Ethiopian Conformity Assessment Enterprise -ECAE

Ethiopian Conformity Assessment Enterprise -ECAE ECAE is the acronym for “Ethiopian Conformity Assessment Enterprise”. In February 2011, ECAE was

የኢተምድ ሰራተኞችና የስራ መሪዎች በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጉብኝት አደረጉ።ነሐሴ 30/2018 ዓ/ምአዲስ አበባ (ኢተምድ)==================== የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅ...
05/09/2026

የኢተምድ ሰራተኞችና የስራ መሪዎች በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ጉብኝት አደረጉ።
ነሐሴ 30/2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የስራ መሪዎችና ሰራተኞች በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ በመገኘት በፓርኩ ውስጥ በሚካሄዱ የላቁ የአመራረት ሂደቶች፣ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም እና የጥራት አጠባበቅ ስርዓቶች ላይ ያተኮረ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርገዋል።
ጉብኝቱ በሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የሚታዩ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ አሰራሮችን በአካል በመመልከት የአምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፍላጎት መሰረት ያደረገ እና ዘመኑን የዋጀ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለውን የስራ ትብብር ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በጉብኝቱ የቴክኖሎጂ እና የአመራረት ስርዓት በፓርኩ ውስጥ የሚገኙ አለምአቀፍና ሀገር በቀል ኩባንያዎች የሚጠቀሟቸውን ዘመናዊ የምርት ቴክኖሎጂዎች እና አጠቃላይ በጥራት ጉዳይ ላይ ከአምራቾችና የኢንዳስትሪ ፓርኩ የስራ ሃላፊዎች ጋር ውይይትና ጉብኝት ተደርጓል።
የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ በጉብኝቱ ተገኝተው በጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች የአለምአቀፍ ደረጃዎችን እና የጥራት ቁጥጥር መስፈርቶችን ያሟሉ መሆናቸውን የሚረጋገጡበት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አገልግሎቶችና አሰራሮች ላይ ገለፃ አድርገዋል።
የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሀላፊዎች በበኩላቸው መሰል የልምድ ልውውጦች በተቋማት መካከል ያለውን ትስስር የሚያጠናክሩና የቴክኖሎጂ ሽግግርን የሚያፋጥኑ በመሆናቸው ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ኢተምድ ለሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ  የጥራት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።ነሐሴ 29/2018 ዓ/ምአዲስ አበባ (ኢተምድ)============...
04/09/2026

ኢተምድ ለሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የISO 9001:2015 ዓለም አቀፍ የጥራት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ።
ነሐሴ 29/2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
====================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የጥራት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት ሰጠ። ቢሮው የጥራት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት (ISO 9001:2015 Quality Management System) ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን መሟላቱን በተከናወነላት የኦዲት ሂደት ተገምግሞ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ የተሰጠው ሰርተፊኬት ነው፡፡

ሰርቲፊኬቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነብያ መሀመድ፣ የክልሉ የተለያዩ የቢሮ ኃላፊዎች፣ የሰርተፍኬት ባለቤት የሆኑ የሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የስራ ሃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ለሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀገረጽዮን አበበ አስረክበዋል፡፡

በሰርተፍኬቱ ርክክብ ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት፣ ቢሮው ያስመዘገበው ይህ ታሪካዊ ስኬት በክልሉ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ዘመናዊና ጥራት ያለው የአገልግሎት አሰጣጥ ባህልን ለማስፈን የሚደረገውን ጉዞ የሚያፋጥን መሆኑን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ነብያ መሀመድ የእንኳን ደስአላችሁ እና የቀጣይ የቱክረት አቅጣጫዎችን መልክት አስተላልፈዋል፡፡

