Ethiopian Coffee & Tea Authority

Ethiopian Coffee & Tea Authority Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Coffee & Tea Authority, Government Organization, Addis Ababa.

የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፤የ10 አመት የተከለሰ ኮምፕሬሄንሲቭ የቡና ስትራቴጂ ዕቅድም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።ነሐሴ 26/2018 ዓ.ምየኢትዮጵያ ቡናና...
01/09/2026

የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄደ፤
የ10 አመት የተከለሰ ኮምፕሬሄንሲቭ የቡና ስትራቴጂ ዕቅድም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ።

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣ ከቡና ሻይና ቅመማ ቅመም አብቃይ ክልሎች እና የባለስልጣኑ አመራሮች በታደሙበት መድረክ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና የ10 አመት የተከለሰ ኮምፕሬሄንሲቭ የቡና ስትራቴጂ ዕቅድ ላይ የግምገማና ውይይት መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የቡና ሻይ ቅመማ ቅመም ልማት ዘርፍ ኃላፊ ክቡር አቶ ታጋይ ኑሩ ንግግር አሰምተዋል። በንግግራቸው ያለባለድርሻ አካላት ተሳትፎ የታቀደ ከዳር እንደማይደር ስለሚታወቅና የተገኘውም የክንውን ውጤት በመድረኩ በታደሙ አካላት እና በቡና ተዋናዩ ጥረት ስለሆነ በጋራ ለመነጋገር መድረኩ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።

ከተዘጋጀ ፓኬጅ የተቀዱ በአንገብጋቢነት የሚለዩ የቡና ኢኒሼቲቮች እንዳሉ የተናገሩት ኃላፊው ወደአርሷደሩ እንደወረደ ገልጸዋል፤ በጉዳዩ ላይም ስልጠና ይሰጣል ብለዋል።

በማስከተልም አቶ ቦንሳ መርጋ የባለስልጣኑ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ዕቅድ አፈጻጸሙን አቅርበዋል። ሲያቀርቡም 1.6 ሚሊዮን ሄክታር በቡና እንደተሸፈነ ገልጸው ከአምናው አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ14 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል።

የምርት አፈጻጸሙን ሲያቀርቡም 1.5 ሚሊዮን 80 ሺ ቶን እንደሆነ ተናግረው ምርታማነት 9.4 ኩንታል በሄክታር እንደሆነ ገልጸዋል።

ከላይ የተጠቀሱት ውጤቶች የተመዘገቡበት ምክንያቶችን ሲናገሩ በአዲስ ቡና ተከላ፣ በማሳ እንክብካቤ፣ በጉንደላ እና በነቅሎ ተከላ ላይ ስራዎች በመሰራታቸው ነው ብለዋል። በቀጣይም ጉንደላና ነቅሎ ተከላ ላይ በይበልጥ መሠራት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።

በተመሳሳይ መልኩ በሻይውና በቅመማቅመም ሰብሎች ላይ ያለውን አፈጻጸም አቅርበዋል።

የኤክስፖርት አፈጻጸሙን ሲያቀርቡም 40 በመቶ የዓለም ዋጋ በቀነሰበት፣ የሆርሙዝ ክስተት በታየበት፣ የነዳጅ ዋጋ በናረበት፣ የብራዚል ቡና በገፍ ወደገበያ በገባበት ሁኔታ የታቀደው 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተሳክቷል ብለዋል። ይህ ብቻ ሳይሆን ከታቀደው የቡና መጠን ያነሰ ተልኮ መሳካቱም ስኬቱን ለየት ያደርገዋል ብለዋል።

በዚህ ሁሉ ተግዳሮቶች ውስጥ ለመጣውም ውጤት ምክንያቶቹን ሲያቀርቡም ከጀረጃ 1 እስከ ደረጃ 3 ያሉ ቡናዎች መጠን እና ዋጋቸው መጨመር መሆኑን ጠቅሰው ይህ ምን ያህል የቡና ጥራት ላይ ውጤታማ ስራ እንደተሰራ ማሳያ ነው ብለዋል።

በማስከተልም ስትራቴጂ ዕቅዱ ቀርቦ በሁለቱም አጀንዳዎች ላይ ሐሳቦች ከታዳሚው ተሰንዝረው የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል።

አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው

በ  #ፓኪስታን  #ኢስላማባድ ለመጀመሪያ ጊዜ የ  #ኢትዮጵያ ቡና መሸጫ ካፌ ተከፈተ​በእስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመንታ ከተሞች እስላማባድ እና ራዋልፒንዲ የመጀመሪያው የሆነው ...
01/09/2026

