Lideta woreda 5 communication office

Lideta woreda 5 communication office ይህ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ኮሙዩኒኬሽን ፅ/ቤት ትክክለኛ

"ሞዴል ብሎክ ለልደታ ከፍታ""ከተሜነት በመደመር መንግስት ዕይታ " በሚል መሪ ቃል የልደታ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት መልሶ ያደራጃቸውን 307...
27/08/2026

"ሞዴል ብሎክ ለልደታ ከፍታ"
"ከተሜነት በመደመር መንግስት ዕይታ " በሚል መሪ ቃል የልደታ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት መልሶ ያደራጃቸውን 307 ብሎክ ካውንስል አባላት የማስተዋወቂያና የውይይት መድረክ አካሂዷል።

መድረኩ የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚና የካውንስሉ ሰብሳቢ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን፣ የብሎክ ካውንስል አባላት በክፍለ ከተማዋ የልማት፣ የአገልግሎት፣ የማህበራዊ ጉዳዮችና የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራዎች ውስጥ ያላቸውን ሚና በተሻለ ሁኔታ እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ ነው።

በመድረኩ “ከተሜነት በመደመር መንግስት ዕይታ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን የከተማ ነዋሪዎች ከመንግስት ጋር በመቀናጀት የሚያደርጉት ተሳትፎ ለከተማ ልማትና ለአካባቢ ምቹነት ያለው ሚና ተነስቷል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ በመድረኩ እንደገለፁት፣ የተሻለችና ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ ለመገንባት የመንግስት ሥራ ብቻ በቂ አይደለም። ንቁ የዜጎች ተሳትፎ፣ የጋራ ኃላፊነትና የመተባበር ባህል መጎልበት እንዳለበት ገልጸዋል።

ከተሜነት ማለት በከተማ መኖር ብቻ ሳይሆን፣ ለከተማው ዕድገት የራስን ድርሻ መወጣትና የጋራ ንብረትን እንደራስ ንብረት መጠበቅ መሆኑንም ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ አስገንዝበዋል።

ከተማን የሚያምርና ለነዋሪዎች ምቹ የሚያደርጉት መሰረተ ልማቶች የመንግስት ኃላፊነት ብቻ እንዳልሆኑ ወ/ሮ ልዕልቲ ጠቁመው፣ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንፅህና መጠበቅ፣ የከተማ ውበትን ማስጠበቅ፣ ህግና ደንብን ማክበር፣ የጋራ ንብረትን መጠበቅና በበጎ ፈቃድ ተግባራት መሳተፍ የዘመናዊ ከተሜነት መገለጫዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።

በተለይም የብሎክ ካውንስል አባላት ከነዋሪዎች ጋር በቀጥታ የሚሰሩ በመሆናቸው፣ በመንግስትና በህብረተሰቡ መካከል የጠነከረ የሥራ ትስስር ለመፍጠር አስተዋፆቸው ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል።

የብሎክ ካውንስል አባላት የነዋሪዎችን ጥያቄና ችግር በቅርበት በመለየት፣ ችግሮችን ወደሚመለከታቸው አካላት በማቅረብ፣ የልማት ተሳትፎን በማስፋትና የበጎ ፈቃድ ባህልን በማጠናከር የነዋሪዎች የጋራ ተሳትፎ እንዲጎለብት ማድረግ እንደሚገባቸው ወ/ሮ ልዕልቲ አስገንዝበዋል።

የ307 ብሎክ ካውንስል አባላት መልሰው መደራጀታቸውም በየአካባቢው የሚነሱ የነዋሪዎችን ጥያቄዎች በቅርበት ለመመልከት፣ በልማትና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የህዝብን ተሳትፎ ለማሳደግና የብሎክ ደረጃ የተሳትፎ ሥርዓትን ለማጠናከር ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ምክትል ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ፀሐይ ኪባሞ በበኩላቸው፣ በየብሎካቸው የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ለጋራ ልማትና ለከተማ ውበት መጠበቅ የሚደረገውን ተሳትፎ የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

ወ/ሮ ፀሐይ አክለውም፣ የብሎክ ካውንስሎችን አቅም በማጎልበትና ከነዋሪዎች ጋር ያላቸውን ቅርበት በማጠናከር በክፍለ ከተማዋ የተሳትፎ ባህልን ማሳደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የልደታ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍራንኦል በበኩላቸው፣ “ሞዴል ብሎክ ለልደታ ከፍታ” የሚለውን ዓላማ በተግባር ለማሳካት በእያንዳንዱ ብሎክ የሚገኙ ነዋሪዎች፣ የብሎክ ካውንስል አባላትና የመንግስት አካላት በቅንጅት መስራት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ ፍራንኦል እንዳሉት፣ ሞዴል ብሎክ ማለት በአካባቢው የንፅህና፣ የከተማ ውበት፣ የአረንጓዴ ልማት፣ የማህበራዊ ትስስርና የዜጎች ተሳት

በልደታ ክ/ከተማ ወርሃ ክረምቱን  ምክንያት በማድረግ "ደረቅ ቆሻሻ የሀብት ምንጭ እንጂ ለጎርፍ አደጋ ስጋት ሊሆን አይገባም!" በሚል መሪ ቃል የፅዳት ዘመቻ ተከናወነበልደታ ክ/ከተማ የአደረ...
15/08/2026

