03/02/2026
በክፍለ ከተማ እና በስሩ ባሉ ወረዳዎች የ6ወራት ተግባር አፈጻጸም ግምገማ እና የአመራር ምዘና ተከናወነ።
#ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፖርቲ
ጥር 26 /2018 ዓ/ም የኮ/ቀ/ክፍለ ከተማ የኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ቅ/ጽ/ት
በኮ/ቀ/ክፍለ ከተማ የብልጽግና ኢንስፔክሽን ቅ/ጽ/ቤት የግምገማ እና ምዘናው በተግባር አፈጻጸም ሒደት የነበሩ ጥንካሬዎችና ጉድለቶች የተለዩበት የተግባር ስምሪትና ስኬታማነትን መሰረት ያደረገ ለተቋም ግንባታ እሴት የሚጨምር እንደሆነ በተሳታፊዎች ተገልጿል።
ኮሚሽኑ የተሰጠውን ተልዕኮ ከመወጣት አንጻር ከክ/ከተማ እስከ ወረዳ እንዲሁም የብልጽግና ህብረት መዋቅር ድረስ ባለው የሥራ ክንውን መንፈቅ አመቱ እመርታ የተመዘገበበት እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ለሥኬቶቹ መመዝገብ ምስጢሩ ከባለድርሻ አካላትና አባላት ጋር በትብብርና በቅንጂት መሰራቱ አስቻይ ሁኔታ የፈጠረ መሆኑ በመድረኩ በስፋት ተገልጿል።
በሁሉም ወረዳ የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም መነሻ በማድረግ ከአመራር ጀምሮ እሰከ ህብረት ድረሰ የሂስና ግለሂስ እንደተደረገ ክ/ከተማው ገልጿል ።