Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party, Political Party, WWW. FIRITCH. COM, Addis Ababa.

ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት፣ ለላቀ የህዝብ ተጠቃሚነት!የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት፣ ለላቀ የህዝብ ተጠቃሚነት በሚ...
10/07/2026

ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት፣ ለላቀ የህዝብ ተጠቃሚነት!

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት ጠንካራ የፓርቲ አደረጃጀት፣ ለላቀ የህዝብ ተጠቃሚነት በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት ዓመት የፓለቲካና የአደረጃጀት ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ አካሄደ።

በግምገማ መድረኩ ላይ የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ወይዘሪት ወይንሸት አስናቀን ጨምሮ ሌሎች የክፍለ ከተማና የሁሉም ወረዳ ፓርቲ ኮሚቴዎች የተገኙ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የተሰሩ የፖለቲካና የአደረጃጀት ሰራዎች ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ ተካሂዷል።

የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ኃላፊ ወይዘሪት ወይንሸት አስናቀ በግምገማ መድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት ባለፈው በጀት ዓመት በተቀናጀና በተናበበ ሁኔታ ባስቀመጥናቸው ግቦች መሠረት ምርጫን ጨምሮ በርካታ ስኬታማ የሆኑ የፖለቲካና የፓርቲ ስራዎችን ሰርተናል ያሉ ሲሆን ከዕለት ወደዕለት እያደገና እየጎለበት እንዲሁም ተጨባጭ ለውጦች እያመጣ ያለውን የአመራራችንን ሁለንተናዊ የማስፈፀምና የመፈፀም አቅምን ባገናዘበ የአመራር ስምሪት ክፍለ ከተማችንን የአዲስ አበባ የብልፅግና ተምሳሌትና በሁሉም ዘርፍ ሞዴል ለማድረግ የሰራናቸው ተግባራት እጅግ አመርቂ ነበሩ ብለዋል።

በተለይ የሰባተኛው ዙር ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ምርጫ ስራ ከተጀመረ በኋላ ሁሉንም አቅማችንን በማስተባበር በአንድ በኩል ምርጫው ፍትሐዊ፣ዴሞክራሲያዊና ቅቡልነት ያለው እንዲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በዴሞክራሲያዊ የምርጫ ውድድር ፓርቲያችን አሸናፊ ሆኖ እንዲያጠናቅቅ ያስቀመጥናቸው መንትያ ግቦችን ለማሳካት የሰራናቸው ስራዎች ውጤት አስገኝቸውልናል ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ አዳዲስ አባላትን ወደ ፓርቲው ከመቀላቀል፣በሰው ተኮር ተግባራትና በንቅናቄ ስራዎች እንዲሁም በየደረጃው ያለውን የአመራራችንና የአባላትን የአቅም በመገንባት ረገድ የሰራናቸው ጠንካራ ስራዎች ለውጤታማነታችን ጠቃሽ ምክንያቶች ናቸው ሲሉም ኃላፊዋ አክለው ገልፀዋል።

የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ፀጋዬ ሳህሉ በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት በክፍለ ከተማችን አመራሩ ህዝባችንና መላ መዋቅራችንን ከጎኑ በማሰለፍ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልፀው የብልፅግና ቤተሰብ ውይይቶችን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን፣ የሌብነትና ሌሎች ብልሹ አሰራሮችን የምንተጋገልበት መድረክ ከማድረግ አንፃር ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመዋል።

የሞዴል ተቋማትን ለመፍጠር ህብረቶች በጎ ተፅኖ ውድድሮች የጥያቄና መልስ ውድድሮች እና የፓርቲ ተቋማት አቅም ሆነው እንዲወጡ በተሰሩ ስራዎች ተጨባጭ ለውጥ የተገኘባቸው ተግባራት መሆናቸውንም አክለው ገልፀዋል።

የግምገማው ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው ባለፈው በጀት ዓመት ለውጥ ባመጣንባቸው ተግባራትና የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ በማጎልበት እንዲሁም የታዩ ክፍተቶችን በማረም በ2019 በጀት ዓመት በልዩ ትኩረት እንሰራለን ብለዋል።



Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

እነሆ ዛሬም ሌላ አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል!!ዛሬ በራስ ደስታ  ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች  ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ  የላቀ የህክምና ማዕከል” ገንብተን...
10/07/2026

እነሆ ዛሬም ሌላ አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል!!