በ #ፓኪስታን #ኢስላማባድ ለመጀመሪያ ጊዜ የ #ኢትዮጵያ ቡና መሸጫ ካፌ ተከፈተ

​በእስላማባድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመንታ ከተሞች እስላማባድ እና ራዋልፒንዲ የመጀመሪያው የሆነው የኢትዮጵያ ቡና ካፌ መከፈቱን አስታወቀ።

​በፓኪስታን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ዑመር ሁሴን (ዶ/ር) እሁድ ዕለት ባካሄዱት የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት፣ የኤምባሲው ሠራተኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በተገኙበት በባህላዊ የቡና አፈላል ሥነ-ሥርዓት ካፌውን መርቀው ከፍተዋል።

​አምባሳደሩ በምረቃው ወቅት እንደገለፁት፣ ካፌው መከፈቱ በኢትዮጵያ እና በፓኪስታን መካከል እያደገ ከመጣው ሁለትዮሽ ግንኙነት ጎን ለጎን የባህል እና ሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር አዲስ መንገድ ይከፍታል።

https://www.facebook.com/share/p/1CHvfNAmPG/

ሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በሙዳ–ድኖቆሰ ቀበሌ በአርሶ አደር ጓሮ እየለማ የሚገኘው የቡና ልማት በአሁኑ ወቅት አበረታች ገጽታ እያሳየ ይገኛል።በተለይም በቡና ዛፎቹ ላይ በብዛት የተያዙ የቡና ፍሬ...
30/08/2026

ሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በሙዳ–ድኖቆሰ ቀበሌ በአርሶ አደር ጓሮ እየለማ የሚገኘው የቡና ልማት በአሁኑ ወቅት አበረታች ገጽታ እያሳየ ይገኛል።

በተለይም በቡና ዛፎቹ ላይ በብዛት የተያዙ የቡና ፍሬዎች የልማቱን የምርት አቅም የሚያሳይ ሲሆን፣ በጓሮ ልማት ውስጥ ከበቆሎና ሌሎች ሰብሎች ጋር ተቀናጅቶ መልማቱም የመሬት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዝ ነው።

የጓሮ ቡና ልማት ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ከመፍጠሩም በላይ የቤተሰብ ኢኮኖሚን በማጠናከር የአካባቢውን የቡና ምርት አቅም ለማሳደግ የሚጫወተው ሚና የጎላ ነው።

በዚህም መነሻነት የቡና ችግኝ ማፍላት፣ በተገቢው የአተካከል ዘዴ መትከል፣ የእርሻ እንክብካቤን ማጠናከር እና የተቀናጀ የቡና ልማትን ማስፋፋት ለቀጣይ የምርት ዕድገት ወሳኝ ናቸው።

በሙዳ–ድኖቆሰ ቀበሌ የሚታየው ይህ የቡና ልማት ገጽታ በጓሮ ልማት የተሻለ ምርትና የተሻለ ገቢ ለማምጣት የሚቻል መሆኑን የሚያሳይ አበረታች ምሳሌ ነው።

መረጃው የሙደ ድኖቆሳ ቀበሌ ግብርና ጽ/ቤት ነው።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።መልካም በዓል!!!
25/08/2026

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።

መልካም በዓል!!!

ዓለም አቀፍ የቡና ሁኔታን በወፍ በረር!!​የገበያ ሁኔታ​የአሜሪካ የግብርና ሚኒስቴር (USDA) በ2026/27 የምርት ዘመን የዓለም ቡና ምርት አዲስ እና  ታሪካዊ ደረጃ ላይ ይደርሳል ሲል ...
21/08/2026

ዓለም አቀፍ የቡና ሁኔታን በወፍ በረር!!

​የገበያ ሁኔታ
​የአሜሪካ የግብርና ሚኒስቴር (USDA) በ2026/27 የምርት ዘመን የዓለም ቡና ምርት አዲስ እና ታሪካዊ ደረጃ ላይ ይደርሳል ሲል መግለጹ ተሰምቷል።

የዓለም የቡና ምርት በ10.8 ሚሊዮን ጆንያዎች በማደግ በድምሩ 189.7 ሚሊዮን ጆንያ በመድረስ አዲስ የምርት ጣሪያ ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል። የዓለም አቀፍ የቡና ፍጆታ 179.7 ሚሊዮን ጆንያ ይደርሳል ተብሎ የተገመተ ሲሆን፣ የዓመቱ መጨረሻ የተጠራቀመ ክምችት ደግሞ ወደ 26.3 ሚሊዮን ጆንያ ያድጋል። ለዚህ የምርት እድገት ኢትዮጵያ፣ ብራዚል፣ ቬትናም እና ኡጋንዳ በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ በተቃራኒው የኢንዶኔዢያ ምርት ከመጠን በላይ በጣለው ዝናብ ምክንያት በ1 ሚሊዮን ጆንያ ይቀንሳል ተብሏል።

በ​ሳህለማርያም ገ/መድህን

19/08/2026
☕️ 1 ዩሮ ወደ 11.20 ዩሮ  ፦ አውሮፓ እሴት ባልተጨመረበት ቡና የምታገኘው ግዙፍ ትርፍ !ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው አጠቃላይ ቡና ውስጥ 34 በመቶ የሚሆነው መድረሻው የአውሮፓ ገበያ...
17/08/2026

☕️ 1 ዩሮ ወደ 11.20 ዩሮ ፦ አውሮፓ እሴት ባልተጨመረበት ቡና የምታገኘው ግዙፍ ትርፍ !

