06/09/2026
የፅዳት መረሃ ግብር ተካሄደ
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 «ጳጉሜን 1 - የእምርታ ቀን»ን አስመልክቶ ታላቅ የአካባቢ ፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።
በመረሃ ግብሩ የከተማ ፅዳት ኤጀንሲ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማና የወረዳው የሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች በንቃት ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ተግባር የአካባቢን ውበት ከማደስ ባለፈ ህብረተሰቡ በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ለፅዳትና ውበት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ለማስገንዘብ አልሞ የተከናወነ ነው። ተሳታፊዎቹ በአንድነት በመሆን የመኖሪያና የሥራ አካባቢያቸውን ፅዱ አድርገዋል።
ህብረተሰቡ አዲሱን ዓመት በአዲስ መንፈስና በፅዱ አካባቢ እንዲቀበል ጥሪ የቀረበ ሲሆን፣ እያንዳንዱ ነዋሪ የአካባቢውን ፅዳት እንደ ዘላቂ ባህል አድርጎ እንዲቀጥል መልዕክት ተላልፏል።
ለሚ ኩራ ወረዳ 05 ኮሙኒኬሽን
ጳጉሜን 1 / 2018 ዓ.ም