Addis Ababa prosperity women’s league- ብልፅግና

Addis Ababa prosperity women’s league- ብልፅግና Creating democrat, vibrant and front line womens that has accepted and ready to implement programs

ራዕይ
የከተማችን ሴቶች፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተሳታፊነትን በማጎልበት እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ የብልጽግና ፓርቲን ተልእኮ በብቃት መወጣትና የመደመር መንገዳችን ቀጣይነት ማረጋገጥ
ተልዕኮ
- ህብረተሰባዊ ለውጥን ማፋጠን፣
- የወቅቱን ፓርቲያዊ ተልዕኮዎች በሚገባ ተገንዝቦ በብቃት መፈጸም፣
- የሴቶችን ሁለንተናዊ ጥቅም ለማስጠበቅ መረባረብ፣
- የሴቶችን የትግል መድረክ ሆኖ ማገልገል፣
- ሁሉንም ሴቶች በጋራ ዓላማዎች እና ጥቅሞች ዙሪያ ማንቀሳቀስ፣
ዓላማ
ከተማችንን ሴቶች በሁለንተናዊ የለውጥ እንቅስቃሴያችን ዙሪያ በንቃት በማሳተፍ ደረጃ በደረጃ ተጠቃሚ በማድረግ የህዳሴ ጉዞአችንን ማቀላጠፍ
የከተማችንን ሴቶች በመሰረታዊ ጥቅሞቻቸው በመነሳት ዙሪያ እንዲሰባሰቡና በመደመር እሳቤ ዙሪያ እነዲሰባሰቡና በቀጣይነት እነዲተጉ ማስቻል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት  አካሂዷል።​ መድረኩ ላይ የከተማው፣ የሁሉም ክፍለ ከተማና የወረዳዎች የዘርፉ አመራሮች እንዲ...
03/09/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት አካሂዷል።

​ መድረኩ ላይ የከተማው፣ የሁሉም ክፍለ ከተማና የወረዳዎች የዘርፉ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

​የአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሮ የሺ ወልዴ፤ “በጎነትና እህትማማችነት የሴቶችን ማህበራዊና ፖለቲካዊ አቅም በማጎልበት ረገድ ትልቅ መሠረት ነወ” ሲሉ ገልጸዋል።

​ፓርቲው ሴት አመራሮችን በብቃት ለማዘጋጀትና ለማብቃት በርካታ አወንታዊ ተግባራትን ማከናወኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በተግባር ያሳዩት አርአያነት ያለው የአመራር ጥበብና ቁርጠኝነት፣ ሴቶች ወደፊት እንዲመጡና ሁለንተናዊ ተሳትፎአቸው እንዲያድግ ትልቅ ብርታትና ድምቀት መሆኑን አብራርተዋል።

በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ​የቦሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትል እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ማስተዋል ፋንታሁን “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ሲረጋገጥ የመላው ህብረተሰብ እድገት ይፋጥናል” ብለዋል።

​ፓርቲው ለሴቶች እያደረገ ያለው አጠቃላይ ድጋፍና የሚሰጠው ትኩረት ከፍተኛ መሆኑን ያመላከቱት ወ/ሮ ማስተዋል፤ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ የሚያሳዩት ጠንካራና አቅጣጫ ጠቋሚ አመራር ለሌሎች ሴት አመራሮች የመንፈስ ብርታትና ታላቅ የቁርጠኝነት ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል።

​ሴቶች በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች ያላቸውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

"በጎነት ለህትማማችነትና ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት"በሚል በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ በሁሉም ወረዳዎችና ክ/ከተሞች በተለያዩ ተግባራት  እንደቀጠለ ነው።በ...
01/09/2026

"በጎነት ለህትማማችነትና ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት"
በሚል በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ በሁሉም ወረዳዎችና ክ/ከተሞች በተለያዩ ተግባራት እንደቀጠለ ነው።
በዛሬው እለትም የኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አ /አበባ ቅርንጫፍ ሴቶች ክንፍ ከአለርት ኮንፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በመተባበር ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለ1853 ለሚሆኑ ሴቶች የነፃ ምርመራ እንዲያገኙ ተደርጓል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የአ/አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ፅ/ቤት ሐላፊ ወ/ሮ የሺ ወልዴ የብልፅግና ፓርቲ ሰው ተኮርነት መገለጫ አንዱ በሆነው የበጎ ፈቃድ ተግባር በተለይም ጤናማ እናትነት ምርታማነትን ለምጨመር ካለው አበርክቶና አክሞ ማዳን ብቻ ሳይሆን አስቀድሞ በመከላከል የእናቶችን ጤንነት እውን የማድረግ ትልቅ ስራ ነው በማለት ይህ መልካም ተግባርና ቅንጅታዊ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል አለብት ብለዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።
25/08/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ።

15/08/2026
"በጎነት ለእትማማችነተት ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት"በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የኮ ልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሴቶች የደም ልገሳ መርሐ ግብር ተከሔደ።በብልፅግና ፓርቲ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍ...
12/08/2026

