Grand Ethiopian Renaissance Dam,Addis Ababa

Grand Ethiopian Renaissance Dam,Addis Ababa ራዕይ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በመላ የከተማችን ነዋሪ ህዝቦች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ተጠናቆ የሰላም ፣ የኢኮኖሚና የብልፅግናችን ምንጭ ሆኖ ማየት፡፡

ይህ የፌስቡክ ገጽ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው፡፡
በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ መላ የሀገራችን ህዝቦች እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የፋይናንስ፤የአካባቢ ጥበቃና ተፋሰስ ልማት ድጋፍ በማጎልበትና የቁጠባ ባህል እንዲያድግ በማድረግ ታሪካዊ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ በማስቻል፤የሀገራችንን ገጽታ ግንባታና ብሄራዊ መግባባት ማጠናከር ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሰራተኞች የአዲስ  አበባ ከተማ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን  "ትውልድን በስነ-ምግባር  ፤...
23/07/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ሰራተኞች የአዲስ አበባ ከተማ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን "ትውልድን በስነ-ምግባር ፤ተቋምን በአሰራር!" በሚል መሪቃል ባዘጋጀው የደም ልገሳ ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ ደም ለግሰዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ታላቁ የኢትዮጵያህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ፕ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት ስራ አፈፃፀሙን ገመገመየህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ፕ/ጽ/ቤቱ ዛሬ ሐም...
15/07/2026

የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ታላቁ የኢትዮጵያህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ፕ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት ስራ አፈፃፀሙን ገመገመ
የህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ፕ/ጽ/ቤቱ ዛሬ ሐምሌ 8/2018 ለግማሽ ቀን ባዘጋጀው የውይይት መድረክ የበጀት አመቱ ስራአፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ከክፍለ ከተማ ጽ/ቤትአመራሮች ጋር ገምግሟል ፡፡ የህዳሴውን የ14 አመታት ጉዞየሚዘክሩና ለቀጣይ ትውልድ በተሞክሮነት ሊተላለፉ የሚችሉዶክመንቶችን እያሰባሰቡ ከማደራጀትና ተንጠባጥበው የቆዩየኦዲት ስራዎችን ከመስራት አንፃር ጠንካራ አፈፃፀም እንደነበረበሪፖርቱ ተብራርቷል ፡፡
የህዳሴ ግድቡን መልካም ገፅታ የሚገነቡና ያለውን ሁለንተናዊፋይዳ የሚዳስሱ የኮሙንኬሽንና የህዝብ ግንኙነት መረጃዎችንበተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ተደራሽ ከማድረግ አንፃርም አበረታችእንቅስቃሴ የተደረገ መሆኑ በመድረኩ ተብራርቷል ፡፡ በበጀትአመቱ በየደረጃው ከሚገኙ ከተለያዩ ባለድርሻና አጋር አካላት ጋርተቀናጅቶ ከመስራትና ውጤታማ አፈፃፀምን ከማከናወንአንፃርም ጥሩ አፈፃፀም እንደታየ በሪፖርቱ ተገልፃል ፡፡
የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የማስተባበሪያ ፕ/ጽ/ቤቱዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ኒዕመተላህ ከበደ እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ የታላቁ ህዳሴ ግድብ እልህ አስጨራሽ ጉዞ የመንግስትና ህዝብ መቀራረብ በተለይም ባለፍት የለዉጥ አመታት መንግስት የህዝብ የረጅም ዓመት ቁጭት የነበረዉን ግድብ አጠናቆ ለምርቃት ያበቃበት ዓመት በመሆኑ በበጀት ዓመቱ የ14ዓመት የማስተባበሪያ ፅ/ቤታችን ዶክመንቶችን የማሰባሰብናየማደራጀትና የተሰበሰበ ሀብት በትክክል ለታለመለት ዓላማ መዋሉን የኦዲት ስራዎችን በመስራት እንዲሁም የኮሙንኬሽንና የህዝብግንኙነት መረጃዎችን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ተደራሽከማድረግ አንፃር ጠንካራ አፈፅፀም መታየቱን አብራርተዋል ፡፡
ስራ አስኪያጇ አክለውም ህዳሴውን ሁለንተናዊ ሂደት ከጅምሩእስከ ምርቃቱ ድረስ ተደረገውን እንቅስቃሴ በመረጃነት እንዲያገለግል መደረጉም የዶክመንቴሽን ስራው ማሳያመሆኑን ገልፀዋል ፡፡
አስኪያጇ በቀጣይም የተቋሙ ቀሪ የዘርፉን ስራዎች ትኩረት ሰጥተንና ተቀናጅተን መስራትይጠበቅብናል የሚል ማብራርያ የሰጡ ሲሆን የክ/ከተማ ጽ/ቤትአመራሮቹ በበኩላቸው የበጀት አመቱን ስራ አፈፃፀም በጋራየሚገመግሙበት መድረክ በመዘጋጀቱ ደስተኛ መሆናቸውንገልፀው በቀጣይም በተሰጣቸው አቅጣጫ መሰረት ተጨባጭየሆነ ውጤት ለማስመዝገብ ተቀናጅተው እንደሚሰሩ ገልፀዋል ፡፡
ከመድረክ ለተነሱ ጥያቄዎችም የውይይት መድረኩን የመሩት የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅና ምክትል ስራ አስኪያጇ ወ/ሮ መቅደስአዱኛ በጋራ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

