Disaster Safety Inclusion &Competence Assurance Directorat

Disaster Safety Inclusion &Competence Assurance Directorat Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Disaster Safety Inclusion &Competence Assurance Directorat, Addis Ababa.

በአፋር ክልል በደረሰ የመሬት ወንቀጥቀጥ አደጋ 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤታቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ተገለጸ ።በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት...
12/10/2025

በአፋር ክልል በደረሰ የመሬት ወንቀጥቀጥ አደጋ 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤታቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ተገለጸ ።

በአፋር ክልል ሰሜናዊ ዞን በባራሕሌ ወረዳ ትናንት ምሽት በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሰውና ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል ።

የሰሜናዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ አሊ አስሓብ የመሬት መንቀጥቀጡ በዞኑ ባራሕሌ፣ ኮናባ እና ዳሎል ወረዳዎች መከሰቱን ተናግረዋል።

በአደጋው የ12 ዓመት የሆነ ታዳጊ ህይወት ሲያልፍ 6 ሠዎች ላይ ጉዳት መድረሱን የስረዱት ኃላፊው 43 ሺህ 456 የሚሆኑ ሰዎች ቤታቸው ሙሉ በሙሉ መውደሙንና ያለመጠለያ መቅረታቸውን ጠቁመዋል።

በሁለቱ ወረዳዎች መረጃ የማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው÷ ለተጎጂዎች ከክልሉ መንግስት ጋር በመተባበር አስቸኳይ ድጋፍ እንደሚደረግ አመላክተዋል።

የባራሕሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አሊ ሁሴን በበኩላቸው÷ በመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት በቡሬ እና ዓስጉቢ ቀበሌዎች በርካታ ቤቶች መፍረሳቸውን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

ለተጎጂዎች ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል።

ለእሳትና ለሌሎች ድንተ ኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነው ያሳወቁ.....

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤትና የአደጋ ፈንድ ተቋቋመ።****************ነሐሴ 09/2017የምክር ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ በአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር በቅድ...
15/08/2025

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤትና የአደጋ ፈንድ ተቋቋመ።
****************
ነሐሴ 09/2017
የምክር ቤቱ መቋቋም ዋና ዓላማ በአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር በቅድመ አደጋ፣ በአደጋ ጊዜ እና በድህረ አደጋ ወቅቶች በሚሰጡ አገልግሎቶች ዙሪያ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት፣ አሰራሩን ለማዘመን እና አገልግሎቶቹ ለከተማው አጠቃላይ ዘላቂ ልማት ቀጣይነት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ መሆኑን የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚና የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ዘመን ተስፋዬ ገልፀዋል።

ደንቡ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ምክር ቤት እና የአደጋ ጊዜ ፈንድ ማቋቋሚያ ደንብ ቁጥር191/2017" ተብሎ እንደተሰየመም አቶ ዘመን አክለው ገልፀዋል።

የተቋቋመው ኮሚቴም በአደጋ ስጋት አመራር እና በሚከሰት አደጋ የተጎዱ ሰዎች የአሰቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ ዕርዳታ፣ የመልሶ ግንባታና በዘላቂነት መልሶ ማቋቋም እንቅስቃሴዎች ላይ አተኩሮ እንዲሰራም ተገልጿል፡፡

ምክር ቤቱ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ስራ የሚገባ ሲሆን የመጠባበቂያ ፈንዱን የመሰብሰብ፣ የማስተዳደር ፣ ሥራ ላይ እንዲውል ማድረግ፣ አፈጻጸሙንም የመከታተልና የመቆጣጠር ስራ እንዲሰራም አቶ ዘመን በአቅጣጫ መልኩ አስቀምጠዋል።

05/08/2025

በነሀሴ ወር ከባድ ዝናብ ይኖራል ተባለ.......

