Addis ketema woreda 9 communication

Addis ketema woreda 9 communication this is adis ketema woreda 9 communnication office

ቅጠል ተራን  ወደ ውብ መኖሪያ ሥፍራ! ለመኖር እጅግ ምቹ ያልሆነ፤ ለሰው ልጅ ክብር በማይመጥን፤ በጣም የቆሸሸ፣ የተፋፈገ እና የተጨናነቀ እንዲሁም ከተማ እምብርት ላይ ሆነው በተተበተበ ለአ...
25/04/2026

ቅጠል ተራን ወደ ውብ መኖሪያ ሥፍራ!

ለመኖር እጅግ ምቹ ያልሆነ፤ ለሰው ልጅ ክብር በማይመጥን፤ በጣም የቆሸሸ፣ የተፋፈገ እና የተጨናነቀ እንዲሁም ከተማ እምብርት ላይ ሆነው በተተበተበ ለአደጋ አጋላጭ የሆነ የኤሌክትሪክ መስመር ብሎም በኩራዝና በሻማ የሚጠቀሙ ነዋሪዎች ይኖሩበት የነበረውን የቅጠል ተራ ሰፈርን፣ ወደ ውብ መኖሪያ አካባቢነት ለመቀየር ዛሬ ባለ 8 ወለል የሆኑ ብዛታቸው 9 ህንጻዎች ከ500 በላይ ቤቶችን ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠናል።

ይህ ፕሮጀክት አካባቢው መንገድ ያልነበረው፣ እንደ ሸረሪት ድር የተጠላለፉ ገመዶች የበዙበት፣ ነዋሪዎች በድህነት ምክንያት ኑሯቸውን ለመደጎም ቤታቸው ውስጥ ቆጥ ሰርተው አልጋ የሚያከራዩበትና ሰዎች ላይ ቆልፈው በሚሄዱበት ጊዜ በሚፈጠር የእሳት አደጋ የሰዎች ህይወት የሚጠፋበት፣ ንብረት የሚወድምበት፣ እጅግ ብዙ ገመናዎችን የያዘ አስከፊ የሰው ህይወትን የሚቀይር ፕሮጀክት ነው።

አካባቢው የከተማ እምብርት ሆኖ ሳለ፣ ነገር ግን በብዙዎቹ የገጠር አካባቢዎች እንኳን የቀረውን ሻማ እና ኩራዝ የሚጠቀም ነዋሪ ያለበት አካባቢ ነው።

መርካቶ አካባቢ ብዙ “ተራ” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው - ቅጠል ተራ፣ ጭድ ተራ፣ ገብስ ተራ፣ ሳር ተራ፣ ቦንብ ተራ … ጠጋ ብለን ስናያቸው የነዋሪዎቻችን የአኗኗር ሁኔታ እና ገፅታውን የሚያሳዩ ናቸው። እንደዚህ ዓይነት ችግሮችን ደጋግመን በማውራት ነዋሪው ሆድ እንዲብሰው ማድረግ ሳይሆን፣ መፍትሄው ሰርተን ህይወቱ እንዲቀየር እና ለሰው ልጆች የሚመጥን የክብር ኑሮ እንዲኖር እዚያው የመኖሪያ ቤት እና የንግድ ቦታዎች እንዲያገኝ ማድረግ ነው ።

በከተማችን ዋነኛ የስራዎቻችንን ማዕከል ሰው ተኮር ስራዎች አድርገን እየሰራን እንገኛለን ።
በቅጠል ተራ ያስጀመርነው የቤት ግንባታ 10ሺህ ካሬ ላይ ያረፈ፤ ተገንብቶ ሲጠናቀቅም ከ20,000 በላይ ሰዎችን ንፁህ፤ ለሰው ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗር ያለው መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጅክት ነው ።

ፕሮጀክቱ ልጆች ቦርቀው እንዲያድጉ የስፖርት ሜዳ እንዲሁም የንግድ ሱቆች እና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ ተሟልተውለት በጥራት እና በፍጥነት ተገንብቶ ይጠናቀቃል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!

የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ይኽ ጉብኝት በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጠንካራ እና ዘላቂ ግ...
24/04/2026

የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት ሳልቫ ኬር ማያርዲትን በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት የሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ተቀብያለሁ። ይኽ ጉብኝት በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለውን ጠንካራ እና ዘላቂ ግኙነት የሚያሳይ ነው። ትብብራችንን እና የጋራ ፍላጎቶቻችን ለማጠናከር የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት እንደምናደርግ እምነቴ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር  ዐቢይ አሕመድ እንኳን ደስ አለዎት!ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር  ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intellige...
23/04/2026

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እንኳን ደስ አለዎት!

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው በመሾምዎ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም እንኳን ደስ አለን ለማለት እወዳለሁ።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን የጥረታቸው ፍሬ በአፍሪካ ደረጃ እውቅና አግኝቶ ለዚህ ሹመት መብቃታቸው ለኢትዮጵያን ሁሉ ኩራት ነው ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የረዳን ፈጣሪ አምላክ የተመሰገነ ይሁን!!ዛሬ በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን የአዲስ መሶብ ተንቀሳቃሽ ዲጂታታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ  ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/...
22/04/2026

የረዳን ፈጣሪ አምላክ የተመሰገነ ይሁን!!

ዛሬ በአይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነውን የአዲስ መሶብ ተንቀሳቃሽ ዲጂታታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) አስጀምረውልናል።

የአዲስ መሶብ ተንቀሳቃሽ አገልግሎት ህዝብ ወደ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች መሄድ ብቻ ሳይሆን አገልግሎት ራሱ ወደ ህዝቡ እንዲጠጋ የማድረግ እድልን ይፈጥራል።

የተንቀሳቃሽ አውቶቢስ የአዲስ መሶብ አገልግሎትን በተሟላ ደረጃ አገልግሎት የጀመረ ሲሆን ህዝባችን በአለበት ቦታ ሆኖ አገልግሎት እንድያገኝ እድል ይፈጥራል።

በአውቶቢሱ ላይ የአገልግሎት መስጫ ሥራ፣ የሀይል አማራጭ ሥራ (ከፀሓይ ብርሃን)፣ ፈጣን የኔትወርክ አማራጭን (MPLS = Multi Protocol Label Switching) በተሳካ ሁኔታ ተግባራዊ ተደርጓል፣ የካሜራ ገጠማ እና የኮንፊግሬሽን ሥራ ተጠናቋል፣ የአገልግሎት መስጫ መሠረታዊ ግብዓቶች ተሟልቶ፣ የሙከራ አገልግሎት በተሳካ ሁኔታ ተደርጓል።

ከቴክኖሎጂ ዝግጅት አንፃር ወጪን የሚቆጥብ (በየማዕከላቱ የዳታ ማዕከል ግንባታን የሚያስቀር)፣ የአገልግሎት ጥራት እና ወጥነትን የሚያረጋግጥ፣ በሁሉም ማዕከላት ተመሳሳይ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የUnified Infrastructure Model ተግባራዊ ማድረግ መቻላችን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነዉ።

ተንቀሳቃሽ የአውቶቢስ አገልግሎት የተጀመሩ አገልግሎቶች፦
በመሶብ የአንድ ማዕከል፥
- የገቢ አገልግሎት (አዲስ ቲን ማውጣት)
- የንግድ አገልግሎት (ንግድ ፈቃድ ማውጣት፣ ማደስ)
- የጤና (ለመንጃ ፈቃድ አካላዊ የጤና ምርመራ)
- የሲቪል ምዝገባ (የመታወቂያ ዕድሳት እና ልደት)
- የአሸከረካሪ ተሽከርካሪ (የመንጃ ፈቃድ እና የቦሎ ዕድሳት)
- የኢትዮ ፖስታ (የመንገድ ፈንድ ክፍያ)
- የብሔራዊ መታወቂያ (አዲስ ምዝገባና የመረጃ እርማት)
- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (ቅድመ ክፍያ)
የሚሰጡ አገልግሎቶች ናቸው።

በከተማችን ብሎም በሀገራችን ለዘመናት የአገልግሎት ዘርፉን ለመለወጥ ሳይቻል ስር በሰደደ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር ተተብትቦ የኖረ ቢሆንም መንግስት ቃል በገባው መሰረት ችግሩን ሥር ነቀል በሆነ መልኩ የሚለውጥ 'የመሶብ' ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በመተግበር ለተገልጋዩ ታላቅ ሽግግር እና እፎይታን ይዞ መጥቷል።

ለሕዝባችን የምናቀርበዉ ባዶ ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን የገባነውን ቃል ሁሌ በታማኝነት በተግባር ተከታታይነት ያለው የማያቋርጥ ተግባር እያከናወን ነዉ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧቿን ይባርክ።

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝግባ ሊጠናቀቅ አንድ ቀናት ብቻ ቀሩት! እንግዲያውስ ባሉበት ሆነው በ"ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በ...
21/04/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ምዝግባ ሊጠናቀቅ አንድ ቀናት ብቻ ቀሩት!

