Prosperity Party Arada Woreda 02 Branch - ብልፅግና

Prosperity Party Arada Woreda 02 Branch - ብልፅግና የብልጽግና ፓርቲ መርህዎች ፣እሴቶች፣ ራዕይ ፣ስራዎችና ቱርፋቶች ለወረዳችን የፓርቲ ደጋፊዎች ብሎም ለአጠቃላይ ማህበረሰቡ ይቀርቡበታል

"የመረጃ እና የትርክት የበላይነትን መጎናፀፍ ዋና ስትራቴጂካዊ ግባችን ነው!"በብልፅግና ፓርቲ የአራዳ ቅ/ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ በከ8ቱም ወረዳዎች የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች ...
05/09/2026

"የመረጃ እና የትርክት የበላይነትን መጎናፀፍ ዋና ስትራቴጂካዊ ግባችን ነው!"

በብልፅግና ፓርቲ የአራዳ ቅ/ፅ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ በከ8ቱም ወረዳዎች የሚገኙ የዘርፉ አመራሮች እና ከበጎ ማህበረሰብ አንቂዎች የዘርፉን የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በውይይት አዳብረዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የአራዳ ቅ/ፅ/ቤት ተወካይ ኃላፊና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደቻሳ ጆቴ በመድረኩ እንዳስገነዘቡት በበጀት ዓመቱ በሀሳብ ልህቀት፣ በተጨባጭ ስኬት የገዘፈውን ብልፅግና ፓርቲን፣ በሁለንተናዊ ዕድገት ላይ የምትገኘውን ኢትዮጵያን እና በፈጣን ለውጥ ላይ የምትገኘውን ክፍለ ከተማችን ብሎም አዲስ አበባን የሚመጥኑ የህዝብ ግንኙነት እና የሚዲያ ስራዎችን ለማከናወን ሁሉንም አቅሞች በማቀናጀት ብርቱ ርብርብ ይደረጋል።

አርቆ ማለም፣ አስፍቶ ማቀድ፣ አልቆ መተግበር እና የላቁ ድሎችን ማስመዝገብ የብልፅግና ፓርቲ መለያ መሆኑን የገለፁት አቶ ደቻሳ ዘርፉም አንድ ዕቅድ፣ አንድ ምዘና፣ አንድ ሪፖርት በሚል የተልዕኮ ስምሪት የተናበበና የተቀናጀ እንቅስቃሴ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።

የመረጃና የትርክት የበላይነትን መጎናፀፍ የዘርፉ ዋና ስትራቴጂካዊ ግብ መሆኑን የጠቆሙት በሰው ሀይል፣ በአሰራር እና በግብዓት የተቋም ግንባታ ስራዎችን በማላቅ ምርጥ ተሞክሮዎችን ማስፋት እንደሚገባ የገለፁት በልጽግና ፓርቲ የአራዳ ቅ/ጽ/ቤት የህዝብ ግኑኝነትና ሚዲያ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሪ ት ቤተልሄም ትደሩ የህዝባችንን የአብሮነት እሴት የሚያጠናክሩ፣ ተጠቃሚነትን የሚያጎለብቱ፣ ስኬቶቻችንን የሚያሰፉ፣ የፓርቲያችንን እና የመንግስትን ቅቡልነት የሚያሳድጉ የህዝብ ግንኙነት እና የሚዲያ ስራዎችን ከፍ ማድረግ እንደሚገባ በአፅንዖት ገልፀዋል።

ክፍለ ከተማችን ብሎም ከተማችን አዲስ አበባ በፈጣን ለውጥ ላይ የምትገኝ ፣ አዳጊ የህዝብ ፍላጎት ፣ ለቴክኖሎጂ የቀረበ ህዝብ ያላት ዓለም አቀፍ መዲና መሆኗን ታሳቢ ያደረጉ የዘርፉ ግቦች የቀረቡ ሲሆን የበሰለ ውይይትም ተደርጎባቸዋል።

ነባራዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገ ቁርጠኝነትን በመላበስ የዘርፉን ስትራቴጅካዊ ግቦች አልቆ ለመፈፀም ሁሉንም የሚዲያ አማራጮች በመጠቀም፣ ሁሉንም አቅሞች በማስተባበር ቅንጅታዊ ርብርብ እንደሚደረግ ተመላክቷል።

