08/06/2026
ትናንትን እያከምን ነገን ዛሬ እየገነባን አስተማማኝ ሰላማችንን እናረጋግጣለን!
ለዘመናት ሲዘራ የኖረው አሉታዊ ትርክት የነበረውን የማህበረሰብ ትስስር እና አብሮነት ሲሸረሽረው ቆይቷል፡፡ በሕዝብ መካከል መከፋፈል፣ መጠራጠር፣ ጥላቻና ተቃርኖ እየፈጠረ በተደጋጋሚ ወደ ግጭት የሚያመራውም ከወል ትርክቶች ይልቅ ተናጠላዊ ትርክቶች ጎልተው በመውጣታቸው ነው፡፡
ህብረ ብሔራዊነትን ከአንድነት አጣጥሞ የሚሄድ የፖለቲካ ሥርዓት ስላልነበረን በአንድ ዘመን በማንነት መኩራት ነውር ነበር፡፡ በኋላ ደግሞ በተቃራኒው ኢትዮጵያ የሚለውን ስም መጥራት እንደ ስህተት ተቆጠረ፡፡
እንዲሁም የአስተሳሰሩን ፀጋዎች ተዘንግተውና ተረስተው ቆዩ፡፡ በዚህም ምክንያት ለሀገራዊ አንድነት መዳከም ትልቁን ሳንካ ፈጠረ። ከዚህም ባሻገር የተለያዩ ሕዝቦችና ማንነቶች በሀገራቸው ባይተዋር ሆነው፣ የጥቂቶች የበላይነት የሰፈነበት አገዛዝ ሀገራዊ አንድነት ሲያዳክም ቆይቷል፡፡
ከለውጡ በፊት የነበረው አግላይ ስርዓት ብዙሀኑን ከፖለቲካና ከኢኮኖሚ ሂደት ፍትሐዊ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ በማድረግ የጥቂቶችን አምባገነናዊ ሥርዓት አስፍኖ ነበር።
ህዝቦች በክልላቸው ራሳቸውን በራሳቸው የማስተዳደር መብታቸው ተገፎ በሞግዚት እንዲተዳደሩ ከማድረጉ ባሻገር የነበረው ስርዓት ዋናና አጋር፣ ልማታዊና ኪራይ ሰብሳቢ፣ ጠባብና ትምክህተኛ፣ ወዘተ. የሚሉ ከፋፋይ ትርክቶችን በመከተል ብዙሀኑን አግልሎ ቆይቷል፡፡
በሀገር በቀሉ የመደመር ፍልስፍና ሁሉም ዜጎች በሀገራቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች እኩል ተሳታፊና ፍትሀዊ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ስርዓት በመዘርጋቱ ህዝብን በሀገሩ ላይ ባይተዋር አድርገው የቆዩ በርካታ ስብራቶች እየተጠገኑ ነው፡፡
ሁሉም ችግሮች በውይይት እና በድርድር እንዲፈቱ፣ ሁሉም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ ፣ የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ የሀሳብ የበላይነት ገዢ እንዲሆን በብልፅግና ፓርቲ የተወሰዱ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ሀገራችንን ከግጭት አዙሪት በማውጣት አስተማማኝ ሰላሟን ዘላቂ ለማድረግ ፅኑ መሰረተ ናቸው፡፡
አሰባሳቢው የብሔራዊነት የወል ትርክት እንዲገነባ ሀገራዊ እሴቶችን በመጠቀም፣ ሌሎችንም አቅሞች በማስተባበር እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትም ከሁሉም፣ በሁሉም፣ ለሁሉም የሆነች፣ ተጋላጭነትን ያስወገደች ሉዓላዊት ሀገር ለመገንባት ያለንን ተጨባጭ ህልም እና ቁርጠኝነት አመላካች ናቸው፡፡
ኢትዮጵያዊያን ከጠዋቱ 12:00 እስከ ሌሊቱ 7:00 እረጃጅም ሰልፎችን ታግሰው ፣ መምረጥ አትችሉም ላሏቸው ኋላቀሮች ዛቻና ማስፈራሪያ ጆሮ ሳይሰጡ ሰባተኛውን ሀገራዊ ምርጫ በስኬት ማጠናቀቃቸውም ሰላምን በሰላማዊ መንገድ ለማምጣት የተጀመረው ርብርብ ስር እንዲሰድ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጠ ሀቅ ሆኗል::
የውይይት ባህልን ለማዳበር እየተሰሩ ከሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ባሻገር 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሀዊ እና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ መጠናቀቁ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ለማረጋገጥ ለሚደረገው አበረታች ጥረት ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል።
ኢጋድ ፣ የአፍሪካ ህብረት ፣ የአውሮፓ ህብረት እና መሰል ቀጠናዊና አህጉራዊ ተቋማት ጭምር የምርጫውን ዴሞክራሲያዊነት የተናገሩለት ፣ ህዝባችን በነፃነት ያካሄደው ፣ በሁሉም መመዘኛዎች ሂደቱም ጭምር ፍትሀዊ የነበረው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከፍተኛ የህዝብ ቅቡልነትንም አግኝቷል።
ሁሉም ተፎካካሪ ፓርቲዎች የመወዳደሪያ ሀሳባቸውን ለህዝባችን አቅርበዋል። ህዝባችን ደግሞ በካርዱ ይበጀኛል ያለውን መርጧል።
የህዝባችን ድምፅ እየተገነባ ለሚገኘው የውይይት ባህል መዳበር ፅኑ መሰረት ነው። የህዝብ ድምፅ ሉዓላዊ ነው ፤ በሁሉም ይከበራል።
መልካም የስራ ሳምንት ይሁንላችሁ! ይሁንልን!
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት