Shegger Insider

Shegger Insider Human Rights Fighter

የወል እወነት እንዲረጋገጥ የሁሉም ሰዉ አሻራ ያስፈልጋል ኢትዮጵያ የብዙ ታሪክ ባለቤት ነች ። አባቶቻችን ብዙ ታሪክ ሰርተው ይችን   ያቆዩልን በብልሃት እና  #በወል እውነት ነው ። የወል ...
14/06/2023

የወል እወነት እንዲረጋገጥ የሁሉም ሰዉ አሻራ ያስፈልጋል

ኢትዮጵያ የብዙ ታሪክ ባለቤት ነች ። አባቶቻችን ብዙ ታሪክ ሰርተው ይችን ያቆዩልን በብልሃት እና #በወል እውነት ነው ። የወል እውነት የሌለበት ሀገር ይቅርና አንድ ቤተሰብ እንኳን በሰላም መኖር አይችልም። መገፋፋት ፣ መኖቃቆር ፣ መጠላለፍ እና ፅንፈኝነት ስለሚኖር #ሀገር ልታድግ አትችልም ።

⁉️የወል እውነት ይህን ያክል ካስፈለገን እንዴት መሬት ማስያዝ ፣ እንቅፋቶቹንስ እንዴት ማሸነፍ እንችላለን ?

የወል እንውነት እንድንለማመድ የመጀመሪያው አንዱ ለአንዱ እውቅና ሲሰጥ ነው። #ኢትዮጵያ የሁላችንም ናት ፤ ሀገራችን እዚህ እስከምትደርስ ድረስ ፣ ሉዓላዊነቷ እንዲጠበቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የድርሻውን ተወቷል ።

እውነተኛ መሬት ማስያዝ ግን በቀላሉ አይመጣም። ለሀገር ይህን ያክል የሚጠቅም ነገር ሲጀመር እንዲው ሊመጣ አይችልም ለምን ከተባለው ሀገራችን ስትረጋጋ ጥቅማቸው የሚቀንስባቸው ብዙ ስላሉ ። ስለዚህ ከግራና ከቀኝ ጥላቻ የሚሰብኩንን ትተን በአንድነት ኢትዮጵያን እናልማት ።


የወል እውነት እንዴት ማምጣት ይቻላልየወል እውነትን እውን ለማድረግ ከሚያስፈልጉ ዋነኛ እርምጃዎች አንዱ እና ዋነኛው  #እውነት እኛ ጋ ብቻ አለመሆኗን መረዳት መቻል ነው።እውነት በሌላኛውም ...
14/06/2023

የወል እውነት እንዴት ማምጣት ይቻላል

የወል እውነትን እውን ለማድረግ ከሚያስፈልጉ ዋነኛ እርምጃዎች አንዱ እና ዋነኛው #እውነት እኛ ጋ ብቻ አለመሆኗን መረዳት መቻል ነው።

እውነት በሌላኛውም አቅጣጫ ያለች መሆኑን መረዳት ለጋራ ወይም ለወል እውነት በር ይከፍታል ትልቁን እውነታም እንድንረዳ ይረዳናል።

እውን ለማድረግ ከሁሉም ወገን ያሉ ትናንሽ እውነታዎችን በመረዳት ትልቁን እውነት በመረዳት የጋራ የሆነ እውነታን በመያዝ እና በማጠናከር እሱንም በማጎልበት #በጋራ ችግሮችን መፍታት ይቻላል።

ይሔን ሊያስፈፅሙ ከሚችሉ መንገዶች አንዱ ብሄራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ነው። ሁሉም ማህበረሰብ በጋራ ለጋራ ሀገር ያለውን እውነታ እና አስተዋፆ በማድረግ እና የሌላውን በመስማት ትልቁን እውነት በማጉላት ሀገርን ማፅናት ይቻላላ።


የጋራ ሀገር ፤ የወል እዉነት እኛ  #ኢትዮጵያዊያን ከታላልቅ ሀገራት ቀድመን የነበር፤ አሁንም ያለን፤  ወደፊትም የምንኖር  #ህዝቦች ነን። ይህ የሆነዉ ደሞ ከምንም በላይ የሚያስተሳስረን  ...
14/06/2023

የጋራ ሀገር ፤ የወል እዉነት

እኛ #ኢትዮጵያዊያን ከታላልቅ ሀገራት ቀድመን የነበር፤ አሁንም ያለን፤ ወደፊትም የምንኖር #ህዝቦች ነን። ይህ የሆነዉ ደሞ ከምንም በላይ የሚያስተሳስረን ስላለን ነዉ።

የወል እዉነታችን መሰረት ደሞ

☑️ አንድነት
☑️ ፍቅር
☑️ መከባበር
☑️ ወንድማማችነት ናቸዉ።

በዚህ ሰዓት እንደ #ሀገር ብዙ ፈተናዎች ዉስጥ እያለፍን ያለን ወደፊትም ብዙ ፈተናዎች የሚገጥሙን ቢሆንም ያለን #የጋራ እዉነት በማስጠበቅ በታሪካችን ላይ አባቶቻችን በደማቅ ታሪካቸዉ ፅፈዉ እንዳለፉት እኛም እናልፋለን።

ምክኒያቱም ደሞ እኛ #ኢትዮጵያዊያን ከሚለየን የተናጠል እዉነት የሚያጋምደን ስላለን ነዉ።

14/06/2023

የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ሀገር በቀል እሳቤ ከመሆን ባለፈ ባለቤቱና ተጠቃሚው ህዝቡና ህዝቡ ብቻ በመሆኑ በዚህም በመርሃ ግብሩ በመታገዝ በርካታ የስራ ዕድል መፍጠር የተቻለ ሲሆን በተለይ ወጣቶችና ሴቶች ችግኝ በማፍላትና በመንከባከብ በስፋት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡

ከዚህ ባለፈ መርሃ ግብሩ የተሻሻለ የግብርና አሰራር በማስፈን፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ የውሃ ሃብትንና የብዝሃ ህይወት ጥበቃን በማረጋገጥ ዘላቂ ተጠቃሚነትን እንደሚያስገኝና፣ በተጨማሪም አለም አቀፍ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የራሱን አስተዋጽኦ በማበርከት የግሪን ሀውስ ጋዝን ለመቀነስ እንደሚረዳ ተረጋግጧል፡፡ ሀገር አቀፉ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከተሞችን ከማስዋብ ባለፈ በዙሪያቸው የሚገኙና የተበከሉ ወንዞችን ደህንነት በማስጠበቅ የአረንጓዴ ውበት ማስጠበቂያ ቦታዎችን በዋና ዋና ከተሞች ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል፡፡

ከሁሉም በላይ የተጀመረው መርሃ ግብር የጎረቤት ሀገራትን ትኩረት በመሳብ ለጋራ ተጠቃሚነት በጋራ እንዲሰሩ ከማነሳሳት ባለፈ በቀጠናው በግጦሽ መሬት፣ በውሃና በደን ሃብት እጥረት የሚፈጠረውን ግጭት በማስወገድ ስደትንና ከመኖሪያ ቀዬ መፈናቀልን ለማስቀረት ያስችላል፡፡

በየአካባቢው የሚኖሩ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ከሀገራዊው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ማግኘት የቻሉ ሲሆን በዕድሉ በመጠቀም ችግኝ በማፍላትና በማቅረብ፣ ጉድጓድ በማዘጋጀትና ችግኞችን በመንከባከብ የራሳቸውን ገቢ አግኝተዋል፡፡ በግላቸው ችግኝ የሚያፈሉ ወጣቶች በተጀመረው መርሃ ግብር በመነቃቃት አመቱን ሙሉ የዛፍ፣ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞችን ለግለሰቦችና ድርጅቶች በመሸጥ ገቢያቸውን ከፍ አድርገዋል፡፡ በመሆኑም ይህ ለሀገራችን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታና ፉይዳ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እንረባረብ!

13/06/2023
የጋራ ሀገር የጋራ እውነት የጋራችን ለሆነችው  #ሀገራችን የተናጥል እውነቶችን ይዝን መሻገር አንችልም ለዚህች አንድ  #ሀገራችን ሁላችንም የየግል እውነታ ኖሮን ስንናቆር እስከዛሬ ከርምናል ...
13/06/2023

የጋራ ሀገር የጋራ እውነት

የጋራችን ለሆነችው #ሀገራችን የተናጥል እውነቶችን ይዝን መሻገር አንችልም ለዚህች አንድ #ሀገራችን ሁላችንም የየግል እውነታ ኖሮን ስንናቆር እስከዛሬ ከርምናል አሁን ግን ይህን በቃ ብለን የጋራ እውነትን ፈጥረን በጋራ ልንቆም ይገባል።

አማራው፣ ትግሬው፣ ወላይታው፣ ሱማሌው፣ ኦሮሞው ሁሉም የብቻ የተናጠል ጉዞ የሚያደርጉ ከሆነ #ሀገርም ህዝብም ተጎጂ ናቸዉ።

በጋራ እውነታ ላይ የተመሰረተች ሀገር ለውጪ ጣልቃ ገብነት እንኳን የማትመች ጠንካራ ሀገር ናት!!

ተያይዘን ወደፊት

ስለዚህ እኛም የተናጠል ሩጫችንን ትተን #በወል እንጓዝ።

የወል እውነት በጋራ እውነታ ላይ የተመሰረተ እውነታ ነው። ይሄ ማለት  #ግለኝነት እና  #የመንደርተኝነት ስሜት የማይንፀባረቅበት  #በወንድማማችነት እና   ላይ የተመሰረተ የጋራ እውነታ ነው...
13/06/2023

የወል እውነት በጋራ እውነታ ላይ የተመሰረተ እውነታ ነው። ይሄ ማለት #ግለኝነት እና #የመንደርተኝነት ስሜት የማይንፀባረቅበት #በወንድማማችነት እና ላይ የተመሰረተ የጋራ እውነታ ነው!

በጋራ እውነታ ላይ የተመሰረተች ሀገር ለውጪ ጣልቃ ገብነት እንኳን የማትመች ጠንካራ ሀገር ናት!!

ተያይዘን ወደፊት

ለጋራ ሀገር የወል እውነት የጋራችን ለሆነችው ሀገራችን የተናጥል እውነቶችን ይዝን መሻገር አንችልም ለዚህች አንድ ሀገራችን ሁላችንም የየግል እውነታ ኖሮን ስንናቆር እስከዛሬ ከርምናል አሁን ...
13/06/2023

ለጋራ ሀገር የወል እውነት

የጋራችን ለሆነችው ሀገራችን የተናጥል እውነቶችን ይዝን መሻገር አንችልም ለዚህች አንድ ሀገራችን ሁላችንም የየግል እውነታ ኖሮን ስንናቆር እስከዛሬ ከርምናል አሁን ግን ይህን በቃ ብለን የጋራ እውነትን ፈጥረን በጋራ ልንቆም ይገባል።

የወል እውነት የሁሉንም እውነት ተቀብለን እንድንኖር ያደርገናል ሁሉም ጋር ያለውን እውነት እንድናውቅ ሌላው ጋርም እውነት እንዳለ እንድንረዳ በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ሌላውም እንደሚያገባው እንድንረዳ ከማድረግም አልፎ የሁሉንም ማንነት እንድንቀበል ያደርጋል


በወል እውነት ሀገር መገንባት ወይስ በውሸት ሀገርን መናድ......ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ እያገጠጠ የመጣው  #ፅንፈኝነት የኢትዮጵያ ህዝቦችን የጋራ ወይም  #የወል እውነትን እያደ...
13/06/2023

በወል እውነት ሀገር መገንባት ወይስ በውሸት ሀገርን መናድ......

