድ ፈንድ ክፍያ)
- የብሔራዊ መታወቂያ (አዲስ ምዝገባና የመረጃ እርማት)
- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (ቅድመ ክፍያ)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ከቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኪነ-ጥበብ ምሽት ተካሄደ።"አስተሳሳሪና የወል ትርክታችን ለዘላቂ አንድነት እና አብሮነ...
22/04/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ከቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኪነ-ጥበብ ምሽት ተካሄደ።

"አስተሳሳሪና የወል ትርክታችን ለዘላቂ አንድነት እና አብሮነታችን" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የኪነ-ጥበብ ምሽት ላይ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች እንዲሁም የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ አለምጸሀይ ሽፈራው በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በከተማዋ እየተመዘገቡ ያሉ የልማት ስራዎች የለውጡ አመራር ለህዝቡ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ኃላፊዋ አክለውም ኪነ-ጥበብ ህብረተሰቡን ለማስተማር ብሎም ለማዝናናት ካለው ሚና ባሻገር አስተሳሳሪና የወል ትርክታችን ለዘላቂ አንድነትና ለአብሮነታችን መጠናከር ያለውን ፋይዳ ሚናው የጎላ ነው" ብለዋል። አርቲስቶችና የጥበብ ባለሙያዎችም ህዝቡን ለሰላምና ለልማት ለአንድነት በማነቃቃት የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ-አስፈጻሚ አቶ አደፍርስ ኮራ በበኩላቸው፤ ክፍለ ከተማው ከማህበራዊ አገልግሎቶች ጎን ለጎን ለኪነ-ጥበብ ስራዎች ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸው፣ የዛሬው መርሐ ግብር የከተማና የክፍለ ከተማ አስተዳደሩን የተቀናጀ አሰራር የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል። አቶ አደፍርስ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍልና አመራሩ የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀፍታይ ገ/እግዚአብሔር፤ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለጎብኚዎች ደግሞ ሳቢ የማድረግ ስራ ውጤት እያመጣ መሆኑን ገልጸዋል። "የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና በአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ መሪነት የለውጡ አመራሮች ሌት ተቀን በመስራታቸው፣ አዲስ አበባ ዛሬ ላይ ውብ፣ ማራኪና አበባ ሆና የቱሪዝም ማዕከል መሆን ችላለች ሲሉ ኃላፊው በተጨማሪ ገልጸዋል።

በመድረኩ በአዲስ ዩኒቨርስቲ የቲያትርና ጥበባት ክፍል የተዘጋጀ ሙዚቃዊ ተውኔት ለታዳሚዎች ቀርቧል።

ቦሌ ኮሙኒኬሽን
ሚያዝያ 14/2018

የምርጫ ካርድ ወስደዋል?ባሉበት ሆነው በ*ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።...
15/04/2026

የምርጫ ካርድ ወስደዋል?

ባሉበት ሆነው በ*ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።

የዛሬው ካርድዎ የነገዋን ታላቂቷን ኢትዮጵያ መገንቢያ ዋነኛ መሣሪያ ነው!የምርጫ ካርድ ወስደዋል?

ባሉበት ሆነው በ*ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።

የዛሬው ካርድዎ የነገዋን ታላቂቷን ኢትዮጵያ መገንቢያ ዋነኛ መሣሪያ ነው!

 !  !!የቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 05 ነዋሪዎች፣ ወጣቶች በደማቅ ሁኔታ አክብሯል ። #መጋቢት24
02/04/2026

!
!!
የቦሌ ክፍለከተማ ወረዳ 05 ነዋሪዎች፣ ወጣቶች በደማቅ ሁኔታ አክብሯል ።
#መጋቢት24

የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ጉዞ- ከቀጣናዊ እርቅ እስከ ስልታዊ ዓለም አቀፍ ትስስርኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት ያስመዘገበቻቸው ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ...
02/04/2026

የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ጉዞ- ከቀጣናዊ እርቅ እስከ ስልታዊ ዓለም አቀፍ ትስስር

ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት ያስመዘገበቻቸው ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም ከማስከበር ባለፈ በቀጣናዊና በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተሰሚነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግረዋል።