እንግዲያውስ ባሉበት ሆነው በ"ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።

እንኳን ደስ አለን !!በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ አጠቃላይ ዝግጅት፣ በመሰረተ ልማቱ ምቹነት፣ በውድድር ሂደቱ እና በደጋፊ የከተማችን ነዋሪ ሞራል እና  ስፖርታዊ ጨዋነት በመደመም፤ አዲስ ...
18/04/2026

እንኳን ደስ አለን !!

በአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪክስ አጠቃላይ ዝግጅት፣ በመሰረተ ልማቱ ምቹነት፣ በውድድር ሂደቱ እና በደጋፊ የከተማችን ነዋሪ ሞራል እና ስፖርታዊ ጨዋነት በመደመም፤ አዲስ አበባ በሚቀጥለው ዓመት በፈረንጆቹ በ2027 የሚካሄደውን የግራንድ ፕሪክስ ውድድር በ'ወርቅ ደረጃ' እንድታዘጋጅ የዓለም አትሌቲክስ በዛሬው መርሃ ግብር ላይ ይፋ አድርጓል ።

በድጋሚ እንኳን ደስ አለን!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ !

Baga Gammanne!

Qophii waliigalaa Giraandi Piriiksi Finfinnee,mijaa'ummaa bu'uura misoomaa,adeemsa dorgommichaa fi hamilee fi naamusa Ispoortii deeggartoota jiraattota magaalaa keenyaa dinqisiifachuun,Finfinneen bara dhufu bara faranjoota 2027tti kan gaggeeffamu dorgommii Giraandi Piriiksi " Sadarkaa Warqeetti" akka qopheessitu atileetiksiin addunyaa sagantaa har'aa irratti ifa godhee jira.

Irra deebiin baga gammanne!
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

Congratulations to all!

In recognition of the exceptional organization of the Addis Ababa Grand Prix, the quality of our infrastructure, and the exemplary sportsmanship displayed by our residents, World Athletics has officially announced that Addis Ababa will host the 2027 Grand Prix with 'Gold Level' status.
This prestigious upgrade reflects our city’s growing capacity to host world-class sporting events. Once again, congratulations to everyone!

ዛሬ ኢትዮዽያ  በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን በአዲስ አበባ (Addis Ababa Grand Prix) በድምቀት አስተናግዳለች። ይህ ስኬት በከተማችን የ...
18/04/2026

ዛሬ ኢትዮዽያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን በአዲስ አበባ (Addis Ababa Grand Prix) በድምቀት አስተናግዳለች።
ይህ ስኬት በከተማችን የገነባናቸው ዘመናዊ የስፖርት መሠረተ ልማቶች ውጤት ከመሆኑም ባለፈ፣ አገራችን በአትሌቲክስ ዘርፍ ያላትን ታላቅ ዝና ዳግም ያረጋገጠ ነው።

በሚያዝያ ወር ብቻ የምናስተናግዳቸው ሦስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች፣ ከተማችን ማንኛውንም ዓይነት ዓለም አቀፍ ውድድር የማስተናገድ ብቃትና ደረጃ ላይ መድረሷን የሚያሳዩ ናቸው። እነዚህ ውድድሮች ተተኪ አትሌቶችን ከማነቃቃታቸውም በላይ ለስፖርታዊ ቱሪዝም ዕድገት የጎላ ፋይዳ አላቸው።
ይህ ታሪካዊ ውድድር በአዲስ አበባ መካሄዱ ከተማችንን ለነዋሪዎቿ ምቹና ሳቢ ከማድረግ ባለፈ፣ ለዓለም አቀፍ ኩነቶች ማራኪ የስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን በተግባር ያሳየ እውነት ነው።

