Affini Media

Affini Media ሁለም ከእውት ጎን እንቆማለን

የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ከምሽት 1፡00 ጀመሮ ማየት እንደሚቻል ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።የሀገረ አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች...
25/08/2026

የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት ከምሽት 1፡00 ጀመሮ ማየት እንደሚቻል ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ።

የሀገረ አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት የሚታይባቸውን አድራሻዎች ይፋ አድርጓል።

አገልግሎቱ የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ማየት እንደሚችሉም አሳውቋል።

ተፈታኝ ተማሪዎችም ውጤታቸውን የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።

አያይዞም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን ምአገልግሎቱ ያሳውቃል።

ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms

ምክክሩን ከባድ ያደረገው አለመተሳሰባችን ነው ብዬ አምናለሁ። እያንዳንዳችን የጋራ ጥቅማችንንና የጋራ እሴታችንን ከማየት ይልቅ፣ የቡድን ጥቅማችንን ብቻ እያሰብን ከተንቀሳቀስን፣ እውነተኛ መግ...
24/08/2026

ምክክሩን ከባድ ያደረገው አለመተሳሰባችን ነው ብዬ አምናለሁ። እያንዳንዳችን የጋራ ጥቅማችንንና የጋራ እሴታችንን ከማየት ይልቅ፣ የቡድን ጥቅማችንን ብቻ እያሰብን ከተንቀሳቀስን፣ እውነተኛ መግባባት ላይ መድረስ እንቸገራለን። በምክክሩ የታየው ይህ ነው። ምክክር ማለት የራስን አቋም ብቻ ማስጠበቅ ሳይሆን፣ የሌላውንም ስሜት፣ ታሪክ፣ ማንነትና ጥቅም በመረዳት የጋራ መፍትሔ መፈለግ ነው።

በምክክሩ ወቅት አንዳንዶች አጀንዳውን ራሳቸው ሲያነሱትና አቋማቸውን ሲያራግቡት ታይተዋል። ነገር ግን ተመሳሳይ ጉዳይ በሌላው ወገን ሲነሳ በተለየ መልኩ መመልከት አይገባም። ያንተ ቋንቋ የፌዴራል ቋንቋ ይሁን ሲባል የማይከፋህ ከሆነ፣ የእኔም አካባቢያዊ ቋንቋ የፌዴራል ቋንቋ ይሁን ሲባል ለምን ይከፋሃል? እኩልነት ማለት ለራሳችን የምንፈልገውን መብት ለሌላውም መፍቀድ ነው።

“ሲዳማ ቡና” የሚለውን ስም በደስታ ተጋርተን የምንጠቀም ከሆነ፣ “ሲዳሙ አፎ” የሚለው ጉዳይ ሲነሳ ብቻ ሊከፋን አይገባም። ሌላውን ለራሳችን ጥቅም ስንፈልገው እንደምናከብረው ሁሉ፣ የሌላውንም ማንነትና መብት በእኩልነት ማክበር ይኖርብናል።

መተሳሰብ ከሌለ፣ በማመሳሰል የምናመጣው አንድነት ዘላቂ አይሆንም። እውነተኛ አንድነት የሚመጣው ልዩነታችንን በመቀበል፣ የሌላውን ስሜት በመረዳትና ለሁሉም በእኩል የሚሠራ መፍትሔ በመፈለግ ነው።

“ሲዳሙ አፎ” በፌዴራል ቋንቋዎች ውስጥ እንዳይካተት የተደረገበት አግባብ አሳማኝ ብቻ ሳይሆን አግላይም ነው ብዬ አምናለሁ። ብልፅግና ፓርቲም ቀድሞ የፌዴራል ቋንቋዎችን በማለት ወስኖ ለተሳታፊዎች ማቅረቡ፣ በምንም መመዘኛ ተቀባይነት ያለው አሠራር አይደለም። ይህም የምክክሩን ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ ከቶታል። በተለይም የምክክሩ ዓላማ የተለያዩ ድምፆችን በእኩል ማዳመጥና የጋራ መፍትሔ ማፈላለግ ከሆነ፣ አንድ ጉዳይ ከውሳኔ በፊት በተወሰነ መልኩ ቀድሞ መቅረቡ ተገቢ አይደለም።