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ እያገጠጠ የመጣው #ፅንፈኝነት የኢትዮጵያ ህዝቦችን የጋራ ወይም #የወል እውነትን እያደበዘዘ በተቃራኒው ደግሞ #ግለኝነትንን እና የሚል አስተሳሰብን እያገነነ መጥቷል።

ሁሉም በየቀየው ተገድቦ የራሱን እውነት ብቻ እያጮኸ የሌላውን እውነታ እየተጋፋ እና ወንድማማችነትን እየገፋ ይገኛል። እንደ ሀገር አንድ ጊዜ ቆም ብለን የምናስብበት ጊዜ ላይ ያለን ይመስለኛል። ከተደጋገፍን እና ይዘን መጓዝ ከቻልን መመስረት እንችላለን ነገር ግን እየገፋን #በመንደር ማሰብ ከጀመርን ተያይዘን እንጠፋለን! ለቀጣዩ ትውልድ የሚናስረክበው ሀገርም አይኖረንም።

በመሆኑም አንድ ጊዜ ቆም ብለን እናስብ!

በሌላኛው ሰው ጫማ"የጋራ እውነት ለመፍጠር የሌላኛውን እውነት ማድመጥ መጀመር አለብን ፤ በሌላኛው ሰው ጫማ መሆን መቻል አለብን ፤ ትላንት በነበረው ሁኔታ የሚቀጥል ምንም ነገር የለም ፈርሷል...
13/06/2023

በሌላኛው ሰው ጫማ

"የጋራ እውነት ለመፍጠር የሌላኛውን እውነት ማድመጥ መጀመር አለብን ፤ በሌላኛው ሰው ጫማ መሆን መቻል አለብን ፤ ትላንት በነበረው ሁኔታ የሚቀጥል ምንም ነገር የለም ፈርሷል ለአዲሱ እሳቤ እራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል"

እዉነት ዉሸት ይሆናል፡፡ሁሉም እዉነት እዉነት ሊሆን የሚችለዉ በሁሉም ዘንድ ተቀባይት ሲኖዉ ብቻ ነዉ፡፡ የተናጥል እዉነቶች የጋራ እዉነት መሆን አይችሉም፡፡  #በፅንፈኝነት መርህ እና ህግ መ...
13/06/2023

እዉነት ዉሸት ይሆናል፡፡

ሁሉም እዉነት እዉነት ሊሆን የሚችለዉ በሁሉም ዘንድ ተቀባይት ሲኖዉ ብቻ ነዉ፡፡ የተናጥል እዉነቶች የጋራ እዉነት መሆን አይችሉም፡፡ #በፅንፈኝነት መርህ እና ህግ መሰረት የራስ እይታ እና ፍላጎት ሁሌም ብቸኛ እዉነት ነዉ፡፡ ይህ ደግሞ በሌላዉ በኩላ ላለዉ እዉነት ቦታ የማይሰጥ ፣ ለማዳመጥ እንኳን ጊዜ የማይኖረዉ ደካማ መርህ ነዉ፡፡

♨️ኢትዮጵያ የብዙ የተናጥል አዉነቶች ባለቤት ሀገር ናት ፣ የወል እዉነቶቻችን እምብዛም አይስተዋሉም ፤ የወል የሆነ እዉነት እስካላበጀን ድረስ #በፅንፈኝነት ስካር በሰከሩ አዉርቶ አደሮች ብዙ እሴቶቻችንን እየተቀማን እንቀጥላለን፡፡

Address

Sheggar
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shegger Insider posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category

Dhugaa Saba keenyaaf Ni falmanna!

Sabni keenya dhugaa akka galaanaa kan jaarraa hedduu qaba. Sirnootaa fi namoota dhuunfaan awwaalamee hafuun hin maluuf.