ይህ የዲፕሎማሲ ጉዞ የሀገሪቱን ሉዓላዊነት በማፅናትና አዳዲስ ስልታዊ አጋርነቶችን በመፍጠር ረገድ ጉልህ ሚና ተጫውቷል።

በኢትዮጵያ የሰላም ዲፕሎማሲ ውስጥ እንደ ቀዳሚ ስኬት የሚጠቀሰው ከቀጣናው ሀገራት ጋር የነበሩ ቅራኔዎችን በመፍታት የዲኘሎማሲ ግንኙነቱን ውጤታማ ማድረግ መቻሉ ተጠቃሽ ነው፡፡

ይህም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኖቤል ሰላም ሽልማትን ከማስገኘቱም በላይ ኢትዮጵያ በጎረቤት ሀገራት መካከል ለሚፈጠሩ ግጭቶች ያላትን የአደራዳሪነትና የሰላም አስከባሪነት ሚና እንድታጠናክር አስችሏታል።

በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና የውኃ ሙሌት ሂደት የሀገሪቱን የሉዓላዊነት ዲፕሎማሲ የፈተነ ታላቅ ክስተት ነበር።

ኢትዮጵያ ከግብፅና ከሱዳን ጋር በነበራት የረጅም ጊዜ ድርድር የውጭ ጫናዎችን በጽናት በመቋቋም ግድቡን በራሷ አቅም የመገንባትና የመሙላት መብቷን በተግባር አረጋግጣለች።

ይህም ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ የሚለውን መርህ በማፅናት በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር የሚደረጉ ድርድሮች ውጤታማ እንዲሆኑ አዲስ መንገድ ከፍቷል።

በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ከተከሰተው ጦርነት ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያን አንድነት ለማስጠበቅ የተከናወኑ ተግባራት በታሪክ የሚጠቀሱ ናቸው።

በተለይም የ(በቃ) ንቅናቄን የመሰሉ ዓለም አቀፍ ድምጾች የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመመከት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበራቸው።

የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በኢኮኖሚና በባለብዙ ወገን ትብብር ረገድም አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።

ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር ሆና መመረጧ በኢኮኖሚ ካደጉና ታዳጊ ከሆኑ ሀገራት ጋር ያላትን ትስስር የሚያጠናክር ስልታዊ ስኬት ነው።

ይህም የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የሀገሪቱን የንግድ ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ባለፉት ስምንት ዓመታት ካጋጠሟት ዲፕሎማሲያዊ ማዕቀቦችና ጫናዎች ወጥታ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ የፖለቲካና የኢኮኖሚ መድረክ ያላትን ተፅዕኖ ፈጣሪነት ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገሯ ተረጋግጧል።

በበረከት ጌታቸው

AMN-Addis Media Network

“ጽዳት የዕለት ተዕለት ተግባራችን እንጂ የአንድ           ቀን ስራ አይደለም”!!    በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር  ጽዳትና ውበት  አስተዳደር ጽ/ቤት አስተባባሪነት ነዋሪ...
28/03/2026

“ጽዳት የዕለት ተዕለት ተግባራችን እንጂ የአንድ
ቀን ስራ አይደለም”!!

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ጽዳትና ውበት
አስተዳደር ጽ/ቤት አስተባባሪነት ነዋሪዎች፣ አመራሮች፣ ባለሙያዎች፣ ሽርክና ማህበራት እና የጽዳት አምባሳደሮች በተገኙበት "ቦሌ ወረዳ 05ን ቆሻሻን ያላግባብ የማይጣልባት ለነዋሪዎቿ ምቹ፤፧ውብ ፤ጽዱ እና ማራኪ ወረዳ እናረጋለን በሚል መሪ ቃል የጽዳት ንቅናቄ ተካሄደ።

በንቅናቄው ላይ የተገኙት የቦሌ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ወረዳውን ከቆሻሻ ነጻ፣ ለነዋሪዎች ምቹ፣ ውብና ማራኪ ለማድረግ ያለመ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ በአካባቢው ጽዳት ላይ የራሱን ሚና እንዲወጣ ሲሉ ጥሪኣቸውን አቅርበዋል።