በሰርተፍኬቱ ርክክብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት በማስተላለፍ በዓለም አቀፍ የጥራት ስራ አመራር ስርዓት ሰርተፊኬት (ISO 9001:2015 Quality Management System) ላይ ሰርተፍኬት ማግኘታችሁ የምትሰጡትን አገልግሎት የደንበኞቻችሁን እርካታ ይጨምራል፣በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነታችሁ ያረጋግጣል፣የአሰራር ስርዓታችሁ ቅልጥፍናን ያመጣል፣ስጋትን በመለየት ቅድመ እርምት እርምጃ ለመውሰድ ያስችላል፣ብክነትንና ብክለትን ይቀንሳል እንዲሁም ቀጣይነት ያለው እድገትና መሻሻልን እንደሚያስገኝላቸው አብራርተዋል።

አክለውም ጥራት ቀጣይነት ባለው የተግባር እና የስርፀት ስራዎችን በመስራት ባህል ማድረግ እንደሚገባም የገለፁ ሲሆን የጥራት ስራ አመራር ስርዓቱ ቀጣይነትም ልዩ ቱክረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡

የፕሮግራሙ ታዳሚዎች በሲዳማ ክልል የሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰሩ የሪፎርም ስራዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ ለጤናማ ማህበረሰብ!የምንመገበው ምግብ ጥራትና ደህንነት ለጤናችን መሰረት ነው። በምግብ ዝግጅትና ምርት ሂደት ውስጥ የሚከሰቱ የምግብ ደህንነት አደጋዎች (Food ...
04/09/2026

የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ ለጤናማ ማህበረሰብ!
የምንመገበው ምግብ ጥራትና ደህንነት ለጤናችን መሰረት ነው። በምግብ ዝግጅትና ምርት ሂደት ውስጥ የሚከሰቱ የምግብ ደህንነት አደጋዎች (Food Safety Hazards) በሶስት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላሉ፡
🔹 ፊዚካል (Physical Hazards): በምግብ ውስጥ የማይገቡ ባእድ አካላት (ለምሳሌ፡ ድንጋይ፣ ብረት፣ መስታወት)
🔹 ኬሚካል (Chemical Hazards): የፀረ-ተባይ መድሃኒቶች፣ የጽዳት ኬሚካሎች ወይም ያልተፈቀዱ የኬሚካል ተጨማሪዎች
🔹 ባዮሎጂካል (Biological Hazards): ባክቴሪያዎች፣ ቫይረሶች እና ሌሎች ለጤና ጎጂ የሆኑ ጥቃቅን ህዋሳት

🏢 የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) የምግብ ምርቶችዎን ጥራትና ደህንነት ለመጠበቅ እና በምርት ሂደት ውስጥ የሚከሰቱ የምግብ ደህንነት አደጋዎች አስቀድሞ ለመከላከል የሚከተሉትን አገልግሎቶች ይሠጣል፡፡

🔬 የላቦራቶሪ ፍተሻ አገልግሎት (ISO/IEC 17025):
 በምግብ እና መጠጥ ፍተሻ፣ በማይክሮ ባዮሎጂ፣ በጨረር ፍተሻ ላቦራቶር እና በግብርና እና የግብርና ግብዓት ፍተሻ ላቦራቶር የምግብ ምርቶችን ሳይንሳዊ ይዘትና ደህንነት በዘመናዊ የላቦራቶሪ ቴክኖሎጂ የታገዘ የማረጋገጥ አገልግሎት ይሠጣል፡፡
🔎 የኢንስፔክሽን አገልግሎት ((ISO/IEC 17020):
 የጥራት እና ደህንነት መስፈርቶች መሟላታቸውን የምርት ንድፍን፣ ምርትን፣አገልግሎትን የሥራ ሂደትን ወይም የሥራ ቦታን ከተቀመጠለት መስፈርት/ መመሪያ ወይም ከሙያዊ ምዘና አንፃር መዝኖና ገምግሞ ተስማሚነትን የማረጋገጥ አገልግሎት ይሠጣል፡፡
🔹 የምርት ሰርቲፊኬሽን (ISO/IEC 17065)/ የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬሽን (ISO/IEC 17021)
 ምርቶች የተጠቀሱ ተፈላጊ/ተጠባቂ መስፈርቶችን ማሟላታቸውን ለማሳየት በገለልተኛ በሶስተኛ ወገን የሚሰጥ የምርት ጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት፡፡
 አምራች ድርጅቶች የሚያከናውናቸውን ተግባራት፣ የምርቶች፣ የአገልግሎቶች እና የሥራ ሂደት ከዓለም አቀፍ የሥራ አመራር ሥርዓት ጋር የተጣጣመ ሥርዓት መተግበሩን በመገምገም ተፈላጊ ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ በገለልተኛ ወገን የሚሰጥ የሥራ አመራር ሥርዓት ማረጋገጫ አገልግሎት፡፡

