Yeshambel Alamirw

አገው ኢትዮጵያን ከሰፈሩ ቀደምት ህዝቦች አንዱ ነው። ይህ ህዝብ ለ270 ዓመታት ኢትዮጵያን እና የዛሬዋን ኤርትራ ያስተዳደረው የዛጉዌ ሥርወ መንግስት ነው!
የአገው ሕዝብ አሁን በሚኖርባቸው በኤርትራ ፡በትግራይ፡በጎንደር፡በጎዣም፡በላስታ አካባቢዎች ራሱን የሚገልጸው በተለያየ መገለጫ ቢሆንም በስፋት የሚታወቁት አዊ ፡ኽምራ፡ቅማንት ፡ብሊን በሚሉ አካባቢያዊ መጠሪያዎች ነው።

23/05/2026
12/05/2026

ሠላም ለኢትዮጵያ ጥምረት፡ “ጽንፈኝነትና የኃይል እርምጃ ለዘላቂ ሰላም እንቅፋት ናቸው” አለ
ዛጉዌ ሚዲያ -Zagwie Media ግንቦት2018
================
በሀገሪቱ እየተስፋፉ ያሉ ጽንፈኛ አመለካከቶችና በመሣሪያ ኃይል የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት ከባድ እንቅፋት እየሆኑ መጥተዋል ሲል ገለጸ።

ጥምረቱ ባወጣው መግለጫ፣ ኢትዮጵያ የታሪክ፣ የባህልና የብዝኃነት ሀገር እንደመሆኗ መጠን ይህንን እሴት ጠብቆ ለማቆየት ሰላም መሠረታዊ ፍላጎት መሆኑን ጠቅሶ፣ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚታዩ ግጭቶች የዜጎችን ሕይወት ከመቅጠፍ ባለፈ የሀገርን ህልውና አደጋ ላይ እየጣሉ መሆናቸውን አሳስቧል።

በተለይም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በአዮ ጓጉሳ ወረዳ አዘና ከተማ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እንደሚያወግዝ ገልጾ፣ በድርጊቱ ውስጥ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተሳትፎ ያደረጉ አካላት ለሕግ እንዲቀርቡ ጠይቋል።

ጥምረቱ በመግለጫው የኃይል አማራጭ ዘላቂ መፍትሔ ሊሆን እንደማይችል በማስገንዘብ፣ ችግሮች በውይይትና በመግባባት መፍታት እንዳለባቸው ገልጿል። “ጥይት የማይመልሳቸውን ጥያቄዎች በውይይት መፍታት የሰለጠነ ማኅበረሰብ መገለጫ ነው” ሲልም አስታውቋል።

በተጨማሪም በብሔርና በሃይማኖት ስም የሚነሱ ጽንፈኛ አመለካከቶች የጋራ አገራዊ እሴቶችን እንደሚያፈርሱ ጠቅሶ፣ ሁሉም ወገኖች ከእንዲህ ዓይነት አጥፊ አስተሳሰቦች እንዲርቁ ጥሪ አቅርቧል።

በመጨረሻም በጥቃቱ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች ሐዘኑን የገለጸው ጥምረቱ፣ የቆሰሉት ፈጣን ማገገም እንዲያገኙ ተመኝቶ፣ ሁሉም ወገኖች መሣሪያ አውርደው ለሰላም እድል እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።

የጥምረቱ ም/ፕረዚዳንት በስልክ በዛጉዌ ሚዲያ በሰጡት መግለጫም “እኛ የሰላም ዘማሪዎች ነን፤ ዜማችንም እርቅ፣ ይቅርታና አብሮነት ነው” ሲል የገለጸው ጥምረቱ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረትና ሠላሟ ጸንቶ ለዘላለም እንድትኖር ምኞቱን ገልጿል።