ውድድሩ በስኬት እንዲጠናቀቅ የተለመደውን ኢትዮጵያዊ ጨዋነትና እንግዳ ተቀባይነት ላሳያችሁ ስፖርት ወዳድ ነዋሪዎቻችን፣ በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።
ለእንግዶቻችን በቆንጆዋ አዲስ አበባ የማይረሳና ያማረ ቆይታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

Har'a Itoophiyaan seenaa ishee keessa yeroo jalqabaaf dorgommii fiigicha guyyaa tokkoo atileetiksii addunyaa (Addis Ababa Grand Prix) miidhaginaan keessummeessitee jirti. Milkaa'inni kuni magaalaa keenyatti kan ijaarre bu'aa misooma bu'uuraa ispoortii ammayyaa ta'uurra dabree, biyyi keenya damee atileetiksiin maqaa guddaa qabdu irra deebiin kan mirkaneesseedha.

Ji'a Eblaa qofa keessa kan keessummeessinu taateewwan ispoortii idil-addunyaa gurguddoo sadi, magaalaan teenya dandeettii fi sadarkaa dorgommii idil-addunyaa kamuu keessummeessuurra gahuu kan mul'isaniidha. Dorgommiileen kunniin atileetota bakka bu'oo kakaasuu caalattis guddina tuurizimii ispoortiif faayidaa olaanaa qabu.

Dorgommiin seena qabeessi kuni Finfinneetti gaggeeffamuun magaalaa teenya jiraattota isheef mijattuufi hawwattuu taasisuu irra dabree, taateewwan idil-addunyaaf giddugala miidhagduufi hawwwttuu ta'aa dhufuushee dhugaa qabatamaan mul'iseedha.
Dorgommichi milkaa'inaan akka xumurumu naamusa Itoophiyummaa baratameefi simannaa keessummaa kan mul'istan jiraattota keenya jaalattoota ispoortii, maqaakoo fi maqaa bulchiinsa magaalaatiin galata guddaan dhiheessa.
Keessummoota keenyaaf Finfinnee miidhagduutti turtii hin irraanfatamnee fi miidhagaa akka qabaattan isiniif hawwa.

Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

የኮፕ32 አስተናጋጅ እንደሆነ ሀገር፤ ኢትዮጵያ‎ብሔራዊ ኮሚቴ በይፋ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ ጀምራለች። ይህን ሂደት በግልጽ ግብ እና በላቀ ምልከታ ለመምራት ቁልፍ አመራር መድበናል። ይ...
17/04/2026

የኮፕ32 አስተናጋጅ እንደሆነ ሀገር፤ ኢትዮጵያ
‎ብሔራዊ ኮሚቴ በይፋ በማቋቋም ዝግጅቷን ቀደም ብላ ጀምራለች። ይህን ሂደት በግልጽ ግብ እና በላቀ ምልከታ ለመምራት ቁልፍ አመራር መድበናል። ይህን ተከትሎ የኮፕ ፕሬዝደንት መዋቅር የተቀናጀና የላቀ ውጤት የሚያስገኙ የቅድሚያ ተግባራቱን ጀምሯል።

ዛሬ ከብሔራዊ ኮሚቴው ጋር በነበረን ስብሰባ፤ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ የእስካሁን ሥራዎችን በመገምገም ክፍተቶችን የመለየት እና ሁሉም ጥረቶቻችን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር የተጣጣሙ መሆናቸው ተዳሷል። በመድረኩ ከግምገማ ባሻገር የጋራ ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጠንበታል። ትኩረታችን ግልጽ ነው፤ በጠንካራ ትብብር፣ በተዋሃደ ታላቅ ርዕይ እና የጋራ ጽኑ ትጋት ተናበን ይህን ዓለም አቀፍ ሁነት በልህቀት በማስተናገድ የሀገርን ታላቅነት ዳግም ማሳየት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጋቢ ቶማስ አዲስ አበባ ገብታለችየኦሎምፒክ እና ዓለም ሻምፒዮና አሜሪካዊቷ ጋቢ ቶማስ አዲስአበባ ገብታለች።አሜሪካዊቷ አትሌት በአዲስ አበባ በሚዘጋጀው "ግራንድ ፕሪክስ" ለመወዳደር ነው የመጣ...
16/04/2026

