07/09/2026
ለጌርጌሴኖን የአዕምሮ ሕሙማን መርጃና ማገገሚያ ማዕከል ሁለተኛ ዙር ድጋፍ ተደረገ!
************************************
(ጷጉሜን 2/2018 ዓ.ም መካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጨፍ ጽ/ቤት)
የመካከለኛ ግብር ከፋዮች ቁጥር 2 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ገቢ ከመሰብሰብ ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ ይገኛል። ከዚህ ቀደም ለጌርጌሴኖን የአዕምሮ ሕሙማን መርጃና ማገገሚያ ማዕከል ድጋፍ ያደረገ ቢሆንም፣ በአካል በተደረገ ምልከታ ያደረገው ድጋፍ በቂ እንዳልነበር በመገንዘብ በድጋሚ ድጋፍ አድርጓል።
የተቋማዊ አቅም ድጋፍ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዑዳ አሊ ቃል በተገባው መሠረት የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱን ሰራተኞች በማስተባበር ድጋፉ መደረጉን ያወሱ ሲሆን፣ የታክስ ሥርዓት ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሮዛ ጀማል በበኩላቸው ማዕከሉ እያደረገ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የሴቶችና ማኅበራዊ ቡድን አስተባባሪ ወ/ሮ ነጻነት ጥጋቤ እንደገለጹት፤ በአካል ተገኝተው ማዕከሉን በጎበኙበት ወቅት የነበረውን አሳሳቢ ሁኔታ በመመልከት ለሠራተኞች ማብራሪያ ተሰጥቷል። በዚህም መሠረት ከሠራተኛው በፈቃደኝነት የተሰበሰቡ የታሸገ ውሃ ፣ ፍራሽ ፣ የሕክምና መድኃኒቶች እና የጽዳት ዕቃዎች ለማዕከሉ ማስረከብ ተችሏል ብለዋል።
የማዕከሉ ኃላፊዎችም "እየተደረገ ያለው ድጋፍ ለእናንተ ትንሽ ቢመስልም ለማዕከሉ ግን ወሳኝ እና ትልቅ አስተዋፅኦ አለው" በማለት ምስጋናቸውን አቅርበው ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።ማዕከሉ በችግር ምክንያት ጎዳና ላይ የወደቁ ወገኖቻችንን በማንሳት እያገገሙ እንዲቋቋሙ እያደረገ ይገኛል። እንደ ዝክር፣ የሙት ዓመት፣ ልደት፣ ሠርግ፣ ኒካህ እና ሌሎች ዝግጅቶችን በማዕከሉ ውስጥ በማዘጋጀት ወይም በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS) 6860 ላይ OK ብለው በመላክ ለማዕከሉ ደጋፊ አባል በመሆን አጋርነትን ማሳየት እንደሚቻል ጠቁመዋል፡፡
የበጎ አድራጎት ሥራችን ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ግብር÷ ለሃገር ክብር!
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ቴሌግራም፦ https://t.me/mormto2
ፌስቡክ፡- https://web.facebook.com/info.mto2/
ቲክቶክ፡-https://www.tiktok.com/
ኢሜል፡- [email protected]
ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-MTO2
አድራሻ፡- ከሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስደዉ መንገድ ገነት ሆቴል ፊት ለፊት ካሳ ግራንድ ሞል ላይ እንገኛለን