ዛሬ በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል” ገንብተን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

ነባሩ ሆስፒታል በጣም በማርጀቱ ለታካሚዎች የማይመች መጨናነቅ የነበረበት፣ የነበሩት ኋላቀር የህክምና መሳሪያዎች ለታካሚዎች ብቻ ሳይሆን ለባለሙያዎቹም አገልግሎት ለመስጠት ጥራቱን ያልጠበቀና ምቹ ያልሆነ ነበር።

ይህንን አስከፊ ሁኔታ ታሪክ በማድረግ እጅግ ንፁህ ውብ የሆነ ባለ7 ወለል ህንፃ ገንብተን በይዘቱ የህክምና አገልግሎቶችን እጅጉን የሚያሻሽል፤ የዘመኑ ቴክኖሎጂ የተሟሉለት ሲሆን በነባሩ ህንፃ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት በአጥፍ የሚያሳድግ ማዕከል ነው።

በአዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል የ2026 ምርቶች የሆኑ AI የሚጠቀሙ ዲጅታል ኤምአርአይ (MRI)፤ ሲቲስካን፣ የአልትራሳውንድ፣ ተንቀሳቃሽ ኤክስሬይ፣ በሰዓት 30,000 ሊትር የሚያመርት የኦክሲጅን ማምረቻ (Oxygen plant)፤ እንዲሁም ቀድሞ የነበረው የአስተኝቶ ህክምና አልጋ ከ147 ወደ 360 አድጓል፥ የኦፕሬሽን ክፍል ከ3 ወደ 7፣ የፅኑ ህክምና ክፍልም ወደ 19 አድጓል። በተጨማሪም ሰፊና የላቀ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ስታንዳርዱን ጠብቆ ተደራጅቷል። የሰራተኛ ማረፊያ ክፍሎች፣ ላይብረሪ፤ ዘመናዊ ቢሮዎች፤ መሰብሰቢያ አዳራሾች እና የሰራተኛ ካፍቴሪያ አገልግሎት ለታካሚዎች በሚመች መልኩ ተገንብቶና ተደራጅቶ ለአገልግሎት በቅቷል።

አዲስ አበባ ላይ ያለው የጤና አገልግሎት ፍላጐት በመንግስት ብቻ የማይሟላ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ በመደገፍም ወደ ውጭ በመሄድ ይደረግ የነበረውን ህክምና በአገር ውስጥ የህክምና አገልግሎት መስጠት መቻሉ፣ ዓለም በዘርፉ የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ የጀመርናቸው ሥራዎች ህያው ምስክር ናቸው።

አዲሰ የላቀ የህክምና ማዕከል በፍጥነትና በጥራት ተገንብቶ የነበረውን አገልግሎት በአጥፍ በማሳደግ የላቀ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ሆኖ እንዲጠናቀቅ አብራችሁን የነበራችሁ፣ የተባበራችሁ፣ የገነባችሁ በራሴና በታካሚው ሥም ከልብ አመሰግናለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

ኢትዮጵያ ምክክርን መርጣለች! አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንም አስፍታለች!ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 5 ቀናት ብቻ ቀርተውታል!መላው ጥቁር ህዝብ የሚኮራበትን የአድዋ ድል ታሪክ የሰራች፣ የሰው ዘር መገ...
10/07/2026

ኢትዮጵያ ምክክርን መርጣለች! አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንም አስፍታለች!

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 5 ቀናት ብቻ ቀርተውታል!

መላው ጥቁር ህዝብ የሚኮራበትን የአድዋ ድል ታሪክ የሰራች፣ የሰው ዘር መገኛ የሆነች፣ የራሷ የዘመን አቆጣጠር የቀመረች፣ ፊደላትን የቀረፀች፣ ገዳን የመሳሰሉ ጥንታዊ የዴሞክራሲ እሴቶች ያሏት ኢትዮጵያ የማይበገር ጀግና ህዝብ ያላት ታላቅ ሀገር ናት፡፡

ሉዓላዊነቷን ሊገረስሱ የመጡ ወራሪ ሀይሎችን በሙሉ አሳፍራ የመለሰች፣ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመገደብ በተፈጥሮ ሀብቷ እንዳትጠቀም ጠላቶቿ የሸረቡትን ሴራ የበጣጠሰች ከጀግንነት ጋር ስሟ የማይነጣጠል ጀግና ሀገር መሆኗን ታሪካዊ ጠላቶቿም ሆኑ ወዳጆቿ ጠንቅቀው ይረዱታል፡፡