በማጠቃለያም የዕቅድ ግቦች ላይ የተመሠረተ አፈጻጸም በKPI መመዘኛ ከወረዳ ዘርፍ አመራሮች ጋር በመፈራረም የዕቅድ ዉይይቱ መድረክ ተጠናቋል።




05/09/2026

የምንረዳበት ጊዜ ቅርብ ነው!!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)




ብሩህ ተስፋን የፈነጠቀው እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠው የቀዳማይ ልጅነት ኘሮግራም! የከተማችን ዕድገት መሰረተ ፅኑ ነው። የብልፅግና ፓርቲ አካታች እሳቤዎች በተግባር እየተተረጎሙባት በ...
04/09/2026

ብሩህ ተስፋን የፈነጠቀው እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ያረጋገጠው የቀዳማይ ልጅነት ኘሮግራም!



የከተማችን ዕድገት መሰረተ ፅኑ ነው። የብልፅግና ፓርቲ አካታች እሳቤዎች በተግባር እየተተረጎሙባት በመሆኑ መዲናችን ዘላቂ ዕድገቷን አስተማማኝ አድርጋለች።

እንደ ሀገር ተግባራዊ የተደረጉ ኢኒሸቲቮችን አልቃ በመፈፀም አዲስ አበባ ተምሳሌትነቷን አስፍታለች።

የከተማችንን ህዝብ ለዘመናት የተከማቹ ውስብስብ ችግሮች ለመፍታትም አዳዲስ ኢኒሸቲቮች ተግባራዊ በመሆናቸው ተጨባጭ ውጤቶች መመዝገብ ጀምረዋል።

አዲስ አበባን ህፃናት ቦርቀው የሚያድጉባት የአፍሪካ ተምሳሌታዊት መዲና ለማድረግ በክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሀሳብ አመንጭነት ወደ ተግባር የገባው የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራምም የታለመለትን ዓላማ ማሳካት ጀምሯል።

ነፍሰ ጡር እናቶች በመኖሪያ ቤታቸው ጭምር ተገቢውን የህክምና ክትትል እንዲያገኙ ምቹ ሁኔታ የፈጠረው ኢኒሸቲቩ የተመጣጠኑ ምግቦችን እንዲያገኙም አስችሏል።

ለህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ብቻ ሳይሆን ለኑሮ ምቹ አካባቢ መፍጠር እንደሚገ በከተማ አስተዳደሩ በተያዘው ፅኑ እምነት የከተማችን ልማት የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን ታሳቢ እንዲያደርግ ብርቱ ርብርብ እየተደረገ ነው።

አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ ለማድረግ የተከናወኑ ሰው ተኮር ልማቶች ጤናው የተጠበቀ አምራች ዜጋ ለማፍራት ወሳኝ ሚና አላቸው።

የህፃናት መጫዎቻዎች፣ የህፃናት መዋያዎች ፣ የህፃናት መቦረቂያ ፓርኮች እና ሌሎችም ለህፃናት ጤናማ ዕድገት ምቹ ሁኔታ የፈጠሩ መሰረተ ልማቶች የከተማችንን ተምሳሌትነት አስፍተዋል:

መዲናችን አዲስ አበባ ከ 3 ዓመት በፊት 11 የህፃናት ማቆያዎች እና 20 የህፃናት መጫዎቻዎች ብቻ እንደነበሯት መረጃዎች ያመለክታሉ።

በሁለንተናዊ መልኩ አንፀባራቂ ዕድገት እያስመዘገበች የምትገኘው አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ የህፃናት ማቆያዎችን ቁጥር 1ሺህ 100 አድርሳለች፤ የህፃናት መጫዎቻዎችን ደግሞ 5 ሺህ በማድረስ የህፃናትን አስተዳደግ አዘምናለች።

መዲናችን ለህፃናትም ሆነ ለሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች እየፈነጠቀች የምትገኘው ብሩህ ተስፋ እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ህዝባችን የሚመሰክረው ዓለም ያደነቀው ስኬት ነው።

በቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል፣ UNICEF ፣ UNESCO እና በሌሎችም አጋር ተቋማት ለክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ የተሰጠው እውቅናም የኢኒሸቲቩ ውጤታማነት አንዱ ማሳያ ነው።