የወረዳ 05 ጽዳትና ውበት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አትርሴ አራጋው፣ በበኩላቸው “ጽዳት የዕለት ተዕለት ተግባራችን እንጂ የአንድ ቀን ስራ ሊሆን አይገባም” ብለው በመግለጽ ፤ወረዳውን ቆሻሻ የማይጣልበት ፣ ለመኖሪያ ምቹና ውብ ለማድረግ ሁሉም ሕብረተሰብ በእኩል ሀላፊነት እንዲሳተፍ እና ይህ ዓይነት ንቅናቄ በቀጣይነት የሚቀጥል ልጆች የሚጫወቱበትና ነዋሪዎች በምቾት የሚኖሩበት አካባቢ እና መንደር ለመፍጠር የህብረተሰቡ ተሳትፎ ዋና ቁልፍ ነው በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

መጋቢት 19/2018 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ "Invest in Ethiopia 2026" የኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊዎች የዓለማቀፍ ኮንፈረንስ ማዕከልነቷን በተግባር እየገለጠች የመጣችውን ውቢቷ ከተማችን አዲስ...
26/03/2026

በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ "Invest in Ethiopia 2026" የኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊዎች የዓለማቀፍ ኮንፈረንስ ማዕከልነቷን በተግባር እየገለጠች የመጣችውን ውቢቷ ከተማችን አዲስ አበባን ጎበኙ።

ከ 71 በላይ ሀገራት በሚሳተፉበት የ"Invest in Ethiopia 2026" ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ለመሳተፍ የመጡ ባለሀብቶችና በዘርፉ የተሰማሩ ተዋናዮች፣ በመዲናዋ ያለውን ፈጣን የዕድገትና የልማት ስራዎች፣ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ጎብኝተዋል።

ከ800 በላይ ዓለም አቀፍ ባለሀብቶች፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የፖሊሲ አውጪዎች የሚሳተፉበት ይህ የቢዝነስ ፎረም በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል በይፋ ተጀምሯል።

Addis Ababa Tourism Commission

""የእንጠያየቅ መድረክ ተካሔደ!!"የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን  ጽ/ቤት ከወረዳዉ ምክር ቤት ፣ ሰላምና ፀጥታ  እና ከደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የእንጠያየቅ መድረክ ተ...
26/03/2026

""የእንጠያየቅ መድረክ ተካሔደ!!"

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት ከወረዳዉ ምክር ቤት ፣ ሰላምና ፀጥታ እና ከደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የእንጠያየቅ መድረክ ተካሔደ!!"

የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ኮሚዩኒኬሽን
ከወረዳዉ ምክር ቤት ሰላምና ፀጥታ እና ከደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከህብረተሰቡ የሚነሱ የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ጋር በተያያዘ አዋኪ ድርጊቶች እና ሌሎች የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት የእንጠያየቅ መድረክ ከነዋሪዎች እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ዉይይት አካሔደ ።

የወረዳ ዐ5 አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ዘላለም ተስፋዬ ፣ የወረዳ 05 ኮሚዩኒኬሽን ጽ/ቤት
ኃላፊ አቶ ሉሉ አለማየሁ እና የሰላም እና ጸጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ የሺዋስ ፣የሴክተር ኃላፊዎች ፣ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት እና ባለሙያዎች በተገኙበት ከዚህ በፊት ከህብረተሰቡ በተለያየ ጊዚያት በተሰበሰቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች እና ተሳታፊዎች በሚያነሷቸው መልካም አስተዳደር ዙሪያ የእንጠያየቅ መድረክ ውይይት ተካሒዷል።

በወይይቱ ላይ የተገኙት ወረዳ 05 አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ ዘላለም ተስፋዬ ይህ አይነት መድረክ መዘጋጀቱ በመደበኛ የአሰራር ስርዓት ያልተፈቱ የህብረተሰቡ መልካም አስተዳደር ችግሮች እንደዚህ ተለቅመው ወጥተው መቅረባቸው ለተቋማቶች በቅንጅት ለመፍታትና መፍትሔ ለመስጠት ያመቻል።