ይህ ጥያቄ የሌላውን መብት ለመንፈግ ወይም የአንዱን ቋንቋ ከፍ ለማድረግ ሳይሆን፣ ለሁሉም በእኩል የሚሠራ ፍትሃዊና ግልጽ መመዘኛ እንዲኖር የሚቀርብ ጥያቄ ነው። የቋንቋ ጉዳይ የአንድ ቡድን ጥቅም ብቻ ሳይሆን፣ የማንነት፣ የእኩልነትና የክብር ጉዳይም ነው።

ስለዚህ የሲዳማ ክልል መንግሥትም ይህንን ጉዳይ በአፅንኦት መከታተልና የሲዳሙ አፎ ጉዳይ በፍትሃዊና ግልጽ መመዘኛ እንደገና እንድታይ ተገቢ ጥያቄ ማቅረብ አለበት።

የምንፈልገው ልዩነታችንን በማክበር፣ መብታችንን በእኩልነት በማስጠበቅና በመተሳሰብ ላይ የተመሠረተ እውነተኛና ዘላቂ አንድነት ነው። የምንገነባውም ሁላችንም በእኩል የምንኮራበት ሀገር መሆን አለበት።

ማርቆስ ቡዱሳ

የኢትዮጵያ ኩራት የሆነውን የሲዳማ ቡና አምራች አርሶ አደሮች የልማት ጥያቄሲዳማ ቡና የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የቡና ምልክት፣ የሀገራችን ኩራት እና በዓለም ገበያ ኢትዮጵያን የሚ...
23/08/2026

የኢትዮጵያ ኩራት የሆነውን የሲዳማ ቡና አምራች አርሶ አደሮች የልማት ጥያቄ

ሲዳማ ቡና የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የቡና ምልክት፣ የሀገራችን ኩራት እና በዓለም ገበያ ኢትዮጵያን የሚወክል የገቢያችን የጀርባ አጥንት ነው። በጥራቱ የተመረጠ፣ በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆነ እና ለሀገራችን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ ምርት ነው።

ነገር ግን አንድ አሳዛኝ ጥያቄ አለ: ይህን የኢትዮጵያ ኩራት የሚያመርተው አርሶ አደር ምን አገኘ? የፈደራል መንግስት ለሲዳማ ቡና እንክብካቤ፣ ምርትና ምርታማነት ላይ ትኩረት ያልሰጠው ለምንድ ነው?

ቡናው የሚመረትባቸው ብዙ የገጠር አካባቢዎች እስካሁን በቂ የመንገድ፣ የመብራት፣ የመጠጥ ውሃ፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የመጋዘንና የማቀነባበሪያ መሠረተ ልማት ተደራሽነት የላቸውም። የቡና ምርት ወደ ውጭ ገበያ ስቀርብ የሚያመጣው የውጪ ምንዛሬ እየጨመረ ቢሄድም፣ ያንን ሀብት የሚፈጥረው የአርሶ አደር ሕይወት በተመጣጣኝ መጠን ሲለወጥ አይታይም።

ቡናችን ዓለምን እየደረሰ አርሶ አደሩ ለምን በመሠረተ ልማት እጦት ውስጥ ይቀራል?
ይህ ቅሬታ የፖለቲካ ጥያቄ ብቻ አይደለም፤ የፍትሃዊ ልማት፣ የአርሶ አደሩ ክብር እና የቡና ምርት ዘላቂነት ጥያቄ ነው።
የፌዴራል መንግስት ለእነዚህ የቡና አምራች አካባቢዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ፦
☑️ የገጠር መንገድና ትራንስፖርት
☑️ የመብራትና የቴሌኮሙኒኬሽን ተደራሽነት
☑️ የመጠጥ ውሃ፣ ጤናና ትምህርት
☑️ ዘመናዊ የቡና ማቀነባበሪያና ማከማቻ
☑️ የተሻለ የገበያ ትስስርና የዋጋ ጥበቃ
☑️ የአርሶ አደሮች የምርታማነትና የገቢ ማሻሻያ
☑️ የአፈርና የአካባቢ ጥበቃ
☑️ የቡና ተክል እድሳትና የአየር ንብረት መላመድ
ላይ የተጠናከረ የረጅም ጊዜ ዕቅድ ሊኖረው ይገባል።
የቡና ልማት ማለት ቡናን ብቻ መግዛትና መላክ አይደለም። የቡና ልማት ማለት የቡናውን አምራች ሰው ማልማት ነው።
የሲዳማ ቡና የኢትዮጵያን ስም በዓለም ካስጠራ፣ የሲዳማ ቡና አምራች አርሶ አደርም በክብር፣ በተሻለ ኑሮ እና በልማት መኖር አለበት።
የሲዳማ ቡና ዋጋ በዓለም ገበያ ብቻ አይለካም፤ የሚለካው ቡናውን በሚያመርተው አርሶ አደር የኑሮ ለውጥም ጭምር ነው።
#ሲዳማቡና CoffeeFarmers

ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አዲስ አበባጉዳዩ፡ ቅሬታ ስለማቅረብ ይሆናል በጉዳዩ እንደተቀጠቀሰው እኛ ስማችን ቀጥሎ በፊርማችን ያረጋገጥን የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ተወካዩች የሲዳሙ አ...
21/08/2026

ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡ ቅሬታ ስለማቅረብ ይሆናል

በጉዳዩ እንደተቀጠቀሰው እኛ ስማችን ቀጥሎ በፊርማችን ያረጋገጥን የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ተወካዩች የሲዳሙ አፎ/ሲዳሚኛ ቋንቋ/ የፌደራል የስራ ቋንቋነት ዝርዝር ከተካተቱ 5 ዋና ዋና ቋንቋዎች ውጪ መደረግ አስመልክቶ ያለንን ቅሬታ ቀጥሎ አቅርበናል።

1ኛ. በቡድን አራት (4) የሀገር ግንባታ አጀንዳ ስር የሲዳሚኛ ቋንቋ በፌደራል የሥራ ቋንቋዎች ምድብ ውስጥ እንዲካተት በአሥር፣ በአምሳ፣ በሁለት መቶ አምሳ እና በአምስት መቶ ቡድኖች ላይ ምክረ-ሀሳብ ቀርቦ ስምምነት ላይ የተደረሰ ቢሆንም፤ አጀንዳዎች ተጣጥመው በአንድ ላይ ተዋቅረው ሲቀርቡ 5 ቋንቋዎች (አፋን ኦሮሞ፣ አማርኛ፣ ትግርኛ፣ አፍ ሶማሌ እና አፋርኛ) ቀጥታ የፌደራሉ መንግሥት የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ፤ ሲዳሚኛ ግን አስፈላጊነቱ በቀጣይ ታይቶ እንዲወሰን ተብሎ መቅረቡ ቅሬታ ፈጥሮብናል። ይህም፡-
* 1.1. የፌደራል መንግሥቱን የሥራ ቋንቋ ለመበየን ግልጽ የሆነ የአመራረጥ መስፈርት ባልተቀመጠበት ሁኔታ የሲዳሚኛ ቋንቋ ከቀዳሚዎቹ 5 ተመራጭ ቋንቋዎች ውጪ መደረጉ አግባብ አለመሆኑ፤
* 1.2. ከሁሉም ቡድኖች ተወጣጥተው የተመረጡ 120 አጠናቃሪዎች የውሳኔ ሀሳብ የማቅረብም ሆነ የቀረበውን ምክረ-ሀሳብ የመሻር ወይም የመለወጥ ሥልጣን በምክክር ኮሚሽኑ አሰራር የማይፈቀድ ሆኖ ሳለ፣ ተመካካሪዎች በቋንቋ ዙሪያ ያቀረቡትን ምክረ-ሀሳብ በመለወጥ ደረጃ መድበው ማቅረባቸውን የማንቀበለው መሆኑን፤

2ኛ. በሀገራችን በአሁኑ ወቅት ያሉት 12 ክልሎች እና 2 የከተማ አስተዳደሮች፤ በአጠቃላይ 6 የመንግሥት የሥራ ቋንቋዎችን (አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ፣ ሶማሌኛ፣ አፋርኛ እና ሲዳሚኛ) በሕገ-መንግሥቶቻቸው ተቀብለው ተግባራዊ አድርገዋል። ይህም ማለት ከሲዳሚኛ ቋንቋ በስተቀር የሁሉም ክልሎች የመንግሥት የሥራ ቋንቋዎች የፌደራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ ምክረ-ሀሳብ የቀረበ መሆኑን ያመላክታል። ከዚህ አኳያ የሲዳሚኛ ቋንቋ ብቻ ተነጥሎ ከዝርዝሩ ውጪ መደረጉ ኢ-ፍትሐዊ ከመሆኑም በላይ አግላይ በመሆኑ በድጋሚ እንዲታይልን እንጠይቃለን።

3ኛ. የሲዳማ ክልል የፌደሬሽኑ አባል ክልል መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፤ የሲዳሚኛ ቋንቋ በክልሉ ሕገ-መንግሥት የሥራ ቋንቋ ሆኖ በማገልገል ላይ ይገኛል። በ1999 ዓ.ም በተደረገው የሕዝብና ቤት ቆጠራ የሲዳማ ብሔር በቁጥር 2,966,474 የነበረ ሲሆን፣ በ2018 ዓ.ም የክልሉ ተወላጆች ቁጥር ከ5.5 ሚሊዮን በላይ እንደሆነ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ግምት ያሳያል። በዚህም ከኦሮሞ፣ ከአማራ፣ ከሶማሌ እና ከትግራይ ቀጥሎ በሕዝብ ቁጥር በአምስተኛ ደረጃ ላይ የሚቀመጥ አንጋፋ ሕዝብ በመሆኑ፤

4ኛ. በተጨማሪም የመማሪያና የምርምር ቋንቋ በመሆን ከቅድመ-መደበኛ እስከ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዲግሪ (MA) ደረጃ ድረስ ትምህርት የሚሰጥበት፣ ሙሉ የሥነ-ልሳን ጥናትና ምርምር የተካሄደበት፣ የሕግ፣ የአዋጆች እና የቴክኖሎጂ አገልግሎት ላይ የዋለ አንጋፋ ቋንቋ በመሆኑ ከሌሎች አቻ ቋንቋዎች ተለይቶ ከፌደራል መንግሥት የሥራ ቋንቋነት መገለሉ መሠረታዊ ስህተት በመሆኑ፤

5ኛ. የሲዳሚኛ ቋንቋ ከክልሉ በተጨማሪ ከአጎራባች ሕዝቦች (ከኦሮሞ፣ ከጌዲዮ እንዲሁም ከወላይታ) ጋር በአዋሳኝ ወሰኖች ላይ ዋነኛ የመግባቢያ ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን፤ በተጨማሪም በፍልሰት ምክንያት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተናጋሪ ከክልሉ ውጪ በዋናነት በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች ተሰራጭቶ ይገኛል። በዚህ ምክንያት የሲዳሚኛ ቋንቋ የፌደራሉ መንግሥት የሥራ ቋንቋ ሆኖ ቢካተት የሕዝቦችን ትስስር የበለጠ ያጠናክራል የሚል እምነት ያለን በመሆኑ፤

6ኛ. የሲዳሚኛ ቋንቋ ከአፋን ኦሮሞ፣ ከአማርኛ፣ ከአፍ ሶማሌ፣ ከትግርኛ እና ከአፋርኛ ቀጥሎ የገዥው ፓርቲ፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት፣ የምርጫ ቦርድ እና የምክክር ኮሚሽን ከሚጠቀሙባቸው የሥራ ቋንቋዎች ውስጥ አንዱ ነው። ነገር ግን ከእነዚህ ቋንቋዎች መካከል የሲዳሚኛ ቋንቋ ብቻ ተነጥሎ ከዝርዝር ውጪ መደረጉ ኢ-ፍትሐዊ እና አግላይ በመሆኑ በድጋሚ እንዲታይልን እንጠይቃለን።

በእነዚህ እና በሌሎችም ምክንያቶች የተነሳ ኮሚሽኑ ቅሬታችንን ተቀብሎ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጠን በትሕትና እንጠይቃለን።

ሰበር ዜና !የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ተወካዮች በፌደራል የስራ ቋንቋነት ጉዳይ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረቡትን ቅሬታ በፊርማ አረጋግጠው ለማስገባት ላይ መሆናቸው ተገለጸየሲዳማ ክልል የህ...
20/08/2026

ሰበር ዜና !

የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ተወካዮች በፌደራል የስራ ቋንቋነት ጉዳይ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያቀረቡትን ቅሬታ በፊርማ አረጋግጠው ለማስገባት ላይ መሆናቸው ተገለጸ

የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ተወካዮች የሲዳሚኛ ቋንቋ በፌደራል የስራ ቋንቋነት ከተካተቱት አምስት ዋና ዋና ቋንቋዎች ውጪ መደረጉን በመቃወም ያዘጋጁትን ይፋዊ የቅሬታ ደብዳቤ በፊርማቸው አረጋግጠው ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆናቸው ተገለጸ።

ተወካዮቹ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ባዘጋጁት በዚህ ደብዳቤ፣ በቡድን አራት የሀገር ግንባታ አጀንዳ ስር በነበሩ ውይይቶች ሲዳሚኛ በፌደራል የስራ ቋንቋነት እንዲካተት በምክረ-ሀሳብ ደረጃ ስምምነት ላይ ተደርሶ የነበረ ቢሆንም፣ አጀንዳዎች ተጣጥመው ሲቀርቡ ግን «በሂደት ታይቶ የሚወሰን» ተብሎ መገፋቱ አግላይና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር መሆኑን በመግለጽ ተቃውሟቸውን አዘጋጅተዋል።

ተወካዮቹ በፊርማቸው አረጋግጠው ለኮሚሽኑ ለማስገባት የተዘጋጁበት የቅሬታ ሰነድ እንደሚጠቅሰው፣ የፌደራል መንግስት የስራ ቋንቋዎችን ለመበየን ግልጽ የሆነ የአመራረጥ መስፈርት ባልተቀመጠበት ሁኔታ ሲዳሚኛን ከቀዳሚዎቹ አምስት ቋንቋዎች ውጪ ማድረግ አግባብ አይደለም። በተጨማሪም ከየቡድኑ የተመረጡ 120 አጠናቃሪዎች የተመካካሪዎችን ምክረ-ሀሳብ የመሻር ወይም የመለወጥ ስልጣን ሳይኖራቸው የውሳኔ ሀሳቡን ቀይረው ማቅረባቸው ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ ከሚገኙ 12 ክልሎችና 2 የከተማ አስተዳደሮች ውስጥ የሲዳሚኛን ጨምሮ 6 የስራ ቋንቋዎች በህገ-መንግስት ደረጃ ተቀባይነት አግኝተው ተግባራዊ እየተደረጉ ቢሆንም፣ ከሲዳሚኛ ውጪ ያሉት አምስቱ ቋንቋዎች ብቻ ለፌደራል የስራ ቋንቋነት መጠቆማቸው ኢ-ፍትሃዊ መሆኑን አብራርተዋል።

በሌላ በኩል የሲዳማ ብሔር ከ5.5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያለውና በህዝብ ቁጥር አምስተኛው ትልቅ ብሔር መሆኑን የጠቀሱት ተወካዮቹ፣ ቋንቋውም ከቅድመ-መደበኛ እስከ ሁለተኛ ዲግሪ (ማስተርስ) ትምህርት መስጫ፣ የስነ-ልሳን ጥናት የተካሄደበት፣ የህግና ቴክኖሎጂ ግልጋሎት ላይ የዋለ በመሆኑ ከሌሎች አቻ ቋንቋዎች ተለይቶ መገለሉ መሰረታዊ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሲዳሚኛ ከአጎራባች ብሔረሰቦች (ኦሮሞ፣ ጌዲዮ፣ ወላይታ) ጋር የጋራ መግባቢያ ከመሆኑም በላይ በአዲስ አበባና በተለያዩ ሀገሪቱ አካባቢዎች በስፋት የሚነገር በመሆኑ የህዝቦችን ትስስር ያጠናክራል ብለዋል።