በዓለም አቀፉ Act For Early Years ኢኒሼቲቭ ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ “የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን” እውቅና ማግኘታቸው ተጠናክሮ የቀጠለው የከተማችን ተምሳሌታዊ ጉዞ ነፀብራቅ ነው።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት




የህዝባችንን የኑሮ ጫና ማቃለል ከቃል በላይ የተገበረ የብልጽግና ዕሴት!ሀገራችን ኢትዮጵያ በለውጡ ማታ ከጀመረችው ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መካከል ዋነኛውና ትልቁ ትኩረት የዜጎችን እለታዊ ...
04/09/2026

የህዝባችንን የኑሮ ጫና ማቃለል ከቃል በላይ የተገበረ የብልጽግና ዕሴት!

ሀገራችን ኢትዮጵያ በለውጡ ማታ ከጀመረችው ሁለንተናዊ የብልጽግና ጉዞ መካከል ዋነኛውና ትልቁ ትኩረት የዜጎችን እለታዊ የኑሮ ፈተና መጋፈጥና ማቃለል ነው። ብልጽግና ፓርቲ ሰውን ማዕከል ያደረገ የፖለቲካና የኢኮኖሚ እሳቤን በመከተል፣ የህዝባችንን የዕለት ተዕለት ኑሮ ለማሻሻልና በተለይም በበዓላት ወቅት የሚፈጠረውን የዋጋ ንረትና የምርት እጥረት ለመቅረፍ ዘመናዊና የተሻገሩ አሰራሮችን በቁርጠኝነት እየተገበረ ይገኛል።

በዓላት የደስታ፣ የመተሳሰብና የፍቅር ማዕድ የሚጋሩባቸው ልዩ ወቅቶች እንደመሆናቸው መጠን፣ በማህበረሰቡ ዘንድ ሰፊ የምርት ፍላጎት ይፈጠራል። ይህንን ፍላጎት ከግምት ውስጥ በማስገባት ፓርቲያችን መሪነቱን ለያዘው መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት፣ በበዓላት ወቅት የምርት እጥረት እንዳይከሰትና አርሶ አደሩና ደንበኛው በቀጥታ የሚገናኙበት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል።

የእሁድና የሸማቾች ገበያዎችን ማስፋፋት አላስፈላጊ ደላሎችንና ደላላ ወለድ የዋጋ ጭማሪዎችን በማስቀረት፣ አምራቹን ከሸማቹ በቀጥታ የሚያገናኙ የእሁድ ገበያዎችና የበዓል ማዕከላት በስፋት እንዲዘጋጁ ተደርጓል። የመሰረታዊ እቃዎች በቂ አቅርቦት እንደ ዘይት፣ ስኳር፣ ዱቄትና የጓሮ አትክልት ያሉ መሰረታዊ የፍጆታ እቃዎች በበቂ መጠንና በቅናሽ ዋጋ ለማህበረሰቡ እንዲቀርቡ የማከፋፈያ መስመሮች ተዘርግተዋል።

የአምራችነት አቅምን ማሳደግ በገበያ ላይ የሚታየውን የእንስሳት፣ የወተት፣ የዶሮና የእንቁላል ፍላጎት በዘላቂነት ለመመለስ በተጀመረው ሀገራዊ የሌማት ትሩፋት ንቅናቄ የበዓላት ገበያ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲሸፈን ተደርጓል።

የህብረት ስራ ማህበራትን ማጠናከር የሸማቾች ህብረት ሥራ ማህበራት የገበያ ማረጋጋት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የፋይናንስና የሎጂስቲክስ ድጋፍ በማድረግ ማህበረሰቡ በቅናሽ ዋጋ ምርቶችን እንዲያገኝ ተደርጓል።

ብልጽግና ማለት አዎንታዊ ለውጦችን ለህዝብ ቅርብ ማድረግ፣ የዜጎችን እንግልት መቀነስና የጋራ ደስታን ማረጋገጥ ነው። የህዝባችንን የኑሮ ጫና ለማቃለል የተጀመሩት ገበያን የማረጋጋትና የአቅርቦት ማሳደግ ስራዎች በበዓላት ወቅት ብቻ የሚገደቡ ሳይሆኑ፣ ዘላቂ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ተጠናክረው ይጥላሉ።