ነዋሪዎች በርካታ ልማቶችን ከመንግስት ጋር በጋራ ግንባር ቀደም ሆነው መስራት አለባቸው።ለዚህ ዛሬ ህብረተሰቡ ተወካዮች በተለያየ ጊዜያት ሲነሱ የነበሩ ጥያቄዎችን ይዛችሁ ማቅረባችሁ ምክር ቤቱ የህብረተሰቡን የልማት ተጠቃሚነት እና ተዳራሽ ለማድረግ አስፈጻሚ አካሉን ድጋፍና ክትትል በማድረግ ለችግሩ አፋጣኝ ምላሽ በማይሰጡ ተቋማት ላይ የተጠያቂነትን ስርዓትን
እያሰፈነ ይሄዳል ብለዋል ።

በመቀጠል በተለያዩ ጊዜያት ከምክር ቤት ጉባኤ፣ከህዝብ ወይይቶች ፣ከከባባዊ ቅኝት ፣ከድንገተኛ ሱፐርቪዥን የተወሰዱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በአቶ ዘላለም ተስፋዬ እንደመነሻ ቀርበው ከነዋሪዎች ተወካይም በርካታ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተነስተው ከተመረጡ ተቋማት ኃላፊዎችና ተወካዮች ለጥያቄዎች ምላሽ ከተሰጠ በኋላ ከመድረክየማጠቃለያ ሐሳብ ተሰጥቶበት ወይይቱ ተጠናቋል።

መጋቢት 17 /2018 ዓ.ም

""በደንብ መተላለፍ  ጥፋቶችና የሚያስከትሉት ቅጣት  በሚል ዕርስ  ዙሪያ  ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጠ።በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ማህበራዊ ፍርድ ቤት   በወረዳዉ ለሚገኙ ለተለያዩ ...
25/03/2026

""በደንብ መተላለፍ ጥፋቶችና የሚያስከትሉት ቅጣት በሚል ዕርስ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጠ።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ማህበራዊ ፍርድ ቤት በወረዳዉ ለሚገኙ ለተለያዩ ማ/ሰብ ክፍሎች ፣ከወረዳዉ ሴክተር ጽ/ቤቶች ለተወጣጡ ሰራተኞች ፣ቡድን መሪዎች
እና ኃላፊዎች ከወንጀል ሕጉ ተከፍለዉ ለፍርድ ቤቱ በተሰጡት 22 አንቀጾች ( ከወ/ሕግ ቁጥር 815 እስከ 862)ባለዉ ውስጥ ስለተገለጸዉ በደንብ መተላለፍ ጥፋቶችና የሚያስከትሉት ቅጣት በሚል ዕርስ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ መስጨበጫ ስልጠና ተጥቷል ።

ስልጠናውን የሰጡት የወረዳ 5 ማህበራዊ ፍርድ
ቤት ሰብሳቢ አቶ ሲሳይ ሽዋፈራው ናቸው።

በስልጠናዉ በማሕበራዊ ፍርድ ቤቱ ማቋቋሚያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር 31/199 ድንጋጌ መሰረት ከወንጀል ሕጉ ተከፍለዉ በፍርድ ቤቱ በተሰጡት 22 አንቀጾች ( ከወ/ሕግ ቁጥር 815 እስከ 862)በለዉ ወስጥ ስለተገለጸዉ የደንብ መተላለፍ ተግባራት በ 22ቱ እንቀጾች ምንነት ዙሪያ በዝርዝር ለሰልጣኞች ቀርቧልተ፣ከተሳታፊዎችም የተለያዩ ጥያቄዎች ሐሳቦች እና አስተያየቶች ተነስተዉ ለተነሱ ጥያቄዎች ከመድረክ ምላሽ ተጥቶ ስልጠናዉ ተጠናቋል።


መጋቢት 15/2018ዓ.ም

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር የሚገኙ የመንግስትና የግል ቅድመ መጀመሪያ ት/ቤቶች “ለሕጻናት ንባብ” በሚል መሪ ቃል የንብብ መርሐ ግብር   አካሄዱ።መርሐ ግ...
25/03/2026

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር የሚገኙ የመንግስትና የግል ቅድመ መጀመሪያ ት/ቤቶች “ለሕጻናት ንባብ” በሚል መሪ ቃል የንብብ መርሐ ግብር አካሄዱ።