በነሀሴ ወር በረዶ የቀላቀለና ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ።

ኢኒስቲትዩቱ እ.ኤ.አ ከኦገስት 1 እስከ 31/2025 የሚኖረውን የአየር ጠባይ ሁኔታ አስታውቋል።

በነሃሴ ወር ከሚጠናከሩት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ጋር ተያይዞ በተለይም በሰሜን ምስራቅ፣ በሰሜን፣ በመካከለኛዉ፣ በደቡብ ምዕራብና በምዕራብ የሃገሪቱ ቦታዎች ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ ተጠቁሟል።

በተጨማሪም በፀሐይ ሀይል ታግዘዉ ከሚፈጠሩ የደመና ክምችቶች በመነሳትም በረዶ የቀላቀለ እና ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ መጠን ያለዉ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል ተመላክቷል።

በሌላ በኩል በአንዳንድ ቦታዎች ከሚኖረው ተደጋጋሚ የሆነ የእርጥበት መብዛት ጋር ተያይዞ በረባዳማ አካባቢዎች የውሃ በሰብል ላይ መተኛት፣ የመሬት አቀማመጡ ከፍታ ባላቸውና ተዳፋታማ በሆኑ አካባቢዎች ደግሞ የመሬት መንሸራተትና በጎርፍ መጠቃት ሊያጋጥም እንደሚችል ተገልጿል።

እርጥበት በሚበዛባቸው አካባቢዎች የሰብል በሽታ እና የአረም መስፋፋት ሊከሰት ስለሚችል አርሶ አደሮችና የሚመለከታቸው አካላት ሰብሎች በጎርፍ እንዳይጠቁ እና በማሳ ላይ ውሃ እንዳይተኛ የጎርፍ መቀልበሻዎችንና ከማሳ ውሰጥ ውሃን ማስወገጃ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ደግሞ አልፎ አልፎ በሚኖረው ተደጋጋሚ ከባድ ዝናብ ቅጽበታዊ ጎርፍ የማስከተል እድል ይኖረዋል ተብሏል ሲል የዘገበው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።

በክረምቱ የዕረፍት ጊዜ ወላጆች ለልጆቻቸዉ በቂ ጥበቃ ሊያደርጉ ይገባል።በአዲስ አበባ ታዳጊዎችና ወጣቶ  ች በቂ የዋና ችሎታ ሳይኖራቸዉ ዋና ለመዋኘት በሚል በአቅራቢ ያቸው አልፍ ሲልም ከአካ...
04/08/2025

በክረምቱ የዕረፍት ጊዜ ወላጆች ለልጆቻቸዉ በቂ ጥበቃ ሊያደርጉ ይገባል።

በአዲስ አበባ ታዳጊዎችና ወጣቶ ች በቂ የዋና ችሎታ ሳይኖራቸዉ ዋና ለመዋኘት በሚል በአቅራቢ ያቸው አልፍ ሲልም ከአካባቢያ ቸው ርቆ ወደሚገኙ ወንዞችና ዉሀ በአቆሩ ጉድጓዶች ዉስጥ እየገቡ ህይወታቸውን ያጣሉ።

በተለይ በአሁኑ ጊዜ ትምህርት ቤቶችዝግ በመሆናቸዉ ታዳጊ ዎችና ወጣቶች ረጅም የእረፍት ጊዜ ስለሚኖራቸው ወደነ ዚህ ስፍራ ሊሄዱ የሚችሉበት ሁኔታ ሠፊ በመሆኑ ወላጆች ለልጆችቻ ቸዉ በቂ ጥበቃ ማድረግና ልጆቻቸው ማስገንዘብ እንደሚገባቸው ተገልጿል ።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎች አስቀድሞ ለመከላከል በተለያዩ አማራጮች ተከታታይ የሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶችን እያስተላለፈ በመሆኑ ህብረተሰቡ ፣በተለይም ወላጆች እንዲሁም ታዳጊዎችና ወጣቶች ከኮሚሽኑ እየተላለፉ ያሉ የጥንቃቄ መልዕክቶችን እንዲተገብሩ ኮሚሽኑ ያሳስባል።

ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!