📌 በተቋምዎ ወይም በንግድ ሥራዎ የጥራት ማረጋገጫ ለመውሰድ ከየትኛው አገልግሎት መጀመር ይፈልጋሉ?
📞 ለበለጠ መረጃና አገልግሎት ያግኙን፡

የጽሕፈት ምርቶች የጥራት ፍተሻየኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የጽሕፈት ምርቶች ፍተሻ ላቦራቶሪ፤ የጽሕፈት መገልገያዎች የተጠበቀውን የጥራት፣ የተግባር ብቃት (Performance) እና ...
02/09/2026

የጽሕፈት ምርቶች የጥራት ፍተሻ
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የጽሕፈት ምርቶች ፍተሻ ላቦራቶሪ፤ የጽሕፈት መገልገያዎች የተጠበቀውን የጥራት፣ የተግባር ብቃት (Performance) እና የውጭ ገጽታ (Appearance) መስፈርት ማሟላታቸውንና ለተፈለጉበት ዓላማ ተስማሚ መሆናቸውን በዘመናዊ የላቦራቶሪ መሣሪያዎች የታገዘ የጥራት ፍተሻ አገልግሎት በመስጠት ያረጋግጣል።

🔬 የላቦራቶሪ ፍተሻው ጠቀሜታ፡
✔️ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶች ማሟላታቸውን ያረጋግጣል፡፡
✔️ የምርት ቆይታ እና አስተማማኝነት ያረጋግጣል፡፡
✔️ ለደንበኞች የምርቱን ደህንነት ያረጋግጣል፡፡
✔️ ለአገር ውስጥ ግብይትም ይሁን ለውጪ ገበያ ብቁነት ማረጋገጫ ይሠጣል፡፡
✔️ በንግድ ውድድሮችና ጨረታዎች ቅድሚያ ያሰጣል፡፡
✔️ የምርት አስተማማኝነት፡ የተለያዩ የወረቀት አይነቶች፣ ፋይል ፎልደሮች እና ሌሎች የፅህፈት መሳሪያዎች የሚጠበቅባቸውን አገልግሎት በብቃት እንደሚወጡ ያረጋግጣል፡፡
✔️ የተግባር ብቃት (Performance)፡ እስክሪብቶዎች ሳይቆራረጡና ቀለም ሳይተፉ እንደሚፅፉ፣ ወረቀቶች በአንዱ በኩል የተጻፈ ወይም የታተመባቸው ጽሑፍ በሌላኛው በኩል የመታየት ባህሪን ፍተሻው ያረጋግጣል፡፡

📞 ስለ ጥራት ፍተሻ አገልግሎቶቻችን የበለጠ ለማወቅና ምርቶችዎን ለማስፈተሽ ዛሬውኑ ያግኙን!


ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/infoecae2003

ኢተምድ ለኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ያገኘውን ሰርተፊኬት አስጠብቆ በማቆየቱ በድጋሚ ሰርቲፊኬት ሰጠ፡፡ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)=...
01/09/2026

ኢተምድ ለኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን በጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ያገኘውን ሰርተፊኬት አስጠብቆ በማቆየቱ በድጋሚ ሰርቲፊኬት ሰጠ፡፡
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
=================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት(ኢተምድ) ለኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (ISO 9001:2015) መስፈርቶችን አሟልቶ በመገኘቱና የተሰጠውን ሰርተፊኬት አስጠብቆ በመቆየቱ ድጋሚ ሰርቲፊኬት (Recertification) ሰጥቷል።

ሰርተፍኬቱን የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ ለኮርፖሬሽኑ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ ለተከበሩ ኢንጂነር ኑመሪ ኑራ ያስረከቡ ሲሆን፣ ኮርፖሬሽኑ ከዚህ ቀደም የISO 14001 (የአካባቢ ሥራ አመራር ሥርዓት) እና የISO 45001 (የሥራ ቦታ ጤናና ደህንነት ሥራ አመራር ሥርዓት) ሰርተፍኬቶችን ማግኘቱ ይታወሳል።

በሰርተፊኬት አሰጣጥ ስነ-ስርዓቱ ላይ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ያስተላለፉት የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢንጂነር መዓዛ አበራ፣ ኮርፖሬሽኑ ነባር ሰርተፊኬቱን ማስቀጠሉ፤ የአሠራር ሂደቱንና የደንበኞቹን እርካታ ለማሳደግ በሥራ አመራሩ ዘንድ ያለውን ቁርጠኝነትና ትጋት እንደሚያሳይ ገልጸዋል። አክለውም ኢተምድ ይህንን ስኬት ወደ ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች በማስፋት አብሮ ለመስራት ያለውን ዝግጁነት አረጋግጠውላቸዋል።

የኮርፖሬሽኑ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ የተከበሩ ኢንጂነር ኑመሪ ኑራ በበኩላቸው፤ ለኮርፖሬሽኑ ሥራዎች ተቀባይነትና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሥራ አመራር ሥርዓቶችን መተግበር ወሳኝ መሆኑን በመግለጽ፣ ጥራትን ባህል ለማድረግ የተገኙትን በማስቀጠል ኮርፖሬሽኑ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። አክለውም፣ በግንባታው ዘርፍ ጥራትን ባህል ለማድረግ ከኢተምድ ጋር አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

Second-Round KOICA Project Assessment Started.August 31, 2026Addis Ababa (ECAE)============ =====         The Korea Inte...
31/08/2026

Second-Round KOICA Project Assessment Started.
August 31, 2026
Addis Ababa (ECAE)
============ =====
The Korea International Cooperation Agency (KOICA) Ethiopia Office has conducted a second-round assessment at the Ethiopian Conformity Assessment Enterprise (ECAE) laboratories to evaluate and enhance testing capabilities for agricultural and processed food products.

The evaluation focused specifically on building technical capacity for Genetically Modified Organisms (GMO) and veterinary drug residue analysis testing. The initiative aims to strengthen national standards and ensure the quality and safety of Ethiopia's agricultural exports and domestic food supplies.

As part of the assessment, the KOICA delegation held a discussion with ECAE Director General Engineer Meaza Abera and members of the enterprise's management team to align on technical requirements and strategic goals. This assessment is a key milestone under the broader Ethiopian National Quality Management Capacity Enhancement Project in the Agro Sector, a joint effort designed to modernize testing infrastructure and support economic growth in the country's agricultural sector.

የሥር - መንስዔ ትንተና ወይም የሥረ-መሠረት መንስዔ ትንተና     (Root Cause Analysis - RCA)የሥር - መንስዔ ትንተና (Root Cause Analysis) በአንድ ድርጅት ወይ...
31/08/2026

የሥር - መንስዔ ትንተና ወይም የሥረ-መሠረት መንስዔ ትንተና
(Root Cause Analysis - RCA)
የሥር - መንስዔ ትንተና (Root Cause Analysis) በአንድ ድርጅት ወይም የሥራ ሂደት ውስጥ ለተከሰተ ችግር ዋናውንና መሠረታዊውን ምክንያት ፈልጎ ለማግኘት የሚረዳ ስልታዊ የችግር መፍቻ ዘዴ ነው።