27/04/2026
03/04/2026
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ሀሉም ኢትዮጵያዊ ያለምንም ልዩነት በጋራ በመነሳት ገንብቶ በማጠናቀቅ የፍሬው ተቋዳሽ ሆኗነል። በቀጣይም ሌሎች መሰል ፕ...
02/04/2026

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተጣለበት ጊዜ አንስቶ ሀሉም ኢትዮጵያዊ ያለምንም ልዩነት በጋራ በመነሳት ገንብቶ በማጠናቀቅ የፍሬው ተቋዳሽ ሆኗነል። በቀጣይም ሌሎች መሰል ፕሮጀክቶችን በተጠናከረ አንድነት መገንባት እንደምንቺል ትልቅ ማሳያ ነው።
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትናንትና ዛሬ

ዜና ሹመትየካቲት 19/2018ዓ.ምወ/ሮ መቅደስ አዱኛ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ  ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ...
26/02/2026

ዜና ሹመት
የካቲት 19/2018ዓ.ም
ወ/ሮ መቅደስ አዱኛ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ምክትል ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙ።
በእለቱም ከቀድሞዋ ም/ስራ አስኪያጅ ወ/ሪት አንቺነሽ ተስፋዬ ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል ። ወ/ሮ መቅደስን በጸ/ቤታችን ስም እንኳን ደህና መጡ ለማለት እንወዳለን።

የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አመራርና ባለሙያዎች ከክ/ከተማ የህዳሴ  ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በመሆን የቀድሞ የጽ/ቤቱን ምክትል ስራ አስኪያጅ የሽኝት መርሃ ግብር አዘጋጁ።የሽኝት መርሃግብሩን በንግግር ...
26/02/2026

የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አመራርና ባለሙያዎች ከክ/ከተማ የህዳሴ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በመሆን የቀድሞ የጽ/ቤቱን ምክትል ስራ አስኪያጅ የሽኝት መርሃ ግብር አዘጋጁ።
የሽኝት መርሃግብሩን በንግግር የከፈቱት የጽ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ንዒመተላህ ከበደ የቀድሞ የጽ/ቤታችን ም/ስራ አስኪያጅ የነበሩትና አሁን የቦሌ ክፍለ ከተማ ምክትል ስራአስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሪት አንቺነሽ ተስፋዬ በስራ ሂደት ስለነበራቸው የአብሮነት ቆይታ አመስግነው አሁን የተሰጣቸውን ኃላፊነትም በብቃት እንደሚወጡና ብቃት ያላቸው አመራር እንደሆኑ ገልፀዋል። ከክ/ከተማና ከማዕከል የባለሙያ ተወካዮችም በስራ በቆዩበት ወቅት ስለነበራቸው መልካም ግንኙነት አመስግነው መልካም የስራ ዘመን እንዲገጥማቸው ምኞታቸውን በመግለፅ የሽኝትና የምስጋና መርሃ ግብሩ ተጠናቋል።

06/02/2026

የከተማችንን ጐስቋላ ገፅታ በመቀየር ውብ፣ ፅዱ እና አረንጓዴ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለጐብኝዎች ሳቢና አለማቀፍ ተወዳዳሪ እንድትሆን በ24/7 የስራ መርሀ ግብር ሰርተን ውጤት ያስመዘገብንበት ነው ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ


Address

Mayor Office
Addis Ababa
1000

Telephone

+251111110152

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Grand Ethiopian Renaissance Dam,Addis Ababa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Grand Ethiopian Renaissance Dam,Addis Ababa:

Shortcuts

Share