25/07/2025

በክረምቱ አልፎ አልፎ የሚኖር ከባድ ዝናብ ሊያስከትል ከሚችለው ቅጽበታዊ ጎርፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል-የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት
****
(ሐምሌ 15/2017ዓ.ም) በመጪዎቹ አስር ቀናት አልፎ አልፎ የሚኖረው ከባድ ዝናብ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል ስለሚችል ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ።

ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በመጪዎቹ አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በበርካታ ቦታዎቻቸው ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው እርጥበት ይኖራቸዋል።

በተጨማሪም በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ እና በደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት እንደሚኖራቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
የሚጠበቀው እርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው ትንበያው ያሳያል።

ስጋቶችን ለመቀነስና የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች በላቀ ሁኔታ ለመጠቀም የቀረቡትን ቦታ ተኮር የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦች በተገቢው ሁኔታ መተግበር እንደሚያስፈልግ አመላክቷል።

በሚኖረው እርጥበት ዘር መዝራት፣ ትርፍ ውሃን ከማሳ በማጠንፈፍ ማስወገድ፣ የአፈር መሸርሸር ስጋትን ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ጠቁሟል።

ረባዳማ በሆኑ ማሳዎች የውሃ ማንጣፈፍ ስራዎች መስራትና የደረሱ የበልግ ሰብሎችን በሚኖሩ ደረቅ ቀናቶች መሰብሰብ እንዲሁም የሚገኘውን እርጥበት በመጠቀም የመኸር ዘር መዝራት እንደሚገባም አብራርቷል።

በቀጣዮቹ አስር ቀናት በሚኖረው ዝናብ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖርም መግለጫው ያመላክታል።

አልፎ አልፎ ከሚኖረው ተደጋጋሚ የሆነ ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ በተለይም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል እንደሚችል አስረድቷል።

ስለሆነም በወንዝ ዳርቻ እንዲሁም ረግረጋማ አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውና የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት አደጋን በመቀነስ መልካም እድሎችን እንዲጠቀሙም አስገንዝቧል።

የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት፣ወራጅ ውሃን በእግርም ሆነ በቀላል ተሽከርካሪ ለማቋረጥ አለመሞከር፣ የጎርፍ የፍሳሽ መውረጃ ቦዮችን ማፅዳት፣ የዝናብ ውሃ ማሰባሰብና ማጠራቀም እንደሚገባ ማመላከቱን ኢዜአ ዘግቧል።

23/07/2025

በክረምቱ አልፎ አልፎ የሚኖር ከባድ ዝናብ ሊያስከትል ከሚችለው ቅጽበታዊ ጎርፍ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አሳሰበ ።

በመጪዎቹ አስር ቀናት አልፎ አልፎ የሚኖረው ከባድ ዝናብ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል ስለሚችል ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ገለፀ።

የኢንስቲትዩቱ መግለጫ እንዳስታውቀው በመጪዎቹ አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በበርካታ ቦታዎቻቸው ላይ ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው እርጥበት ይኖራቸዋል።

በተጨማሪም በሰሜን ምስራቅ፣ በምስራቅ እና በደቡብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው እርጥበት እንደሚኖራቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።

የሚጠበቀው እርጥበት ለወቅቱ የግብርና ስራ እንቅሥቃሴ በአመዛኙ አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረው ትንበያው ያሳያል።

ስጋቶችን ለመቀነስና የሚኖሩትን መልካም አጋጣሚዎች በላቀ ሁኔታ ለመጠቀም የቀረቡትን ቦታ ተኮር የግብርና ሚቲዎሮሎጂ ምክረ ሀሳቦች በተገቢው ሁኔታ መተግበር እንደሚያስፈልግ አመላክቷል።