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልከው አጠቃላይ ቡና ውስጥ 34 በመቶ የሚሆነው መድረሻው የአውሮፓ ገበያ መሆኑን «የቡና ምጣኔ ሀብታዊ ተፅዕኖ በአውሮፓ» (Economic Impact of Coffee in Europe) የተሰኘ ጥናት ይፋ አድርጓል።

ይህንን የቡና ኢኮኖሚ የዳሰሰ ጥናት ያጠናው በዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) የሚገኘው «አውሮፓ ኢኮኖሚክ ሪሰርች ሊሚትድ» (European Economic Research Limited) የተባለ ተቋም ነው።

ሰነዱ የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራትን ጨምሮ እንግሊዝ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድን ያካተተ ሰፊ ቀጠናን የተመለከተ ነው።

በጥናቱ መሠረት እ.ኤ.አ. በ2024 የአውሮፓ ሀገራት ከኢትዮጵያ 523.6 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ቡና ያስገቡ ሲሆን፣ ይህም ለአውሮፓ አጠቃላይ የቡና ገቢ ንግድ (Import) 3.4 በመቶውን ብቻ የሚሸፍን ቢሆንም፣ ለኢትዮጵያ ግን አጠቃላይ የውጭ ሸቀጥ ሽያጭ 11.8 በመቶውን የሚሸፍን ዋነኛው የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ነው።

ጥናቱ እንደሚያሳየው አውሮፓ ራሷ ቡና የማታመርት ብትሆንም እ.ኤ.አ. በ2025 ከቡና ዘርፍ ከግማሽ ትሪሊዮን ዩሮ በላይ የምጣኔ ሀብት ምርታማነት (Economic Output) እና 251.5 ቢሊዮን ዩሮ አጠቃላይ የተጨመረ እሴት (GVA) አግኝታለች።

እ.ኤ.አ. በ2025 ብቻ ወደ አውሮፓ 18.7 ቢሊዮን ዩሮ የሚያወጣ 2.9 ሚሊዮን ቶን ቡና የገባ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ከ97 በመቶ በላይ የሚሆነው አምራች ሀገራት የላኩት ያልተቆላና ያልተቀነባበረ አረንጓዴ ቡና መሆኑ ተጠቅሷል።

ሰነዱ እንደሚጠቁመው ቡናን የመቁላትና የማቀነባበር ሥራዎች የሚከናወኑት ምርቱ ከሚመነጭባቸው አገሮች ይልቅ ወደ ሸማቹ ማኅበረሰብ በቀረቡ የአውሮፓ ቀጣናዎች ነው።

እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አምራች ሀገራት ያልተቆላና እሴት ያልተጨመረበት አረንጓዴ ቡና ብቻ በብዛት የሚልኩ ሲሆን አውሮፓውያን ግን ቡናውን ካስገቡ በኋላ በማከማቸት፣ በመቁላት፣ ካፌይን በመቀነስ፣ ፈጣን (Soluble) ቡና በማምረት እና በተለያዩ የችርቻሮ ሽያጭ፣ የሆቴልና ቱሪዝም (Hospitality) ዘርፎች ላይ በማዋል ከፍተኛውን ጥቅም ለራሳቸው ያተርፋሉ።

የጥናቱ የምጣኔ ሀብት ማባዣ (Economic Multiplier) ሙሉ ሐሳብ እንደሚያሳየው፤ እያንዳንዱ አምራች ሀገር 1 ዩሮ የሚያወጣ አረንጓዴ የቡና ምርት ወደ አውሮፓ ገበያ ሲያስገባ፣ ቡናው አውሮፓ ከገባ በኋላ በሚደረግለት ፦
- የማቀነባበር፣
- የማሸግ፣
- የችርቻሮ ሽያጭ እና በካፌዎች አማካኝነት በሚቀርብበት ሰንሰለት ውስጥ አልፎ 11.20 ዩሮ ቀጥተኛ የአውሮፓ ምጣኔ ሀብት ምርታማነትን (Direct European Economic Output) ይፈጥራል።

ይህ መረጃ ከሪፖርተር ጋዜጣ መወሰዱን እንገልጻለን።

15/08/2026

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Coffee & Tea Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Coffee & Tea Authority:

Shortcuts

Share