በልደታ ክ/ከተማ ወርሃ ክረምቱን ምክንያት በማድረግ "ደረቅ ቆሻሻ የሀብት ምንጭ እንጂ ለጎርፍ አደጋ ስጋት ሊሆን አይገባም!" በሚል መሪ ቃል የፅዳት ዘመቻ ተከናወነ

በልደታ ክ/ከተማ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደረጀ ትሪቦ እንደተናገሩት የፅዳት ንቅናቄ መርሀግብሩ አዲስ አበባን እንደ ስሟ ፅዱ፣ ውብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች ከተማ ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።

የክ/ከተማዋ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያየህ በበኩላቸው የፅዳት ዘመቻው በየሳምንቱ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው ውብ ፅዱና አረንጓዴ ከተማን ለመፍጠር እየሰራን ነው በማለት ገልፀዋል።

በፅዳት ንቅናቄው ላይም አመራሮችን ጨምሮ የፅዳት አምባሳደሮች፣ አርቲስቶች፣ የፀጥታ አካላት፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እና ነዋሪው ህብረተሰብ ተሳትፏል።

 የቀድሞ የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ የነበሩት ወ/ሮ አበባ እሸቴ   የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋሙ አማካሪ የነበሩት እና በምክትል ስራ አስኪ...
13/08/2026



የቀድሞ የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ የነበሩት ወ/ሮ አበባ እሸቴ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን የተቋሙ አማካሪ የነበሩት እና በምክትል ስራ አስኪያጅነት ተቋሙን የመሩት ወ/ሮ አበባ እሸቴ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።

ወ/ሮ አበባ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው እለት ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም ህይወታቸው በማለፉ ተቋሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለመላው ቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናቱን ይመኛል::

 የክረምት በጎ ፍቃድ ቤት ዕድሳት መርሀ ግብር ተጠናክሮ ቀጥሏል።ነሀሴ 05-2018 ዓ.ም | ልደታ ወረዳ 05 ኮሚኒኬሽንበልደታ  ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር የ90 ቀን የክረምት በጎ ...
11/08/2026



የክረምት በጎ ፍቃድ ቤት ዕድሳት መርሀ ግብር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ነሀሴ 05-2018 ዓ.ም | ልደታ ወረዳ 05 ኮሚኒኬሽን

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር የ90 ቀን የክረምት በጎ ፈቃድ የቤት እድሳት ፕሮግራም በዛሬው ዕለት 2 የአቅመ ደካሞችን ቤት ዕድሳት ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በመርሀ ግብሩ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ በለጠ መኮንን ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ፈዬራ እንዲሁም የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴዎች አመራሮች እንዲሁም በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ተገኝተዋል።

የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ በለጠ መኮንን ባስተላለፉት መልዕክት “በጎነት መልሶ የሚከፍል ታላቅ በጎ እሴት ነው” ያሉ ሲሆን፣ ዛሬ የተጀመረውን የቤት ግንባታና ዕድሳት በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለተጠቃሚዎቹ ለማስረከብ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ተደጋጋፊነት የሚያጎለብትና የአቅመ ደካሞችን እንግልት የሚቀንስ በመሆኑ፣ በወረዳው የሚካሄዱ መሰል በጎ አድራጎቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል።

"ኦሮሞ የታገለው ኢትዮጵያን ወይንም ኢትዮጵያ ላይ አልነበረም፤ ትግሉ የተበላሸ የአስተዳደር ስርአትን መታገል ነበር"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
08/08/2026

"ኦሮሞ የታገለው ኢትዮጵያን ወይንም ኢትዮጵያ ላይ አልነበረም፤ ትግሉ የተበላሸ የአስተዳደር ስርአትን መታገል ነበር"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

"የኦሮሞ ሕዝብ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ አድርጎ በመፍጠርና በመገንባት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና አለው" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
08/08/2026

"የኦሮሞ ሕዝብ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ አድርጎ በመፍጠርና በመገንባት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና አለው"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት...
06/08/2026

መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ ነው ፡፡

በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።

እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።

በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡

በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።

በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።

በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤

በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።

በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።

በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።

መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

06/08/2026
በልደታ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ስር የቋቋመዉ ይህ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መ...
06/08/2026

በልደታ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ

በልደታ ክፍለ ከተማ ጤና ጽ/ቤት ስር የቋቋመዉ ይህ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል በዛሬው ዕለት በልደታ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ በአቶ ዘመኑ ደሳለኝ ተመርቆ በይፋ ስራ ጀምሯል።

ማዕከሉ የተቋቋመበት ዋና ዓላማ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚከሰቱ ልዩ ልዩ የጤና ጠንቆችና ድገተኛ አደጋዎችን አስቀድሞ ለመከላከል፣ ለመከታተልና አደጋዎች ሲከሰቱም በተደራጀ፣ በተቀናጀና ፈጣን በሆነ መልኩ ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ተገልጿል፡፡

ማዕከሉ በክፍለ ከተማው የሚሰጠውን የህብረተሰብ ጤና ጥበቃ ስራ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ከመሆኑም በላይ ህብረተሰቡን ከጤና ስጋቶች የመጠበቅ አቅምን በእጅጉ ያጎለብታል ተብሏል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lideta woreda 5 communication office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share