በመጨረሻም የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ተወካዮች የቋንቋው ከዝርዝር ውጪ መሆን ኢ-ፍትሃዊና አግላይ አሰራር መሆኑን በማስገንዘብ፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በፊርማ የተደገፈውን ቅሬታ ተቀብሎ ጉዳዩን በድጋሚ በመመርመር አፋጣኝና ፍትሃዊ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ ደብዳቤውን ለኮሚሽኑ ለማስገባት የመጨረሻ ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በምሁራን ላይ ያነጣጠረ የዲሲፕሊን እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸበሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሲዳማ ተወላጅ ምሁራን ላይ ያነጣጠረ የስነ-ልቦና ማሸማቀቅ፣ ተወዳዳሪ አልባ የማድረግ...
17/08/2026

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በምሁራን ላይ ያነጣጠረ የዲሲፕሊን እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ

በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሲዳማ ተወላጅ ምሁራን ላይ ያነጣጠረ የስነ-ልቦና ማሸማቀቅ፣ ተወዳዳሪ አልባ የማድረግና ከተቋሙ የማጽዳት የተቀናጀ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑ ተጠቆመ።

በማህበራዊ ሚዲያ የተቋሙን ፕሬዚዳንት ተችተዋል እንዲሁም በሲዳማ ተወላጆች ላይ የሚደርሰውን በደል አጋልጠዋል በሚል በግብርና ኮሌጅ መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር ባዩ ቡንኩራ ላይ ክስ እንዲቀርብ መታዘዙ ተገለጸ።

ይህ የዲሲፕሊን ክስ በተጠባባቂው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ትዕዛዝ፣ በአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ፍሥሐ ጌታቸው አማካኝነት የተላለፈ መሆኑ ታውቋል።

ዶ/ር ባዩ ቡንኩራ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ ዩኒቨርሲቲው በተቋማዊ መድልዎና ውስጣዊ ጥላቻ የተባባሰ ከባድ የአሠራር ውድቀት እያጋጠመው እንደሚገኝ ጠቁመዋል። የመናገር ነፃነት መብታቸውን ተጠቅመው በማህበራዊ ሚዲያ ባቀረቧቸው ማስረጃዎች ምክንያት እሳቸውን ለማነጣጠር ሲባል ብቻ ልዩ ጊዜያዊ የዲሲፕሊን ኮሚቴ መቋቋሙን ገልጸዋል። ይህ አሰራር ቀደም ሲል የነበሩ መደበኛ ተቋማዊ ህጎችን ወደ ጎን በመተው፣ ምሁሩን በህጋዊ ሽፋን ለማሸማቀቅና ከኃላፊነታቸው ለማገድ ሆን ተብሎ የተዘጋጀ የአስተዳደር በቀል እንደሆነም አክለው ተናግረዋል።

ይህ በምሁራኑ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ የተቋሙን ድክመቶች የማጋለጥ አቅምን ለመገደብና የሲዳማ ተወላጆችን መሪና ተቆርቋሪ አልባ ለማድረግ የተወጠነ አደገኛ አካሄድ መሆኑ ተመልክቷል። ድርጊቱ ለሕይወታቸውና ለቤተሰባቸው ስጋት ደቅኖ እንደሚገኝ የገለጹት ዶ/ር ባዩ፣ ትግላቸው እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በአሁኑ ወቅት በተቋሙ የበላይ አመራሮች ዘንድ የሚታየው ዝምታ አሳሳቢ በመሆኑ፣ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የዩኒቨርሲቲው ቦርድ እና የሲዳማ ክልል አስተዳደር ጉዳዩን በአስቸኳይ መርምረው አስፈላጊውን የእርምት እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪ ቀርቧል።

በኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲዎች ራስን በራስ የማስተዳደር መብት፡ ለቤንሳ ዳዬ ካምፓስ ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶች።በኢትዮጵያ የሚተገበረው የዩኒቨርሲቲዎች ራስን በራስ የማስተዳደር ሥርዓት ከአለም አቀ...
01/08/2026

በኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲዎች ራስን በራስ የማስተዳደር መብት፡ ለቤንሳ ዳዬ ካምፓስ ያሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶች።