የተከሰተውን ችግር ለመቅረፍ መሠረታዊ መንስኤው ላይ ሳይሆን በሚታየው ውጫዊ ምልክት (Symptom) ላይ ብቻ ማተኮር፣ ለችግሩ ጊዜያዊ «የእሳት ማጥፊያ» መፍትሔ እንደ መስጠት ነው። ይህም ምልክቱን ለጊዜው ቢያጠፋውም፣ ችግሩ በሌላ መልክ ተደጋግሞ እየተከሰተ የተቋሙን ሀብትና ጊዜ ያባክናል።

📌 የRCA 4 ዋና ዋና ዓላማዎች
1. ምን እንደተከሰተ ማወቅ: ችግሩን በትክክል መለየትና መረዳት
2. እንዴት እንደተከሰተ መረዳት: የክስተቶችን ቅደም-ተከተል ማጥናት
3. ለምን እንደተከሰተ ማረጋገጥ: መሠረታዊውን ምክንያት (Root Cause) ማግኘት
4. የመከላከያ እርምጃ መውሰድ: ችግሩ እንደገና እንዳይከሰት በዘላቂነት ማስቀረት

ችግሩን በትክክል መረዳት የችግሩ ግማሽ መፍትሔ ነው። ተቋማት ችግሮችን በጥልቀት መተንተንና ሳይንሳዊ መፍትሔ ማመንጨት ሲጀምሩ፣ ከችግር አዙሪት ወጥተው ወደ አስተማማኝ ስኬት ያመራሉ። RCA ውጤታማ የሥራ አመራር ሥርዓት ለመገንባትና ለማስቀጠል መሠረታዊው ምሰሶ ነው።
በሥራ አመራር ሥርዓት ውስጥ RCA የሚከተሉት ዋና ዋና ሚናዎች አሉት፡

1. ቀጣይነት ያለው መሻሻል (Continual Improvement)
ለምሳሌ ISO 9001 የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (Quality Management System) በቋሚነት መሻሻልን ይጠይቃል። የተከሰቱ የጥራት መጓደል ችግሮችን በምልክታቸው (Symptom) ላይ ብቻ ተመስርቶ ማከም የጥራት ደረጃን አይጠብቅም። RCA በመጠቀም የችግሩን መነሻ ማስወገድ ድርጅቱ በየጊዜው ጥራቱን እያሻሻለ እንዲሄድ ያስችለዋል።

2. የማረሚያና የመከላከያ እርምጃዎች (CAPA)
በ ISO 9001 Quality Management System ውስጥ CAPA (Corrective and Preventive Action) ትልቁን ድርሻ ይይዛል።
የእርምት እርምጃ (Corrective Action): የተከሰተን ግድፈት (Non-conformance) ማስተካከል ብቻ ሳይሆን፣ RCAን በመጠቀም ችግሩ በድጋሚ እንዳይከሰት ዘላቂ መፍትሔ ይሰጣል።
መከላከያ እርምጃ (Preventive Action): ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን አስቀድሞ በመተንተን ችግሩ ሳይከሰት መከላከል ያስችላል።

3. በስጋት ላይ የተመሠረተ አስተሳሰብ (Risk-Based Thinking)
ዘመናዊ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት (QMS) መመሪያዎች ተቋማት ቅድመ ስጋት ትንተና ላይ ተመስርተው እንዲሠሩ ያዛሉ። RCA ቀደም ሲል የተከሰቱ ስህተቶችን በመተንተን፣ ወደፊት ሊመጡ የሚችሉ የአሠራርና የምርት ስጋቶችን (Risks) አስቀድሞ ለመለየትና ለመቀነስ ይረዳል።