ድህነት መገለጫዬ ሊሆን አይገባም በማለት ለሁለንተናዊ ብልፅግና እየተጋች የምትገኘው ኢትዮጵያ ለዘላቂ ዕድገቷ እና ለአስተማማኝ ሰላሟ ቆርጣ ተነስታለች፡፡

ሀገር አፍራሽ ሀይሎች ደቅነውት የነበረውን ጦርነት በብቃት በመመከት፣ በአሸናፊነት በመቋጨት፤ ሀገራዊ ችግርን በሀገራዊ መፍትሔ በሚል በፕሪቶሪያው ስምምነት ተምሳሌትነቷን ያጠናከረችው ኢትዮጵያ ችግሮችን በጠረንጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ቁርጠኝነቷን ካረጋገጠች ሰነባብታለች፡፡

የኢትዮጵያ የሰላም እጆች አሁንም እንደተዘረጉ ናቸው፡፡ ሀገራዊ ምክክር የሚባል ታላቅ የሰላም ድግስ ደግሳለች፡፡ በዚህ የምክክር ሂደት የሁሉም ኢትዮጵያዊ የግል እና የቡድን ጥያቄዎች በስፋት የቀረቡ ሲሆን፤ ከ5 ቀናት በኋላ ሀምሌ 8 በመዲናችን መካሄድ በሚጀምረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን በተቀረፁት ጥቅል አጀንዳዎች ላይ ታሪካዊ ምክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

የኢትዮጵያ ብልጽግና እስኪረጋገጥ ድረስ በጋራ መቆም አለብን! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party
09/07/2026

የኢትዮጵያ ብልጽግና እስኪረጋገጥ ድረስ በጋራ መቆም አለብን! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)


Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

ሀገራዊ ምክክር፤ ለዘላቂ ሰላምና ለሀገር ግንባታ ኢትዮጵያችን በረጅም ታሪኳ ልብን በኩራት የሚሞሉ በርካታ አንጸባራቂ ድሎችን አስመዝግባለች፤ በተመሳሳይ ደግሞ እጅግ ፈታኝ የሆኑ ውጣ ውረዶችን...
09/07/2026

ሀገራዊ ምክክር፤ ለዘላቂ ሰላምና ለሀገር ግንባታ

ኢትዮጵያችን በረጅም ታሪኳ ልብን በኩራት የሚሞሉ በርካታ አንጸባራቂ ድሎችን አስመዝግባለች፤ በተመሳሳይ ደግሞ እጅግ ፈታኝ የሆኑ ውጣ ውረዶችንም አሳልፋለች። የፖለቲካ ልዩነቶች፣ የታሪክ አተረጓጎም ሽኩቻዎች፣ የማንነት ጥያቄዎችና የፍትሕ መጓደሎች ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡና ማህበራዊ ትስስራችንን የፈተኑ ከባድ ጉዳዮች ናቸው። ዛሬ ላይ ሆነን ስናስበው፣ እነዚህን ውስብስብና ስር የሰደዱ ችግሮች በጠመንጃ አፈሙዝ ወይም እርስ በርስ በመወነጃጀል ልንፈታቸው እንደማንችል በግልፅ ተረድተናል። ይልቁንም፣ በመደማመጥ፣ በውይይትና በመግባባት አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት የጀመርነው ሀገራዊ የምክክር ጉዞ ለሀገራችን አዲስ የብርሃን ወጋገን ነው።

ሐምሌ 8 በይፋ የሚጀመረው ሀገራዊ ምክክርም ከዚህ እውነታ የሚመነጭ ነው። ይህ መድረክ ከተለያየ የህብረተሰብ ክፍል የመጡ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠው የልባቸውን የሚነጋገሩበት፣ ስጋትና ተስፋቸውን የሚያካፍሉበት ትልቅ የጋራ አላማ ያነገበ ውይይት ነው። ከመላው ሀገሪቱ፣ ከታችኛው የህብረተሰብ ክፍል ጀምሮ በከፍተኛ ተሳትፎ የተሰባሰቡት አጀንዳዎች የጥቂቶችን ድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ የብዙሃኑን ኢትዮጵያዊ የልብ ትርታና እውነተኛ ጥያቄ የሚያንፀባርቁ ናቸው። ይህ ሂደት እያንዳንዱ ዜጋ "ድምፄ ተሰምቷል" ብሎ እንዲያምንና ለመፍትሄውም የራሱን ጡብ እንዲያኖር የሚያስችል ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።