በሚኖረው እርጥበት ዘር መዝራት፣ ትርፍ ውሃን ከማሳ በማጠንፈፍ ማስወገድ፣ የአፈር መሸርሸር ስጋትን ለመቀነስ የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት እንደሚያስፈልግም ጠቁሟል።

ረባዳማ በሆኑ ማሳዎች የውሃ ማንጣፈፍ ስራዎች መስራትና የደረሱ የበልግ ሰብሎችን በሚኖሩ ደረቅ ቀናቶች መሰብሰብ እንዲሁም የሚገኘውን እርጥበት በመጠቀም የመኸር ዘር መዝራት እንደሚገባም አብራርቷል።

በቀጣዮቹ አስር ቀናት በሚኖረው ዝናብ በአብዛኛው ተፋሰሶች ላይ ከመጠነኛ እስከ ከፍተኛ መጠን ያለው የገፀ ምድር የውሃ ፍሰት እንደሚኖርም መግለጫው ያመላክታል።

አልፎ አልፎ ከሚኖረው ተደጋጋሚ የሆነ ከባድ ዝናብ ጋር ተያይዞ በተለይም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ተፋሰሶች ላይ ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል እንደሚችል አስረድቷል።

ስለሆነም በወንዝ ዳርቻ እንዲሁም ረግረጋማ አካባቢ የሚኖሩ ማህበረሰቦች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸውና የሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት አደጋን በመቀነስ መልካም እድሎችን እንዲጠቀሙም አስገንዝቧል።

የጎርፍ መቀልበሻ ቦዮችን ማዘጋጀት፣ወራጅ ውሃን በእግርም ሆነ በቀላል ተሽከርካሪ ለማቋረጥ አለመሞከር፣ የጎርፍ የፍሳሽ መውረጃ ቦዮችን ማፅዳት፣ የዝናብ ውሃ ማሰባሰብና ማጠራቀም እንደሚገባ ተመላክቷል ።

በ2017 በጀት ዓመት የተሰሩ የማዘጋጃ ቤታዊ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸው ተገለፀ።*******************ሰኔ 16/2017የቂርቆስ ክፍለ  ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት እና የተጠሪ ተቋማት...
25/06/2025

በ2017 በጀት ዓመት የተሰሩ የማዘጋጃ ቤታዊ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸው ተገለፀ።
*******************
ሰኔ 16/2017
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት እና የተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት ማጠቃለይ እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከወረዳ ስራ አሴኪያጆች፣ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት እና ፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ሀላፊዎች፣ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎች፣የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር፣የኤለክትሪክ፣ውሃና ፍሳሽ ሀላፊዎችና ተወካዬች፣ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የተለያዩ የህዝብ አደረጃጀት አባላት ጋር ገመገሙ።

ከተግባራት አፈፃፀም ባሻገር በቅንጅታዊ አሰራር የመጡ ውጤቶችም በግምገማው ትኩረት የተደረገባቸው እንደነበሩም ተገልጿል።

በግምገማውም ፅ/ቤቱ ለተጠሪ ተቋማት ያደረገው የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ፣የአቅም ግንባታ ስራዎች፣ በቅንጅታዊ አሰራር ስረአት የተለያዩ የመብራት፣የውሃ፣የፅዳት እና የሲቪል ምዝገባ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች በመፍታት የህብረተሰቡን እርካታ ማሳደግ መቻሉ፣ በፅዳት ስራ ሞዴል ወረዳ፣ብሎክና ተቋማትን በመፍጠር ፅዱና ለኑሮ ምቹ ክፍለ ከተማ መፈጠሩ፤ በዓመቱ ትልልቅ ሀይማኖታዊና መንግስታዊ ኩነቶችንና በዓላትን በስኬታማ የሆኑ የንቅናቄ ስራዎች መሠራታቸው፤ የነዋሪነት አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የታገዙ እንዲሆኑ ስራዎች መሠራታቸውና ተጠያቂነትን በማስፈን ብልሹ አሰራርን በመቀነስ የህብረተሰቡን እርካታ ማሻሻል መቻሉ፣የተቋም ሪፎርም ስራዎችን በክፍለ ከተማና ወረዳ ተቋማት በመስራት አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ማድረጉ እንዲሁም የኮሪደር ልማት ስራዎች አበረታች ውጤት የተመዘገበባቸው በመሆኑ በጀት ዓመትም ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተመላክቷል።