በዚህ አምስት ዓመት በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ ማምጣት የሚጠበቅብን እመርታ እንቅልፍ የሚያስተኛ አይደለም፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
04/09/2026

በዚህ አምስት ዓመት በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ ማምጣት የሚጠበቅብን እመርታ እንቅልፍ የሚያስተኛ አይደለም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)

ዓለም ዕውቀና የቸረው የአዲስ አበባ የትውልድ ግንባታ ተግባር ዛሬን በሰው ተኮር ተግባራቶቿ የብዙዎች የከተማው ነዋሪዎቿ እንባ ያበሰችው አዲስ አበባ፤ ነገዋን ብሩህ ለማድረግ ደግሞ በትውልድ ...
04/09/2026

ዓለም ዕውቀና የቸረው የአዲስ አበባ የትውልድ ግንባታ ተግባር

ዛሬን በሰው ተኮር ተግባራቶቿ የብዙዎች የከተማው ነዋሪዎቿ እንባ ያበሰችው አዲስ አበባ፤ ነገዋን ብሩህ ለማድረግ ደግሞ በትውልድ ግንባታ ላይ ያልተቆጠቡ ስራዎችን እያከናወነች ነው፡፡

የዛሬ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢ ናቸው በሚል መርህ ባለፉት ሶስት ዓመታት አዲስ አበባን ህጻናትን ለማሳደግ የምትመች ምርጧ የአፍሪካ ከተማ ለማድረግ የተሰራው ስራ እና የተገኘው ውጤት ፈርጀ ብዙ ነው፡፡

የሰው ልጅ አእምሮ በህይወት ዘመኑ ከሚያሳየው አጠቃላይ እድገት ውስጥ እጅግ ፈጣኑ እና ወሳኙ ክፍል በመጀመሪያዎቹ የልጅነት ዓመታት ውስጥ የሚከናወን ነው፡፡

የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የህፃናት እድገት ማዕከል እና የአለም ጤና ድርጅት ሳይንሳዊ መረጃ እንደሚያሳየው የህፃናት የአዕምሮ ዕድገት አስከ ሶስት ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ 80 በመቶ እንደሚጠናቀቅ ሲያረጋግጥ፤ ይህ እድገት ከ5- 6 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ደግሞ 90 በመቶ ላይ እንደሚደርስ ሳይንሳዊ ጥናቱ ይፋ አድርጓል፡፡

ህፃናት በዚህ ጊዜ ውስጥ የሚያገኙት እንክብካቤ፣ ፍቅር፣ ጥሩ አመጋገብ እና ማነቃቂያ (ጨዋታ፣ ንባብ፣ የንግግር ችሎታ) የወደፊት አእምሯዊ ብቃታቸውን ይወስናል።

በመሆኑም በቀዳማይ ልጅነት መረኃ ግብር ላይ መስራት ለወደፊት ትውልድ ግንባታ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የተረዳው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመሰጠት በለፉት ዓመታት ውጤታማ ስራዎችን አከናውኗል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ በቀዳማይ ልጅነት ልማት መርሃ ግብሩ የህፃናት የተቀናጀ የጤና እና የክትትል አገልግሎት በተጨማሪ በህፃናት ማቆያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን በመገንባት ረገድ ውጤታማ ስራ ተሰርቷል፡፡

ከሶስት ዓመት በፊት በአዲስ አበባ ያሉ የህፃናት ማቆያዎች 11 ብቻ ነበሩ ዛሬ 1100 ደርሰዋል፤ 20 የነበሩት የህፃናት መጨወቻዎች አሁን 5 ሺህ ደርሰዋል። ይህ መዋቅራዊ ለውጥ ነው፡፡
ቤተሰቦቻቸው መክፈል ለሚችሉ ህፃናት ብቻ ተትቶ የነበረው የቅድመ መደበኛ ትምህርት አሁን በአዲስ አበባ ለሁሉም ሆኗል፤ ልጆቻቸው እስኪያድጉ ከስራ ገበታ እርቀው ለኢኮኖሚ ችግር ይጋለጡ የነበሩ እናቶች ዛሬ ላይ ግን በተዘጋጀው የህዝብ የህፃናት ማቆያ ልጆቻቸውን በማስቀመጥ አምራች ወደሚያደርጋቸው የስራ ገበታ ላይ መሰማራት እንዲችሉ አድርጓል፡፡

