03/06/2026
ከጓዳ ወደ ዓለም ገበያ፡
ሀገር በቀል ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪና ተመራጭ ሆነው እንዲቀጥሉ የሚከተሉትን 4 ወሳኝ የጥራት ማረጋገጫ ሂደቶቸን/መስፈርቶች ማሟላት ያስፈልጋል፡፡
1.የጥሬ ዕቃ ጥራት (Raw Materials) ፡ የሚጠቀሙባቸው ጥራጥሬዎችና ቅመማ ቅመሞች ሙሉ በሙሉ ንፁህ፣ ከፈንገስ፣ ከተባይ እና ከባዕድ ነገሮች የፀዱ መሆናቸውም ማረጋገጥ፣
2.አካላዊና ኬሚካላዊ መመዘኛዎች (Chemical & Physical requirements) ፡ ምርቱ ሳይበላሽ ለረጅም ጊዜ እንዲቀመጥ የእርጥበት መጠኑ (Moisture Content) በደረጃው መሰረት መሆን፣
3.የንፅህና ደረጃ (Microbiological Safety) ፡ ምርቱ በሚዘጋጅበት ወቅት ምንም ዓይነት ለጤና ጠንቅ የሆኑ ባክቴሪያዎች (እንደ Salmonella) እንዳይፈጠሩ የምርት አካባቢውና ማሽነሪዎቹ ንፁህ መሆን፣
4.በማሸጊያ ላይ የሚገለፁ መረጃዎች (Packaging & Labeling)፡ በኢትዮጵያ ደረጃ መሠረት በማሸጊያው ላይ የምርቱ ስም፣ የአምራች አድራሻ፣ የተመረተበትና የሚያበቃበት ቀን (Expiry Date) ፣ የግብዓቶች ዝርዝር (Ingredients) እና የተጣራ ክብደት በግልፅ መቀመጡን ማረጋገጥ።
📌 እርስዎ በብዛት የሚጠቀሙበት እና የሚወዱት የታሸገ የሀገር በቀል ምርት (ብራንድ) የትኛው ነው? አምራቾቹን በኮሜንት ላይ ‘Tag’ በማድረግ የጥራት ማረጋገጫ እንዲያገኙ መረጃውን እናጋራቸው!
የተከበራችሁ የሀገር በቀል ምርቶች አምራቾች፤
ባህላዊ እውቀታችሁን ከዘመናዊ የጥራት አሰራር ሥርዓት ጋር በማጣመር ምርቶቻችሁን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲሆኑ በጋራ እንስራ!
ወደ ላቀ ብቃት የሚያደርስዎ! የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት
የኢተምድ ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች፡
https://linktr.ee/infoecae2003