በተጨማሪም ከመብራትና ውሃ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ መቆራረጦችን በቅንጅት ለመፍታት የተሄደው ርቀት እጅግ አበረታች እንደነበር መድረኩን የመሩት የስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ኃላፊዋ ወይዘሮ ዘይዳ ነስረዲን ገልፀዋል።

የግምገማ መድረኩ ከወይዘሮ ዘይዳ በተጨማሪ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ በወይዘሪት ፍቅርተ ተወልደ እና የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ቂርቆስ ቅ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ አደፍርስ የተመራ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ ውጤታማ ስራዎች በቀጣይ በጀት ዓመት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

25/06/2025

ከአደጋዉ ስድስት ሰዎችን መታደግ ተችሏል።

ትላንት ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 9:05 ሰዓት ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 6 ሳሪስ በአንድ ፔንሲዎን
በተነሳ የእሳት አደጋ ሁለት ሰዎች በጪስ ታፍነዉ ህይወታቸዉ አልፏል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች
በአደረጉት ርብርብ
በፔንሲዮን በክፍል ዉስጥ ተኝተዉ የነበሩ ስድስት ሰዎችን መታደግ የቻሉ ሲሆን የእሳት አደጋዉ ሳይስፋፋ በፍጥነት መቆጣጠርም ችለዋል።

በጪስ ታፍነዉ በአንድ ክፍል ዉስጥ ህይወታቸን ያጡት የ30 ዓመት ወንድና የ25 ሴት ናቸዉ።

ፔኔሲዮኑ የዉስጥ ክፍሉ እሳትን መቋቋም ከማይቹሉና አደጋን አባባሽ ከሆኑ በቺፑድ እና በጣዉላ የተከፋፈሉ መሆናቸዉ እሳቱ እንዲባባስና ጪስ እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል።

ፔንሲዮኖችና የሆቴል አገልግሎት
የሚሰጡ ድርጅቶች ወይም ባለንብረቶች እንግዶች የሚያርፉባቸዉን ክፍሎች የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ያሟሉና የተጠበቁ በማድረግ የደንበኞቻቸዉ ደህንነት በመጠበቅ አስፈላጊዉን ጥንቃቄ ማድረግ የሚገባቸዉ ሲሆን ኮሚሽኑ የአደጋ ደህንንነት መስፈርትን በማያሟሉ አገልግሎት መስጫዎች ላይ አስፈላጊዉን ዕርምጃ እንደሚወስድ ያሳስባል።

ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!

በወረዳዉ አስተዳደር በእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዙሪያ እንዲሁም ከኤሌክትሪክ ጋር ተያይዞ የ4ኛ ሩብ አመት እና የ12ወራት ቅንጅታዊ አሰራር ስራዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተገመገመ =...
23/06/2025

በወረዳዉ አስተዳደር በእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዙሪያ እንዲሁም ከኤሌክትሪክ ጋር ተያይዞ የ4ኛ ሩብ አመት እና የ12ወራት ቅንጅታዊ አሰራር ስራዎች ከባለድርሻ አካላት ጋር ተገመገመ
=============================
ሰኔ 12/2017 ዓ.ም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር
በዋና ስራ አስፈፃሚ ዋና ሰብሳቢነት በስራ አስኪያጅ ምክትል ሰብሳቢነት የሚመራው በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር እና አወጋገድ ፣በሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል፣በእሳትና ድንገተኛ አደጋ መከላከል ዙሪያ እንዲሁም ከኤሌክትሪክ ጋር ተያይዞ የ4ኛ ሩብ አመት እና የ12ወራት ቅንጅታዊ አሰራር በመገምገም ፤ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እንጠያየቅ መድረክ አካሄደ።