በአጠቃላይ በዚህ መራኃ-ግብር በአዲስ አበባ 1.3 ሚሊዮን ህፃናት በመረኃ ግብሩ ታቅፈው ተጠቃሚ እየሆኑ ሲሆን ፕሮግራሙ በአጭር ጊዜ ውስጥ እምርታዊ ለውጥ እያስመዘገባ ይገኛል፡፡

ዋና መቀመጫው በእንግሊዝ ለንድ የደረገው Act For Early Years ኢኒሼቲቭ በፈረንጆቹ 2023 በይፋ ስራውን የጀመረ ሲሆን መሰረታዊ እንክብካቤ እና የቅድመ መደበኛ ትምህርት የተነፈጉ ከ350 ሚሊዮን በዓለም ላይ የሚገኙ ህፃናትን ችግር እልባት ለመስጠት የተመሰረት ኢንሼቲቭ ነው፡፡

ኢንሼቲቩ በዋናነት የመንግስታት እና ፖሊሲ አውጪዎችን ግንዛቤ በመለወጥ ከጽንሰት እስከ ስድስት ዓመት እድሜ ያላቸው ህፃናት ጉዳይ ትኩረት እዲሰጥ ማድረግ ሲሆን ፕሮግራሙ በበርካታ ሀገራት ተግባራዊ ሲደረግ በእነዚህ ዓመታት ውስጥም አዲስ አበባ ውጤታማ ስራዎችን በመስራት ግንባር ቀደም ከተማ ስትባል፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤም በኢንሼቲቩ"የቅድመ ልጅነት እድገት ሻምፒዮን" ማዕረግን ተቀዳጅተዋል፡፡

ይህን እውቅና የተሰጠው ከቀድሞው የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚኒስትር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ጎርደን ብራውን በኩል የኢኒሼቲቭ አጋሮች በመወከል ሲሆን፣ UNICEF እና UNESCOን ጨምሮ ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመተባበር የተሰጠ ነው።





04/09/2026

"ኢትዮጵያን ወደሚመጥናት የታላላቅ ዓለም ሥልጣኔዎች ጎራ ለማሰለፍ የሚያስችለን የ25 ዓመት ዐቢይ (Grand) ስትራቴጂ!"

​ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የመደመር መንግሥት ኢትዮጵያን ወደ ታላቅ የሥልጣኔ ማዕከልነት ለማሸጋገር ስላዘጋጀው የ25 ዓመት ዐቢይ (Grand) ስትራቴጂ ምን ብለዉ ነበር?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)




ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ አዲስ አበባ- የዓለም አቀፍ ሽልማቶች ሚስጥርአዲስ አበባ ያሸነፈቻቸው የዓለም አቀፍ ሽልማት ዋነኛ ሚስጥር የሚገኘው ከመሠረተ ልማትና ውጤታማ  ስራዎች ብቻ ሳይ...
03/09/2026

ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ አዲስ አበባ- የዓለም አቀፍ ሽልማቶች ሚስጥር

አዲስ አበባ ያሸነፈቻቸው የዓለም አቀፍ ሽልማት ዋነኛ ሚስጥር የሚገኘው ከመሠረተ ልማትና ውጤታማ ስራዎች ብቻ ሳይሆን፣ ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ ለማድረግ አጠቃላይ የሁለንተናዊ ብልፅግና ጉዞ ማዕከል በሆነው የሰብዓዊ ልማት እና ትውልድን በማነጽ ላይ በሰራችው ስር ነቀል ለውጥ ጭምር ነው።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ “የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም”ን በብቃት በመምራታቸው በዓለም አቀፉ “አክት ፎር ኤርሊ ይርስ” (Act For Early Years) ኢኒሼቲቭ “የቅድመ ልጅነት ዕድገት ሻምፒዮን” ተብለው ተሸልመዋል። ይህ ትልቅ እውቅና ከተማዋን ለህፃናት የምትመች ከተማ እና ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ የአፍሪካ መዲና ለማድረግ የሰነቀችውን ራዕይ የሚያንፀባርቅ፣ እንዲሁም ለትውልድ ግንባታ የሚደረገው ኢንቨስትመንት ያመጣውን ለውጥ በጉልህ የሚያሳይ ነው።