በኢትዮጵያ የሚተገበረው የዩኒቨርሲቲዎች ራስን በራስ የማስተዳደር ሥርዓት ከአለም አቀፍ መስፈርቶች ጋር የሚጣጣም ሲሆን፣ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተወሰኑ ቅድመ-ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ይህንን ደረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል የረጅም ጊዜ ግብ አለው። በአሁኑ ወቅት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የትምህርት ክፍያ የሚፈጽሙበት እንዲሁም የትምህርት መስካቸውንና ተቋማቸውን በራሳቸው የሚመርጡበት ወደሆነው ይህ ሥርዓት እየተሸጋገረ ይገኛል፤ ሆኖም ይህ ለውጥ የቤንሳ ዳዬ ካምፓስን ህልውና አደጋ ላይ ሊጥለው ይችላል፤ ምክንያቱም ተማሪዎች ዋናውን የሀዋሳ ካምፓስ የመምረጥ ዕድላቸው ሰፊ ነው።

ራስ-ገዝነት እና ከፍተኛ ትምህርት

1) ዓለም አቀፍ ተጣጣሚነት፡ የዩኒቨርሲቲዎች ራስ-ገዝነት ወደ ዓለም አቀፍ የአሠራር ደረጃዎች ለመሸጋገር የሚደረግ አዎንታዊ እርምጃ ነው።

2) ሀገራዊ ግብ፡ የረጅም ጊዜ ዕቅዱ፣ ሁሉም የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች አስፈላጊ መስፈርቶችን ካሟሉ በኋላ ራስ-ገዝ የመሆን ደረጃ ላይ እንዲደርሱ ማድረግ ነው።

3) አፈጻጸም፡ ብቁ የሆኑ ተቋማት አዲስ በወጣው የአፈጻጸም አዋጅ መሠረት ወደ አዲሱ አሠራር እየተሸጋገሩ ነው።

4) የተማሪዎች ምርጫ፡ ራስ-ገዝ ሥርዓቶች የትምህርት ክፍያን (በግል ገንዘብ፣ በብድር ወይም በነጻ የትምህርት ዕድል አማካኝነት) እንዲሁም ተማሪዎች የሚፈልጉትን የትምህርት መስክ እና ተቋም የመምረጥ ነፃነትን ያካትታሉ።

የቤንሳ ዳዬ ካምፓስ ተግዳሮቶች

1) የጂኦግራፊያዊ ገደብ፡- በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚመራው ራሱን የቻለ አስተዳደር የተማሪዎችን ምርጫ በሃዋሳ ከተማ ውስጥ ባሉ ፕሮግራሞች ላይ ብቻ ያተኩራል።

2) የልዩነት እጥረት፡- የቤንሳ ዳዬ ካምፓስ እንደ አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች ራሱን የቻለ የትምህርት ፕሮግራሞች ወይም የተለየ ስልት የለውም።

3) የምዝገባ ስጋት፡- በቤንሳ ዳዬ የሚገኙ የአካዳሚክ ክፍሎች በዋናው ካምፓስ የሚገኙትን በመድገም የአካባቢውን የተማሪዎች ፍላጎት ቀንሰዋል።

4) የተሟጋችነት ጥረቶች፡- የህዝብ ግንዛቤ ዘመቻዎች ለቤንሳ ዳዬ በተመሰረተባቸው ዓላማዎች ላይ በመመስረት እኩል የልማት እና ገለልተኛ የአሠራር እድሎችን ፈልገዋል።

እንደሌሎች አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ፣ የቤንሳ ዳዬ (Bensa Daye) ጉዳይም ከመጀመሪያው ዓላማው አንጻር እንዲታይ ለማድረግ የህዝብ ግንዛቤን ለማሳደግ ጥረት አድርገናል። ምን ማመን እንዳለበት የመምረጥ መብት የእያንዳንዱ ሰው ነው፤ ነገር ግን እውነት በመጨረሻው ላይ ግልጽ ይሆናል።