መርሐ ግብሩ ላይ በወረዳው ትምሕርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ ኢፋ፣ የት/ቤቱ ርዕሰ መምህር ወ/ሮ እየሩሳሌም ተሾመ ፣ መምህራን ፣ ወላጆች፣ ተማሪዎች እና የትምሕርት ባለሙያዎች በተገኙበት ተካሄዷል።

በንቅኔቄው ላይ የተገኙት የወረዳው ትምሕርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ ኢፋ የንብብ ክህሎት ለሕጻናት እድገት እና ለትምህርታዊ ስኬት ያለውን ጠቀሜታ ገልጸዋል ለተሳታፊዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።ኃላፊ አክለውም በሕጻናት የንብብ ባህልን ለማጠናከር ት/ቤቶችና ወላጆች እና ባለሙያዎች በአንድነት እንዲሰሩ ለማበረታታት እና ወላጆችም በተቀመጠው የንባብ ቀን ከልጆቻቸው ጋር ተሳታፊ በመሆን የንባብ ባሕልን ማደበር ይገባል ብለዋል

በመጨረሻም በተማሪዎች ፊት ወላጆች የተለያዩ ተረቶችን መልዕክት አዘል መጽሐፎችን አንብበዋል።

መጋቢት 15/2018 ዓ.ም

""የሳይንስ እና የፈጠራ አዉደ ርዕይ  ተካሔደ!!በቦሌ ክፍለ ከተማ  ወረዳ 05  አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር ባሉ የግል እና የመንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች    የ2018  በጀት...
24/03/2026

""የሳይንስ እና የፈጠራ አዉደ ርዕይ ተካሔደ!!

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ስር ባሉ የግል እና የመንግስት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች የ2018 በጀት አመት የወረዳ 05 ት/ት ጽዳት/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ ኢፋ ፣የአዲስ ራዕይ ት/ቤት ርዕሰ መምህር ወ/ሮ እየሩሳሌም ተሾመ ፣የወረዳ አመራሮች የትምህርት ጽ/ቤት ባለሙያዎች፣ርዕሳነ መምህራን ፣መምህራን ፣ሱፐርቫይዘሮች ፣ወተመ ፣ የፈጠራዉ ባለቤት የሆኑ ተማሪዎች በተገኙበት በወረዳው አዘጋጅነት በአዲስ ራዕይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምርት ቤት" የሳይንስ ፈጠራ ስራ በሳይንስ የተካነ ትውልድ ለተምሳሌት ሀገር" በመሪ ቃል የሳይንስና የፈጠራ ስራ አዉደ ርዕይ "አካሔደ።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር ትምህርት
ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ እሸቱ ኢፋ በበኩላቸዉ ዉድድሩ እጅግ በጣም አጓጊና ፋክክር እንደሚታይበት ያቀረባችሁት ስራ ይመስክራል በማለት ይህ ለእዕይታ ያቀረባችሁትየፈጠራ ስራ ተማሪዎች በሐሳብ/በትዎሪ የተማሩትን በተግባር የምታሳዩበት ትልቅ የፈጠራ ችሎታ ነዉ፤ ነገር ግን በዉድደር መካከል አሸናፊ መኖር የግድ ስለሚሆን ስራችሁን በግልጽ ና በተረጋጋ ሁኔታ ለተመልካች ፣ ለዳኞች እንድታቀርቡ በማለት ለተወዳዳሪዎች መልካም እድል እንዲሆንላቸዉ በመመኘት በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑት ተማሪዎች ና ተቋማት በቀጣይም በክፍለ ከተማ ደረጃ በሚዘጋጀው አወደ ርዕይ ላይ ስራቸዉን ይዘዉ እንደሚቀርቡ ገልጸዋል።
በዚሕም በተቋም ተወዳደሪዎች
* ሽብርቅ በተቋም
1.ኛ.ግሎሪን ት/ቤት
2ኛ. አዲስ ራዕይ ትምህርት ቤት
* በፈጠራ ዉድድር
1ኛ.አዲስ ራዕይ ት/ቤት
2ኛ.ግሎሪን ት/ቤት በቅደም ተከተል ደረጃ በመያዝ ፣የእዉቅና ሽልማት ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።


መጋቢት 15/2018 ዓ.ም

Address

Megenagna
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bole 05 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share