09/09/2026
ዎላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የ2019 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል ያለምንም የጸጥታ ስጋት በሠላም ተከብሮ እንዲውል ለማድረግ በቂ ዝግጅት መደረጉን ገለፁ ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮ/ር ሀብታሙ አሠፋ እንደገለጹት፣ አዲሱ ዓመት ያለምንም የጸጥታ ስጋት በሰላም እንዲከበር ቅድመ ዝግጅቶች መደረጉን ገልጿል ።
ህብረተሰቡ በበዓሉ ወቅት የበኩሉን ጥንቃቄና ትብብር እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።
በበዓሉ ምክንያት የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉና ባዕድ ነገር ቀላቅለው በሚሸጡ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዉ ህብረተሰቡ መሰል ድርጊቶችን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል።
በገበያ አካባቢዎች ከፍተኛ የሰው ፍሰት ስለሚኖር ማህበረሰቡ ራሱን ከሌቦችና ኪስ አውላቂዎች እንድሁም ሎተሪ ደርሰውኛል ግን ለከተማው አድስ ነኝ እያሉ ከሚያታለሉ ግለሰቦች እንዲጠብቁ አሳስበዋል ።
የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት የጸጥታ አካላትና ትራፊክ ፖሊሶች ከወትሮው በተለየ መልኩ ጥብቅ ቁጥጥር ያደርጋሉ ተብለዋል ።
በበዓሉ አከባበር ወቅት የእሳት አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊው ጥንቃቄ ሁሉ መደረግ አለበት ተብሏል ።
ኮ/ር ሀብታሙ አሠፋ የ2019 አዲስ ዓመት ለመላው የከተማ ህዝብ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።
ማንኛውንም ዓይነት የጸጥታ ስጋትና ጥቆማ ሲኖር በከተማዉ ፖሊስ መረጃ ስልክ ቁጥር 0465510146 እና በነፃ ስልክ ቁጥር 6793 ላይ በመደወል ማሳወቅ ይቻላል።
🌼 እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! 🌼