ዶ/ር ባዩ ቡንኩራ አሊቶ በሀዋሳ ዩኒሸርሲቲ መምህር እና ተመራማሪ

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ አንጋፋውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመምራት ብቃት የለለው በመሆኑ ተቋሙ አሁን ለገጠመው ውድቀት ከኃላፊነት ወርዶ እንድጠየቅ አበክረን እ...
31/07/2026

የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ አንጋፋውን ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የመምራት ብቃት የለለው በመሆኑ ተቋሙ አሁን ለገጠመው ውድቀት ከኃላፊነት ወርዶ እንድጠየቅ አበክረን እናሳስባለን።

ውብቷ ሀዋሳ ❤❤❤❤
31/07/2026

ውብቷ ሀዋሳ ❤❤❤❤

"ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግሥት ፖሊሲ ነው። አዎ እኛም እናምናለ። እናዉቃለንም። ተቋሙን ከገደላችሁ በኃላ አታስተባበሉን። የሁሉም ተቋማት አቅም እንድጎለበት ያደረጋችሁት ጥረት አለመኖሩ ለማ...
31/07/2026

"ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የመንግሥት ፖሊሲ ነው። አዎ እኛም እናምናለ። እናዉቃለንም። ተቋሙን ከገደላችሁ በኃላ አታስተባበሉን። የሁሉም ተቋማት አቅም እንድጎለበት ያደረጋችሁት ጥረት አለመኖሩ ለማንም የማይደበቅ ሀቅ ነው።

ለእናንተ የሚናቀርባችሁ ጥያቄ የሚመለከተው ነው:
1. እናንተ ግን ዳዬ በንሳ እና አዋዳ አይዘጋም እያላችሁ ከማዘናጋት ባሻጋር አቅማቸው ለራስ-ገዝነት የበቃ እንድሆን ምን ሰርታችኃል/እየሰራችሁ ነው?
2. የእኛ ጥያቄ አሁን ተቋሙን እየመራ ያለው አካል የመምራት አቅም ስለለለው የራስ-ገዝነት ጉዞም አደጋ ላይ ነው እያልን ነው። እናንተ አሁን ተቋሙ ትክክለኛ ጎዳና ላይ ነው ብላችሁ ታምናላችሁ?
3. እኛም የዳዬ ካምፓስ እና የአዋዳ ብዚነስ ኮሌጅ ሱቅ ነው አላልንም። ነገር ግን ሁለቱም ተቋማት ራስ-ገዝ የመሆን አቅምና አቋም ላይ ካልሆኑ የማይዘጋበት አግባብ አለ ወይ? ለሁለቱም ተቋማት ያደረጋችሁት ድጋፍ ካለ በግልፅ ልታስረዱን ትችላላችሁ?
4. ሌላው ቀርቶ በምርምር አንጋፋ የተባለው ግብርና ኮሌጅ እና ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እራሱ አሁን አቅማቸው ተዳክመዋል። በበጀት እጥረት የሚሰቃዩ ናቸው።
ለእናንተ ግን ትልቁ ስኬት ሁሉንም ምርምሮች ወደ ዋና ግቢ ሰብስባችሁ ከመዝረፍ ውጪ ሌላ ምን ታሪክ አላችሁ?
5. የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሲዳማ ክልል ጋር የውሸት ውል እየተፈራረመ ፕሮፖጋንዳ ከመስራት ውጪ በተግባር የማህበረሰቡ ኑሮ እንድሻሻል በፈጠራ የሰራው ስራ ምን አለ?

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታፈሰ ማቴዎስ በቅርቡ በራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ዙሪያ እየተሰራጩ ስላሉ መረጃዎችና ግምቶች ምላሽ በመስጠት፣ የዩኒቨርሲቲዎችን ወደ ራስ-ገዝነት የማሸጋገር ሂደት የመንግሥት የትምህርት ፖሊሲ አካል መሆኑን መግለጻቸው ትክክል ቢሆንም ያለውን የተቋሙን ክፍተት ለመሸፈን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ግን አጥብቀን እንቃወማለን።

ዝም ብለናል እንጅ እርሶዎም አንዳንዴ ዝም በማለት፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ አብሮ በመወሰን ተባባሪ ኖት እኮ

> yaanno Sidaamu maammaahanni.

Address

Addis Ababa
ET00000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Affini Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share