ጋቢ ቶማስ አዲስ አበባ ገብታለች

የኦሎምፒክ እና ዓለም ሻምፒዮና አሜሪካዊቷ ጋቢ ቶማስ አዲስአበባ ገብታለች።

አሜሪካዊቷ አትሌት በአዲስ አበባ በሚዘጋጀው "ግራንድ ፕሪክስ" ለመወዳደር ነው የመጣችው።

የ29 ዓመቷ አትሌት በ2024ቱ የፓሪስ ኦሊምፒክ በ200 ሜትር የወርቅ ሜዳልያ ባለቤት እንደሆነች ይታወሳል።

አዲስ አበባ -ሁሌም ጀግኖችዋን ታከብራለች!እነዚህ ሃውልቶች እና ቅርጾች በቅርቡ በኮሪደር ልማቱ እውን ከሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች ውስጥ ናቸው።ዛሬ በህይወት ባይኖሩም ስለ አዲስ አበባ ብዙ ...
16/04/2026

አዲስ አበባ -ሁሌም ጀግኖችዋን ታከብራለች!

እነዚህ ሃውልቶች እና ቅርጾች በቅርቡ በኮሪደር ልማቱ እውን ከሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች ውስጥ ናቸው።

ዛሬ በህይወት ባይኖሩም ስለ አዲስ አበባ ብዙ የፃፉ፥ ሙዚቃ ያዜሙላት፥ በስዕል ውበቷን የገለጿት እና በእደጥበብ ደግሞ ያስጌጧት ውድ ልጆችዋን የሚዘክሩ ናቸው።

ጀግኖችዋን የምታከብር አዲስ አበባ፥ ለከተማቸውና ለሀገራቸው ያበረከቱት ስራ ህያው ሆኖ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገር ሃውልት አኑራላቸዋለች።

ለከተማዋ እፎይታን የሰጡት ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያዎችበአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም በቂ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ ባለመኖሩ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች በመንገድ ላይ ለረጅም ጊዜ በመቆ...
15/04/2026

ለከተማዋ እፎይታን የሰጡት ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያዎች

በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም በቂ የመኪና ማቆሚያ ስፍራ ባለመኖሩ በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች በመንገድ ላይ ለረጅም ጊዜ በመቆም በትራፊክ ፍሰቱ ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል ሲፍጠሩ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ችግሩን ከምንጩ ለመፍታት አዳዲስና በቴክኖሎጂ የታገዙ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ ተርሚናሎችን በመገንባት በከተማዋ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነስ ባሻገር ለመዲናዋም ዘመናዊ ገጽታን እያላበሳት ይገኛል፡፡

አሁን ላይ በከተማዋ የተገነቡ የመኪና ማቆሚያዎች ዝናብና ፀሀይን የሚከላከሉ፣ ማረፊያ ስፍራ ያላቸው እና የደህንነት ካሜራ የተገጠመላቸው በመሆኑ ከዚህ ቀድም ይደርስ የነበረውን እንግልት ማስቀረት ተችሏል፡፡

በተጨማሪም ለተጠቃሚው እፎይታን ያላበሱ እነዚህ ዘመናዊ የመኪና ማቆምያዎች የትራፊክ መጨናነቅን በመቀነስ ፣ የትራንስፖርት ፍሰትን በማሳለጥ ፣ የትራፊክ አደጋን እንዲቀንስና የመኪና ስርቆትን በመከላከል የጊዜና የነዳጅ ብክነትን በመቅረፍ ምርታማነት እንዲያድግ አስችለዋል፡፡

በቀጣይም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ መጨናነቅን በከፍተኛ ደረጃ የሚያቃልሉና የትራንስፖርት ፍሰቱን የሚያሳልጡ ተጨማሪ አዳዲስ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያዎችን በመገንባት መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ይቀጥላል፡፡

እኔ ምርጫ ካርድ ወስጃለሁ እናተስ !በሀገር ጉዳይ ላይ ባለቤትነትዎን የሚያረጋግጡበት የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙን ያውቃሉ? እስካሁን ባለው የምዝገባ ሂደት...
13/04/2026

እኔ ምርጫ ካርድ ወስጃለሁ እናተስ !

በሀገር ጉዳይ ላይ ባለቤትነትዎን የሚያረጋግጡበት የመራጮች ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም መራዘሙን ያውቃሉ? እስካሁን ባለው የምዝገባ ሂደት ከ42 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ተመዝግበዋል፤ እርስዎስ ተመዝግበዋል?

ባሉበት ሆነው በ*ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis ketema woreda 9 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Addis ketema woreda 9 communication:

Share