ይህን ጉዞ ስንጀምር፣ የብልፅግና ፓርቲ ከመነሻው ያነገበውን "መደመር" የተሰኘ መሪ ዕሳቤ ማስታወስ ተገቢ ነው። ልዩነቶችን በግጭትና በመጠላለፍ ሳይሆን፣ በውይይትና በወንድማማችነት መንፈስ ለመፍታት የተያዘው ይህ ፖለቲካዊ አቅጣጫ፣ ዛሬ በሀገራዊ ምክክሩ መልክ መሬት እየነካ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ደጋግመው እንደሚያነሱት፣ "ሰላም እንደ ውርስ በራሱ የሚተላለፍ ስጦታ ሳይሆን፣ በጋራ ጥረት፣ በውይይትና በመተማመን የምንገነባው እሴት ነው።" አክለውም "ኢትዮጵያን የምንገነባት አንዱ ሌላውን በማሸነፍና በመርገጥ ሳይሆን፣ በመደመር ነው" በማለት የገለጹት ጥልቅ ሀሳብ፣ የዚህ ሀገራዊ ምክክር ዋነኛ ሞተር ነው።

በዚህ ምክክር ማንም የሚያሸንፈው ወይም ማንም የሚሸነፈው አካል የለም፤ ብቸኛዋ አሸናፊ ኢትዮጵያ ነች። ይህ መድረክ የታሪክ ቁርሾዎቻችንን በይቅርታ የምናክምበት፣ የትውልዱን ጥያቄዎች በጋራ የምንመልስበት፣ እንዲሁም መጪው ትውልድ ቂም ሳይሆን ፍቅርን፣ ጦርነትን ሳይሆን ሰላምን አውርሰነው እንዲያልፍ የምንሰራበት ወርቃማ እድል ነው።

በመሆኑም፣ ይህ የጋራ ቤታችን ጉዳይ ነውና እያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ተዋናዮች፣ የሲቪል ማህበራት፣ ምሁራን፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች ሁላችንም በቅንነት፣ በከፍተኛ ኃላፊነትና በተስፋ መንፈስ ልንደግፈው ይገባል። ዛሬ የምናደርገው በሳል ውይይት፣ ነገ የልጆቻችን መፈንጠቂያ የሆናች፣ ሰላሟ የተረጋገጠ፣ ፍትሕ የሰፈነባትና የበለፀገች ኢትዮጵያን ይገነባል።
ሀገራዊ ምክክር እውነተኛ የሀገር ግንባታ የመሠረት ድንጋይ፣ የጋራ ዕጣ ፈንታችን መሪ አቅጣጫ ጠቋሚ እና የአንድነታችን ዘላቂ ዋስትና ነው።
Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

ኢትዮጵያ በምክክር ችግሮቿን ትፈታለት ! አዲስ አበባም እንደ መዲናነቷ  ታዳሚያንን ተቀብላ በብቃት ለማስተናገድ  ዝግጅት አድርጋለች!ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሊካሄድ 6 ቀናት ብቻ ቀ...
09/07/2026

ኢትዮጵያ በምክክር ችግሮቿን ትፈታለት ! አዲስ አበባም እንደ መዲናነቷ ታዳሚያንን ተቀብላ በብቃት ለማስተናገድ ዝግጅት አድርጋለች!

ታሪካዊው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሊካሄድ 6 ቀናት ብቻ ቀሩት!

የሀሳብ የበላይነት ሲከበር ፣ መደማመጥ ሲዳብር ሀሳብ አልባነት ቦታ ያጣል። ኢትዮጵያ በብሔራዊ ምክክር በኩል የውይይት ባህልን ለመገንባት ብርቱ ጥረት ጀምራለች።

ከሰሜን ጫፍ እስከ ደቡብ ጫፍ ፣ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ጫፍ ህዝባችን አሉኝ የሚላቸውን ጥያቄዎች በሰለጠነ መንገድ አቅርቧል።

በህዝብ የተነሱ ሁሉንም ጥያቄዎች ሲያሰባስብ የቆየው ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ስምንት ጥቅል አጀንዳዎችን በመጠመር ሀምሌ 8 / 2018 ዓ.ም ሁሉም የህበረተሰብ ክፍል በተወካዮቹ በኩል የሚሳተፍበትን የምክክር መድረክ ደግሷል።

የሁሉም ኢትዮጵያዊ ቤት፣ የአፍሪካ ኩራት፣ የዲፕሎማቲክ ስዕበት የሆነችው መዲናችን አዲስ አበባም ከሁሉም የኢትዮጵያ ወረዳዎች የሚመጡ እንግዶችን መቀበል ጀምራለች፡፡

