Bole Subcity Woreda 13 Health Office

Bole Subcity Woreda 13 Health Office ቦሌ ወረዳ 13 ጤና ጽ/ቤት የሚገኘው በወረዳ 13 በልዩ ስሙ ገርጂ አ

06/10/2020

ለተከታታይ 4 ቀናት የሚሰጠው የፖሊዮ መከላከያ ክትባት ነገ ይጀምራል!

ለተከታታይ 4 ቀናት የሚሰጠውን የልጅነት ልምሻ (የፖሊዮ) መከላከያ ክትባትን አስመልክቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ የወረዳ 13 ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ቂጣታ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የልጅነት ልምሻ መከላከያ ክትባት በሽታው በክልላችን በተከሰተባቸው አካባቢዎች ዕድሜያቸዉ ከ5 ዓመት በታች ለሆናቸዉ ህጻናት ከመስከረም 27-30/2013 ዓ.ም ለተከታታይ 4 ቀናት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

በወረዳችን ውስጥ በሚገኙ 6ቱም ቀጠናዎች ተደራሽ ለማድረግ ግብዓቶችን የማሟላት ተግባራትን ጨምሮ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁንም አስታውቀዋል፡፡

ዕድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህፃናት ቤት ለቤት በጤና ባለሙያዎች በሚሰጠው የክትባት ዘመቻ የማህፀን ጫፍ ካንሰርን ጨምሮ 10 ክትባቶችን መውሰዳቸውን የመረጋገጥ፣ ከ2.1 ሚለዮን በላይ የህፃናት የምግብ እጥረት ልየታን ለመቃኘት የሚያስችሉ ቡድኖችን የማንቀሳቀስ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተናግረዋል፡፡

በዚህ የክትባት ዘመቻ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችሉ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በተገቢው በመተግበር ህጻናትን ማስከተብ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ጎረቤት አገራት የፖሊዮ ቫይረስ መከሰቱን ተከትሎ ከመስከረም 27 ጀምሮ ለአራት ቀናት የሚቆይ አገር አቀፍ ክትባት እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

31/08/2020

Address

Imperial To Gerji Roba Dabo
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 02:30 - 23:30
Tuesday 02:03 - 23:30
Wednesday 02:30 - 23:30
Thursday 02:30 - 23:30
Friday 02:30 - 22:30

Telephone

+251116299942

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bole Subcity Woreda 13 Health Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bole Subcity Woreda 13 Health Office:

Share