በመጨረሻም በቅንጅታዊ አሰራር የተሻለ አፈጻጸም ለነበራቸው ባለድርሻ አካላት የእዉቅናና ሽልማት በማበርከት መድረኩ ተጠናቋል

ሰኔ 15/2017ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ማዕከልና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ለተወጣጡ አመራሮች...
23/06/2025

ሰኔ 15/2017ዓ.ም፡- የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ማዕከልና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ለተወጣጡ አመራሮችና ባለሙያዎች በአደጋ ስጋት ቅነሳ ላይ ያተኮረ ውይይትና ሥልጠና ለሁለት ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ ሲካሄድ የነበረው ዛሬ ተጠናቀቀ፡፡

በውይይቱ ከቀረቡት ሰነዶች መካከል የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ፖሊሲ ምንነትና አስፈላጊነት፣ ሰብዓዊ ድጋፍ ሉዓላዊነት በኢትዮጵያ ዕሳቤዎች፣ ማስፈንጠሪያዎችና መለኪያዎች፣ የቤተሰብ ኃላፊነትና የማህበረሰብ አጋርነት፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓት ሮድ ማፕ፣ የአደጋ ስጋት ፕሮፋይል ጥናትና ውጤቶች እና የአደጋ ስጋት ዕቅድ ማካተት ዙሪያ ሰፋፊ ርዕሰ ጉዳዮች በጥልቀት በኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አመራሮች ከዩኒቨርሲቲ በተጋበዙ ምሁራን አማካኝነት ተሰጥተዋል፡፡

ከቀረቡት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች መካከል፤ የሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ለማሳካት ተግዳሮቶቹ ምን እንደሆኑ እና ምን መፍትሔ እንደሚያስፈልጋቸው፣ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ፖሊሲን በአዲስ አበባ በሚሰሩ ቢሮዎች የአደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራን በልማት ዕቅዶቻቸው እንዲያካትቱ ምን እየተደረገ እንደሆነ፣ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን ውጤታማ ለማድረግ እንዲቻል መሰራት ያለበት ወሳኝ ነገሮች እና እንዴት የተሻለ የቤተሰብ ሀላፊነትንና የማህበረሰብ አጋርነትን ማሳደግ እንደሚቻል በሚሉ የመወያያ ነጥቦች የቡድን ውይይት ተደርጎ የቡድኑ አቅራቢዎች ከልምዳቸው በመነሳት ተግዳሮት ይሆናሉ ያሏቸውን ነጥቦችን እስከ መፍትሄዎቻቸው ያቀረቡት ሲሆን ለወደፊት የአደጋ ስጋት ቅነሳ ተግባርና ለአደጋ የማይበገር ማህበረሰብና ሀገር ለመፍጠር በሚደረገው ርብርብ ትልቅ ግብኣት እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

በመረሀግብሩ ማጠቃለያ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ኮማንደር አህመድ መሀመድ ፖሊሲውን ከማስፈፀምና ከመፈፀም አንፃር፣ ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ በመሥጠትና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራን በስልጠናው ባገኘነው ጥልቅ ዕውቀትና የልምድ ተሞክሮ በመነሳት በቁርጠኝነት፣ በቅንጅት እና በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ውጤታማ ስራ ልንሰራ ይገባል የሚል አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን፣ አመራሮችንና ስልጠናውን የሰጡትን አካላት አመስግነው ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው ቅንጅታዊ ስራ ከመሥራት አኳያ ከአዲስ አበባ እሳትና የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሥራት እንደሀገር የአደጋ ስጋት ቅነሳ ስራን ማሳካት እንደሚቻል ያላቸውን ቁርጠኝነት ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ሜኒስትሪሚንግ መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ነጋ ጋረደው በመድረኩ እንደተናገሩት ከሌሎች ክልሎች ጋር በቅንጅት እንደምንሰራው ሁሉ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋርም በአቅም ግንባታ፣ ልምድ ልውውጥ፣ ውጤታማ የአደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራ በቅንጅት ለመሥራት ትብብራችንና ድጋፋችን ይቀጥላል ብለዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ስጋት ቅነሳ ሥራንና ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ምላሽ መስጠት እንዲቻል በዕውቀትና በክህሎት የዳበረ አመራርና ባለሙያ ለማፍራት የሚረዳ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና የመድረክ ውይይቶች እንዲደረጉ በማመቻቸቱ ምስጋናቸውን ገልፀው ባገኙት እውቀት፣ ልምድምና ተሞክሮ ወደ ውጤታማ ተግባር እንደሚቀይሩም ቁርጠኝነታቸውን ገልፀዋል።