📌 RCA ተቋማት ከምልክቶች በላይ እንዲመለከቱ፣ መሰረታዊ መንስኤዎችን እንዲረዱ እና ድገግግሞሹን የሚያስቀሩ መፍትሄዎችን በመተግበር ዘላቂ ጥራትን እንዲያረጋግጡ ያስችላቸዋል። RCA ችግርን መፍታት ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለው መሻሻል እሳቤን በማሳደግ የተቋሙን የጥራት ባህል (Quality Culture) ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል።

«በጥራት እንሻገር» በሚል መሪ ቃል የጥራት የውይይት   መድረክ ተካሄደ፡፡ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ (ኢተምድ)=================«በጥራት እንሻገር» በሚል መሪ ቃል...
28/08/2026

«በጥራት እንሻገር» በሚል መሪ ቃል የጥራት የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
=================
«በጥራት እንሻገር» በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት (ኢተምድ) ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ በፓናሊስትነት የተሳተፉበት ሀገራዊ የጥራት የፓናል ውይይት በጥራት መንደር ተካሄደ።
በተቋማትና በሕብረተሰቡ ዘንድ ስለ ጥራት ያለው ግንዛቤ እያደገ ቢመጣም፣ ጥራትን የዘወትር ባህል ከማድረግ አንጻር አሁንም ክፍተቶች እንደሚታዩ በውይይቱ ላይ ተገልጿል። እነዚህን ክፍተቶች ለመሻገር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የኢተምድ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ለጥራት ባህል ግንባታ ዋና ዳይሬክተሯ ካነሷቸው ዋና ዋና የመፍትሔ ነጥቦች መካከል ጥራትን የተቆጣጣሪ አካላት የቁጥጥር ማዕቀፎች ለማለፍ ብቻ ከመጠቀም፤በየቀኑ የአገልግሎት አሰጣጥና አሰራር ውስጥ ጥራትን እንደ ባህል መወሰድ እንደሚገባ አብራርተዋል።

በተጨማሪም የጥራት ጉድለት ሲያጋጥም ሠራተኞችን ከመውቀስ ይልቅ ጥፋቱ እንዳይደገም የሚያደርግ የአሰራር ሂደት ማሻሻያ መተግበር፣ ጥራትን በድህረ-ቁጥጥር ለማረጋገጥ ከመሞከር ይልቅ ስህተቶችና ጉድለቶች እንዳይከሰቱ የሚያስቀር የቅድመ-መከላከል አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ እንደሆነ ገልጸዋል።

አክለውም ጥራትን በጥራት ተቆጣጣሪ አካላትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ብቻ የሚረጋገጥ ሳይሆን የመላው ህብረተሰብ የጋራ ኃላፊነት ማድረግ፣ ከዘልማድ አሰራር በመውጣት በጥራት መስፈርቶችና በመረጃ ላይ የተመሰረቱ ውሳኔዎችን መስጠት እንዲሁም ቀጣይነት ባለው የማሻሻያ ሥራ ላይ ማተኮር ወሳኝ መሆናቸውን ለመድረኩ ተሳታፊዎች አብራርተዋል።

27/08/2026

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ያካሄደውን የክረምት በጎ አድራጎት መርሃ ግብር በተመለከተ በወላይታ ቲቪ የተሰናዳ ዘገባ።

Discussions were held on the implementation of the AfCFTA.August 26, 2026Addis Ababa (ECAE)============ ===== Ethiopian ...
26/08/2026

Discussions were held on the implementation of the AfCFTA.
August 26, 2026
Addis Ababa (ECAE)
============ =====
Ethiopian Conformity Assessment Enterprise held discussions with project coordinators from IGAD and UNECA to evaluate institutional readiness, address operational challenges, and streamline cross-border trade flows under the African Continental Free Trade Area (AfCFTA) framework.

Accordingly, discussions were held regarding ECAE’S readiness for the implementation of the free trade area, focusing on the opportunities and challenges existing around standard harmonization and the role of conformity assessment facilities.

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251900878845

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Conformity Assessment Enterprise -ECAE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Conformity Assessment Enterprise -ECAE:

Shortcuts

Share