ይህ የምክክር እና የውይይት አካሄድ አሻጋሪ ነው ። ይህ አካሄድ የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ጉዞን በፅኑ አለት ላይ የሚገነባ ብቸኛው መንገድ ነው።

የሀገራችን ውስብስብ ችግሮች የሚቀረፉት በዳበረ የውይይት ባህል ነው ፤ ከጫፍ እስከ ጫፍ ሁሉንም እያሳተፈ የሚገኘው ብሔራዊ ምክክር ደግሞ አንደኛው ቁልፍ ነው።

ለሀገራችን ብሩህ ተስፋ የፈነጠቀውን ይህ እድል የሰመረ እንዲሆን ሁሉም ዜጋ የድርሻው ጠጠር ሊያሳርፍ ይገባል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት


Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

09/07/2026
ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን የጦርነት ቅስቀሳና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ በአስቸኳይ ሊያቆም ይገባልሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን አዲ...
08/07/2026

ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን የጦርነት ቅስቀሳና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ በአስቸኳይ ሊያቆም ይገባል

ሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን በትግራይ ክልል እያደረገ ያለውን አዲስ የጦርነት ቅስቀሳና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ በአስቸኳይ ሊያቆም እንደሚገባ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችና የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጠየቁ፡፡

ሴንተር ፎር ሪስፖንሲብል ኤንድ ፒስፉል ፖለቲክስ (CRPP) ከትግራይ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (TBS) ጋር በመተባበር ”ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፣ የመገናኛ ብዙኃን እና የማኅበረሰብ አንቂዎች ሚና” በሚል ርዕስ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የውይይቱን መጠናቀቅ ተከትሎ ባለ 14 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ባወጡት የአቋም መግለጫ በትግራይ ክልል እየተፈጸመ ያለው የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላና አፈና በአስቸኳይ እንዲቆም የጠየቁ ሲሆን፤ አካባቢውን ወደ አዲስ የጦርነት አዙሪት የሚገፉ ማናቸውም እንቅስቃሴዎች እንዲገቱ አሳስበዋል።

በትግራይ ክልል ወጣቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው አፈና እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላም በአስቸኳይ እንዲቆም በጽኑ ጠይቀዋል።

የመሬት ላይ እውነታው የትግራይ ወጣቶች ለተደጋጋሚ መክሸፍና ለከፋ እልቂት ሲዳረጉ መቆየታቸውን የጠቀሰው የአቋም መግለጫው፤ ይህ ታሪካዊ ምዕራፍ በአስቸኳይ ሊያበቃ እንደሚገባና ለዚህ መርህ መከበርም ባለሙያዎች በሙሉ አቅማቸው እንደሚሠሩ አስታውቋል።
የጋዜጠኞች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችና የአክቲቪስቶች አጀንዳዎች በሙሉ በሕዝቡ እውነተኛና አንገብጋቢ ፍላጎቶች ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ ጥሪ ቀርቧል።

የጦርነት ጋዜጠኝነትን እና ቀስቃሽ ፕሮፓጋንዳዎችን፣ የጥላቻ ንግግሮችና የተሳሳቱ መረጃዎችን፣ የሕዝብ አስተያየትን ለቡድን ፍላጎት የማጭበርበር ተግባራትን ማውገዝ እንደሚገባ በአቋም መግለጫው ተመላክቷል።

በዚህም የሕዝቡ ጥልቅ ሥቃይ ከፖለቲካ መፈክሮችና ከወታደራዊ ንግግሮች በስተጀርባ ሊደበቅ እንደማይገባ በአቋም መግለጫው ተገልጿል።

የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት መመለስና መልሶ ማቋቋም፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የጤና እና የትምህርት አገልግሎቶችን በይፋ ማግኘት፣ የመንግሥት ሠራተኞች የተከማቸ ደመወዝ ክፍያ መፈጸም እና የኢኮኖሚ ማገገም ላይ መገናኛ ብዙኃን በትኩረት ሊሠሩባቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንደሆኑም ተመልክቷል።

የትግራይ የፖለቲካ ቡድኖች የሕዝቡን ሕልውና ከፓርቲ ፍላጎት በላይ እንዲያስቀድሙ፣ ቀጣናውን ወደ አዲስ ጦርነት ከሚገፋፉ ቅስቀሳዎች እንዲቆጠቡና ልዩነቶችን በሰላማዊ ውይይት ብቻ እንዲፈቱ ተጠይቋል።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት የሰላም ስምምነቶች መፈጸማቸውን እንዲያረጋግጥ፣ ተፈናቃዮችን ለመመለስና ወጣቶችን ከአዲስ ወታደራዊ ቅስቀሳ ለመጠበቅ በሕገ-መንግሥታዊና ሞራላዊ ሥልጣኑ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ ቀርቧል።