"በጎነት ለእትማማችነተት ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት"
በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ የኮ ልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሴቶች የደም ልገሳ መርሐ ግብር ተከሔደ።

በብልፅግና ፓርቲ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የሴቶች ክንፍ ከ11ዱም ወረዳዎች የተውጣጡ ሴቶችን በማስተባበር «ደሜን ለወገኔ!» በሚል መሪ ቃል አርአያነት ያለው የደም ልገሳ መርሃ ግብር አካሂዷል።

ደም መስጠት ሕይወትን የማዳን ታላቅ የበጎ አድራጎት ሥራ ከመሆኑም በላይ፣ ሴቶች በማህበረሰባዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ግንባር ቀደም ተሳትፎ አብሮነት መንፈስ በተግባር ያረጋገጡበት አበረታች ተግባር ሆኖ አልፏል።

ይህ በጎ አድራጎት በሴቶች መካከል ያለውን እህትማማችነትና አንድነት ከማጠናከሩ ባሻገር፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጤናና ደህንነት የጎላ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ተግባር ነው።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ አሚ ሙሄ ባደረጉት ንግግር፤ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረጉ መሰል ማህበረሰብ አቀፍ በጎ አድራጎቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴት ክንፍ ሀላፊ ወ/ሮ ምስራቅ አለምሰገድ በበኩላቸው የዛሬው የደም ልገሳ መርሃ ግብር የሴቶችን የማህበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ቁርጠኝነት የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ እህትማማችነትን ለሚያጎለብቱ ተግባራት ትልቅ ማህበራዊ ጥንካሬን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

በጎነት ለእህትማማችነት፤ ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት!​በአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ የየካ ክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ከጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከ12ቱም ወረዳዎች የተውጣጡ ሴ...
08/08/2026

በጎነት ለእህትማማችነት፤ ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት!

​በአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ የየካ ክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ከጤና ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከ12ቱም ወረዳዎች የተውጣጡ ሴቶችን በማስተባበር ያካሄደው የደም ልገሳ መርሃ ግብር የሴቶችን የማህበራዊ ኃላፊነት የመወጣት ቁርጠኝነትና የጋራ ደጋፊነት መንፈስን በግልጽ ያሳየ ተግባር ነው።

ደም መስጠት ሕይወትን የማዳን ታላቅ የበጎ አድራጎት ሥራ ከመሆኑም በላይ፣ ሴቶች በማህበረሰባዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ግንባር ቀደም ተሳትፎና ውሳኔ ሰጪነት በተግባር ያረጋገጡበት አበረታች ተግባር ሆኗል።​ይህ አርአያነት ያለው በጎ አድራጎት በሴቶች መካከል ያለውን እህትማማችነትና አንድነት ከማጠናከሩ ባሻገር፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ ጤናና ደህንነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል።

በመሆኑም የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረጉ መሰል የማህበረሰብ አቀፍ በጎ አድራጎት ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የሚያሳይ ሲሆን፣ ለቀጣይ እህትማማችነትን ለሚያጎለብቱ ተግባራትም ትልቅ ማህበራዊ ጥንካሬን ይፈጥራል።

‎ዛሬ ነሀሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ  የብልፅግና ፓርቲ ሴቶቸ  ክንፍ ከቸርቸር ጤና ጣቢያ በመጡ የጤና ባለሙያዎች ለህብረተሰብ ክፍሎችና ለበጎ ፈቃደኞች የማህፀን በር ካንሰር ምር...
07/08/2026

‎ዛሬ ነሀሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ የብልፅግና ፓርቲ ሴቶቸ ክንፍ ከቸርቸር ጤና ጣቢያ በመጡ የጤና ባለሙያዎች ለህብረተሰብ ክፍሎችና ለበጎ ፈቃደኞች የማህፀን በር ካንሰር ምርመራ ግንዛቤ የተሰጠ ሲሆን በመድረኩ የአዲስ አበባ የብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ የአደርጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ እየሩስ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎በቀጣይ ከጤና ጣቢያው ጋር በመነጋገር ምርመራውን እንደሚያረጉ የክፍለ ከተማው የሴቶች ክንፍ ወ/ሮ ፌቨን የገለፁ ሲሆን በጎ ፈቃደኞችም በየተሰማሩበት አካባቢ ስለ ማህፀን በር ካንሰር ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

05/08/2026
"በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት" በሚል በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር  በሁሉም ወረዳዎችና ክ/...
04/08/2026

"በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት" በሚል በብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሐ ግብር በሁሉም ወረዳዎችና ክ/ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በመርሐ ግብሩም በጎ ፈቃደኛ ሴቶች በደም ልገሳ ከደም ባንክ ጋር በመተባበር ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ምርመራ ከጤና ተቋማት ጋር በመተባበር እና በጎነት በሆስፒታል በትራፊክ ደህንነት ና በሁሉም በእቅድ በተያዙ ተግባራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa prosperity women’s league- ብልፅግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share