Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ

Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ ሚሊዮን በለጠ አሰፋ

ሲኖሩ ለመብል፥ ለ'ኔ ለ'ኔ ቅሚያ ፤ሲያልፍም ጊዜ ሄዶ፥ የታሪክም ሽሚያ ።ሰሜን ወደ ደቡብ፥ ሥልጣኔ አንድምታ፤ምሥራቅ ወደ ምዕራብ፥ፀሐይ ወጥታ ገብታ።ምሽቱ ወደ ቀን ፥ ሌሊቱም ሲነጋ ፤መፀው...
24/08/2026

ሲኖሩ ለመብል፥ ለ'ኔ ለ'ኔ ቅሚያ ፤
ሲያልፍም ጊዜ ሄዶ፥ የታሪክም ሽሚያ ።
ሰሜን ወደ ደቡብ፥ ሥልጣኔ አንድምታ፤
ምሥራቅ ወደ ምዕራብ፥ፀሐይ ወጥታ ገብታ።
ምሽቱ ወደ ቀን ፥ ሌሊቱም ሲነጋ ፤
መፀው ወደ ፀደይ ፥ ክረምቱም ሲበጋ ፤
መስቀልና አደይ ፥ ፈክተውና በርተው ፤
ወቅቶች ተፈራርቀው፥ መጥተውና ሄደው፤
ካለፈም በኋላ ፥ ያ ሁሉ መከራ ፤
ያኔ ነው የሚመጣው፥ ያስመሣይ ፉከራ ።
በድል አጥቢያ ኮከብ ፤
ያም ይኼም መዋከብ ፤
"ብለን ነበር ..." ማለት ፤
ነግቶ ለውጡን ሲያዩት ።
መሃል ሰፋሪዎች ፣
ማልያ ቀያሪዎች ፣
ብልጣብልጥ ሰዎች ፤
. . . አጥር ላይ ነበሩ ፤
ሲነጋ ጠብቀው ፥ ወዲያው የዘለሉ ።
ደክመናል ፣ ወርደናል ፤
ቆስለናል ፣ ሞተናል ፤
ለትግሉ የሚሉ ፥ ብዙ ሰዎች አሉ ።
በዚያ ቀውጢ ጊዜ፥ የገዳይ አጃቢ ቀድሞ የነበሩ።
ታች እና ላይ ሲወረድ ሲወጣ ፤
እኔም ብዬ ነበር፥ ይኽ እንደሚመጣ ።
ዥዋዥዌ ሆነ ፥ የሀገሬ ክፉ ዕጣ ፤
ተጽፎ ይቀመጥ ፥ ቀን እስከሚወጣ ።

ሚሊዮን በለጠ አሰፋ ነሐሴ ፲፮ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም

https://vt.tiktok.com/ZSXUBQNBS/ጥርስ ምላስን ነክሶበምላስ የተነሣ ፥ ..ጥርስም ቦክስን           . . .ቀምሶ፤አብረው ይኖራሉ ፤     እንደ ተቻቻሉ ፤ሰውን ሊያስ...
16/07/2026

https://vt.tiktok.com/ZSXUBQNBS/
ጥርስ ምላስን ነክሶ
በምላስ የተነሣ ፥ ..
ጥርስም ቦክስን
. . .ቀምሶ፤
አብረው ይኖራሉ ፤
እንደ ተቻቻሉ ፤
ሰውን ሊያስተምሩ
ፍቅር ይሰብካሉ
በአንድ አፍ ሁለቱ ፦
ጤፍ የሚቆላ
. . . እሳታም!
ስቆ ገዳይ ስለታም!
ለምን አንማርም ?
ከጥርስ እና ምላስ ፤
ከምንበሻሸቅ ...
በነገር ምልልስ ።

ሚሊዮን በለጠ
አሰፋ
ጥር 25 -
2017 ዓ/ም
https://vt.tiktok.com/ZSXUBQNBS/

08/07/2026

Address

Addis Ababa

Telephone

0911723075

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Finote Tibeb ፍኖተ ጥበብ:

Shortcuts

Share

Category