የዚህ ስኬት እና የከተማዋ አስደናቂ እድገት ማሳያ የሆነው ከቁጥር በላይ የሆነው መረጃ የመጫወቻ ስፍራዎች እና የሕፃናት ማቆያዎች መስፋፋት ነው። 20 የመጫወቻ ስፍራዎች ብቻ የተነሳው የከተማዋ አስተዳደር በሦስት ዓመታት ውስጥ ብቻ 5 ሺህ 500 ማድረስ ችሏል። በሌላ በኩል 5 ሺህ 3 የሚሆኑት የልጆችን የዕድገት ደረጃና ሥርዓት ታሳቢ ያደረጉ የመጫወቻ ቦታዎችም ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። በተጨማሪም የሕዝብ የሕፃናት ማቆያዎች ከ11 ብቻ ተነስተው በአሁኑ ሰዓት 1 ሺህ 100 ደርሰዋል። ይህ በተለያዩ ሞዴሎች የተደራጀው የማቆያ ቁጥር በጥቅሉ 1 ሺህ 155 የደረሰ ሲሆን፣ 27 ሺህ 302 ሕፃናት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሆነዋል።

ይህ ስኬታማ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም በመዲናችን የሚገኙ 1.3 ሚሊዮን ገደማ ሕፃናትን፣ በተለይም 330 ሺህ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ታዳጊዎች ተደራሽ ለማድረግ ያለሙ አምስት አንኳር ጉዳዮችን ያካተተ ነው።

አዲስ አበባ ዛሬ አለምን ያስገረመችው እና የትኩረት ማዕከል የሆነችው በውብ የኮሪደር ልማቷ፣ በወንዝ ዳርቻዎቿ ውበት፣ ወይም በሌሎች ፕሮጀክቶቿ ብቻ አይደለም። ብሩህ አእምሮ ያለው ጤናማ ትውልድ በማፍራት፣ ህፃናትን ለማሳደግ ምርጧ ከተማ መሆኗን በተግባር በማሳየትና የዜጎችን በተለይም የሕፃናትን ሕይወት በሚቀይር የሰብዓዊ ልማት ሥራዋ ጭምር ነው። ይህ በሰብዓዊነት እና በትውልድ ላይ የተደረገው ጥልቅ ኢንቨስትመንት የመንግስትን የመደመር እሳቤ መሬት ያወረደ፣ ዜጎችን በአንድነት አስተባብሮ ከተማዋን እውነተኛ የብልፅግና ተምሳሌት ያደረጋት ሲሆን፣ ተደጋጋሚ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን እንድትቀዳጅ ያስቻላት ዋነኛ ሚስጥርም ይኸው ነው።




"ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ!" በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ  የሴክተር ተቋማት ልዩ ወረዳ አመራሮች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በመወያየት የጋራ...
03/09/2026

"ጠንካራ አደረጃጀት ለጠንካራ ፓርቲ!"

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ የሴክተር ተቋማት ልዩ ወረዳ አመራሮች የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በመወያየት የጋራ ግንዛቤ ፈጥረዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ጉሉማ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት ብልፅግና በእሳቤ፣ በአደረጃጀት እንዲሁም በሰው ሀይል ግዙፍና ጠንካራ ፓርቲ መሆኑን አመላክተዋል።

ጠንካራ ፓርቲ ለጠንካራ መንግስት የሚለውን መርህ በተግባር ለመተርጎም ተቋማዊ ጥንካሬን ማጠናከር እንደሚገባ ያስረዱት አቶ ሙሉጌታ ለአባለት የተግባር ስምሪት በመስጠት፣ በተከታታይ ድጋፍና ክትትል ተቀራራቢ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ለመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ትልቅ አቅም የሚፈጥረው የልዩ ወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት አፈፃፀሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን የጠቀሱት አቶ ሙሉጌታ ፓርቲያችን ከያዛቸው ሰፊ ተልዕኮዎች አንፃር ብዙ እንደሚጠበቅበት አስረድተዋል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት የልዩ ወረዳ ሴክተር ተቋማት ክትትል ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብዱልሃዲ ረሺድ በበኩላቸው ውይይቱ ብልፅግና ፓርቲ መንትያ ግቦችን ካሳካበት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እና ከታሪካዊው ሀገራዊ ምክክር ማግስት መካሄዱ ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀው፤ 2019 በጀት ዓመት ፓርቲያችን ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር የሚተረጉምበት በመሆኑ አደረጃጀቱ ተልዕኮውን የሚመጥን ርብርብ እንደሚያደርግ አስገንዝበዋል።