ስለምትከታተሉን ምስጋናችን ከልብ ነው።

ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ በተለዩ ቦታዎች አደጋውን ለመከላከል የሚያስችሉ የማቅለያ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ...
27/05/2025

ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ በተለዩ ቦታዎች አደጋውን ለመከላከል የሚያስችሉ የማቅለያ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ አስታወቁ።

በአዲስ አበባ ከተማ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ተብለዉ በተለዩ ቦታዎች እየተከናወኑ ያሉ የማቅለያና የመፍትሄ እርምጃዎች የደረሱበትን ደረጃ ለመገምገም በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ የተመራ በቅንጅት የጎርፍ መከላከልን ስራ እያከናወኑ ያሉ የከተማ አስተዳደር የሴክተር ተቋማትና የተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የክፍለከተሞች አመራሮች በተገኙበት ዛሬ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም የመስክ ምልከታ ተካሂዷል።

በመስክ ምልከታው ማጠቃለያ ላይ ኢንጂነር ወንድሙ ሴታ እንደተናገሩት ለአደጋ ተጋላጭ ተብለዉ በተለዩ ቦታዎች እየተወሰዱ ያሉ የማቅለያና መፍትሄ የመስጠት ስራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑን ጠቅሰዉ ያልተጠናቀቁ ቀሪ ስራዎች የክረምቱ ጊዜ ሙሉ በሙሉ ከመግባቱ በፊት ባሉት ጥቂት ጊዚያት አስቀድሞ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

አያይዘዉም በተለይም ኑሯቸዉን በወንዝ ዳርቻ ያደረጉና ለአደጋ ተጋላጭ የነበሩ ነዋሪዎችን ከአደጋ ወደተጠበቀና ምቹ ወደሆነ አካባቢ መዘዋራቸዉንና ቦታዉም በወንዝ ዳርቻ ልማት ታቅፎ እየለማ መሆኑን ጠቅሰዉ ለጎርፍ አደጋ ምክንያት የሚሆኑ የፍሳሽ መስመሮችን በተለያዩ ባዕድ ነገሮች ባለመዝጋትና ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን ለመቀነስ በሚደረገዉ ጥረት ህብረተሰቡ እንደ ከዚህ ቀደሙ ተባባሪ በመሆን የመፍትሄዉ አካል እንዲሆንም አሳስበዋል።

በመስክ ምልከታዉ በአቃቂ ፣ በነፋስ ስልክ፣ በአዲስ ከተማ፣ ቂርቆስ እና በአራዳ ክፍለ-ከተሞች ባሉ እየተከናወኑ ያሉ የጎርፍ መከላከልና የማቅለያ ስራዎች የተጎበኙ ሲሆን በጉብኝቱም የሴክተር ተቋማት፣ የክፍለ-ከተሞች ዋና ስራ አሰፈጻሚዎችና ስራ አስኪያጆች ፣ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንና የአካባቢ ጥበቃ እንዲሁም የጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Disaster Safety Inclusion &Competence Assurance Directorat posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share