12/05/2026

ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ፦
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ፓርቲያችን በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አዘና ከተማ በቀን 04/09/2018 ዓ.ም ከማለዳው 12:00 ጀምሮ በታጠቁ ኃይሎች በተከፈተ ተኩስ በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ጉዳት በጥልቅ ሐዘን ተመልክቶታል። በዚህ ጥቃት የአዘና ከተማ ቀበሌ አስተዳዳሪን ጨምሮ ንጹሐን ዜጎች ውድ ሕይወታቸውን ማጣታቸውና የአካባቢው ሰላም መታወኩ ፓርቲያችንን እጅግ አሳዝኖታል። ይህ ጥቃት በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመ ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት በመሆኑ ጥምረታችን በጥብቅ ያወግዘዋል።

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እየተስፋፉ የመጡ ጽንፈኛ አመለካከቶችና በመሣሪያ ኃይል የሚካሄዱ እንቅስቃሴዎች ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና አንድነት ከባድ እንቅፋት እየሆኑ መጥተዋል። ኢትዮጵያ የታሪክ፣ የባህልና የብዝኃነት ሀገር እንደመሆኗ መጠን ይህንን ታላቅ እሴት ጠብቆ ለማቆየት ሰላም መሠረታዊና የማይታለፍ ፍላጎታችን ነው።

ጥይት የማይመልሳቸውን ጥያቄዎች በውይይትና በድርድር መፍታት የሰለጠነ ማኅበረሰብ መገለጫ እንጂ የድክመት ምልክት አይደለም። በመሆኑም በብሔርና በሃይማኖት ስም የሚነሱ ጽንፈኛ አመለካከቶች የጋራ አገራዊ እሴቶቻችንን የሚያፈርሱ በመሆናቸው፣ ታጣቂ ኃይሎች ከእንዲህ መሰል አጥፊ የኃይል እርምጃዎች ተቆጥበው ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ የትግል መንገድ ብቻ እንዲያቀርቡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በሌላ በኩል የዞኑ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ መንግሥት ከቸልተኝነት ወጥቶ የዜጎችን ደህንነትና ሰላም የማረጋገጥ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል። መንግሥት በአዘና ከተማ የተፈጸመውን ጥቃት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የረዱ አካላትን ለሕግ የማቅረብና የአካባቢውን ሰላም የመመለስ ኃላፊነት አለበት።

በአሁኑ ወቅት ፓርቲያችን ለ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕጩዎችን አቅርቦ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረገ በሚገኝበት በዚህ አካባቢ እንዲህ ዓይነት የፀጥታ መታወክ መፈጠሩ በሕዝብና በፓርቲዎች መካከል ሊኖር የሚገባውን ነፃና ፍትሐዊ የፉክክር ድባብ ክፉኛ ጎድቶታል።

ሰላም በሌለበት ሁኔታ ሕዝብ በነፃነት መምረጥም ሆነ እኛ በዲሞክራሲያዊ መንገድ መፎካከር የማንችል በመሆኑ፣ መንግሥትና የሚመለከታቸው አካላት አካባቢውን በፍጥነት ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲመልሱ በጥብቅ እንጠይቃለን።

በመጨረሻም በጥቃቱ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎችና ቤተሰቦቻቸው መጽናናትን እየተመኘን፣ የቆሰሉት ወገኖቻችንም ፈጣን ማገገም እንዲያገኙ እንመኛለን።

እኛ የሰላም ዘማሪዎች ነን፤ ዜማችንም እርቅ፣ ይቅርታና አብሮነት ነው። ሁሉም ወገኖች መሣሪያ አውርደው ለሰላም እድል እንዲሰጡና ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ሠላሟ ጸንቶ እንድትኖር ጥሪያችንን እንደግማለን።

ኢትዮጵያ በሠላም ለዘላለም ትኑር!
ዶክተር አዲሱ መኮነን
የሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት ምክትል ፕሬዝደንት
ግንቦት 04 ቀን 2018 ዓ/ም
እንጅባራ፤ ኢትዮጵያ

Address

Ethiopian
Addis Ababa
100

Telephone

+251910038515

Website

https://www.youtube.com/@agewtv1

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeshambel Alamirw posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Yeshambel Alamirw:

Share