አደረጃጀትን እና አሰራርን በማዘመን፣ ጥራት ያለው የአባላትና የአመራር ልማት ተግባራዊ በማድረግ፣ የፓርቲያችንን ተቋማዊ ጥንካሬ ማረጋገጥ የበጀት ዓመቱ ስትራቴጅካዊ ግብ መሆኑን አቶ አብዱላሂድ ገልፀዋል።

በፓርቲያችን መመሪያ መሰረት ጥራት ያለው አባል ምልመላ፣ ተኪ አመራሮችን ማፍራት፣ ግንባር ቀደሞችን ማበራከት በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የጠቆሙት አቶ አብዱላሂድ የፓርቲያችንን አቅም ለተሳለጠ የመንግስት አገልግሎት ለማዋል ቅንጅታዊ ርብርብን ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በውይይቱ ላይ የከተማ ፣ የሴክተር ተቋማት፣ የልዩ ወረዳ፣ የብልፅግና ህብረት እና የብልፅግና ቤተሰብ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የተጠናቀቀውን በጀት ዓመት ስኬት የሚያስቀጥሉ፣ ጉድለቶችን የሚሞሉ ሀሳቦችን በመስጠት የ 2019 በጀት ዓመት ዕቅድን አዳብረውታል።

በውይይቱ መጨረሻም የ2019 ዋና ዋና ተግባራትን በተቀናጀ የአመራር ስምሪት አልቆ ለመፈፀም፣ የሁሉም ልዩ ወረዳ ተወካዮች ከከተማ አመራሮች ጋር የፊርማ ስነ ስርዓት አከናውነዋል።


በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት




የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት  አካሂዷል።​ መድረኩ ላይ የከተማው፣ የሁሉም ክፍለ ከተማና የወረዳዎች የዘርፉ አመራሮች እንዲ...
03/09/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ቤት የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት አካሂዷል።

​ መድረኩ ላይ የከተማው፣ የሁሉም ክፍለ ከተማና የወረዳዎች የዘርፉ አመራሮች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

​የአዲስ አበባ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ቅ/ጽ/ ቤት ኃላፊ ወ/ሮ የሺ ወልዴ፤ “በጎነትና እህትማማችነት የሴቶችን ማህበራዊና ፖለቲካዊ አቅም በማጎልበት ረገድ ትልቅ መሠረት ነወ” ሲሉ ገልጸዋል።

​ፓርቲው ሴት አመራሮችን በብቃት ለማዘጋጀትና ለማብቃት በርካታ አወንታዊ ተግባራትን ማከናወኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ በተግባር ያሳዩት አርአያነት ያለው የአመራር ጥበብና ቁርጠኝነት፣ ሴቶች ወደፊት እንዲመጡና ሁለንተናዊ ተሳትፎአቸው እንዲያድግ ትልቅ ብርታትና ድምቀት መሆኑን አብራርተዋል።

በመድረኩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት ​የቦሌ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ምክትል እና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ማስተዋል ፋንታሁን “የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ሲረጋገጥ የመላው ህብረተሰብ እድገት ይፋጥናል” ብለዋል።

​ፓርቲው ለሴቶች እያደረገ ያለው አጠቃላይ ድጋፍና የሚሰጠው ትኩረት ከፍተኛ መሆኑን ያመላከቱት ወ/ሮ ማስተዋል፤ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ የሚያሳዩት ጠንካራና አቅጣጫ ጠቋሚ አመራር ለሌሎች ሴት አመራሮች የመንፈስ ብርታትና ታላቅ የቁርጠኝነት ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል።

​ሴቶች በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዘርፎች ያላቸውን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ ለማረጋገጥ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በትጋት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።





Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity Party Arada Woreda 02 Branch - ብልፅግና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share