ለዚህም የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት መሪዎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ተዋናዮች በሂደቱ እንዲሳተፉ ተጠይቋል። “ወደ ጦርነት መመለስ የለም! በሥቃይ ፊት ዝምታ አይኖርም! ሕዝብን ለፖለቲካ ወይም ለወታደራዊ ዓላማ መጠቀሚያ ማድረግ ይብቃ!” በማለት በአቋም መግለጫቸው አስገንዝበዋል።

የአቋም መግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፡ የመገናኛ ብዙኃን እና የማህበረሰብ አንቂዎች ሚና
ሰኔ 30 2018 አዲስ አበባ

1. እኛ “ሰላም፣ ዴሞክራሲና ልማት በትግራይ፡ የመገናኛ ብዙኃን እና የማህበረሰብ አንቂዎች ሚና” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የውይይት መድረክ ላይ የተሳተፍን አካላት፤ በትግራይ ወቅታዊ የፖለቲካ፣ የፀጥታ፣ የሰብአዊ እና የልማት ሁኔታዎች ላይ በጥልቀት ከተወያየን በኋላ፣ ለትግራይ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም ለሰላም፣ ለዲሞክራሲ፣ ለሰብአዊ ክብር እና ለሀገራዊ መረጋጋት ካለን ጥልቅ የኃላፊነት ስሜት በመነጨ ይህንን የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

2. የትግራይ ሕዝብ በጦርነት፣ በመፈናቀል፣ በኢኮኖሚ መቃወስ፣ በፀጥታ እጦት፣ በተቋማዊ አለመረጋጋት፣ በሰብአዊ ቀውስ እና በተራዘመ አለመተማመን ሳቢያ ከፍተኛ መከራ እያሳለፈ መሆኑን እንገነዘባለን። የትግራይ ሕዝብ ሕይወት፣ ክብር፣ ደኅንነት እና የወደፊት ዕጣ ፈንታ ከማንኛውም የፖለቲካ ስሌት፣ የቡድን ፍላጎት፣ የወታደራዊ ምኞት እና ከፋፋይ ትረካዎች በላይ ሊቀመጥ እንደሚገባ በጽኑ እናምናለን።

3. በተጨማሪም ሰላም አሁንም ተሰባሪ መሆኑን እና ወደ ማንኛውም የትጥቅ ግጭት መመለስ ለትግራይ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ እንዲሁም ለሰፊው ቀጠና አስከፊ መዘዝ እንደሚያስከትል እንረዳለን። እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶች፣ ሕጻናት፣ ተፈናቃይ ቤተሰቦች፣ የጦር ጉዳተኛ ዜጎች፣ ሥራ አጥ ምሩቃን፣ አርሶ አደሮች፣ የመንግሥት ሠራተኞችና ተጋላጭ የኅብረተሰብ ክፍሎች ቀደም ሲል ያሳለፉት ሥቃይ ሊደገም አይገባም። ምንም ዓይነት የፖለቲካ ዓላማ እንደገና ለሚመጣ ሥቃይ፣ ለግዳጅ ቅስቀሳ፣ ለጥላቻ ንግግር፣ ለማስፈራራት ወይም የሰላማዊ ድምጾችን ለማፈን ምክንያት ሊሆን አይችልም።

4. ስለሆነም ይህ መድረክ የሁሉም የፖለቲካ ተዋናዮች፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት፣ የማህበረሰብ አንቂዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና በየትኛዉም እርከን ላይ ያሉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ዋነኛ ኃላፊነት እንደገና ግጭት እንዳይቀሰቀስ መከላከል፣ ሰላማዊ ዜጎችን መጠበቅ፣ እውነትን ማስከበር፣ ዲሞክራሲያዊ ምህዳሩን መከላከል እና ሰላማዊ፣ ሕገ-መንግሥታዊና ሕዝብ-ተኮር የፖለቲካ ሂደትን መደገፍ መሆኑን ያውጃል።

5. ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እና ለማህበረሰብ አንቂዎች የቀረበ ጥሪ፦ ሁሉም የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ጋዜጠኞች፣ አዘጋጆች፣ አሰራጮች፣ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች እና የአስተያየት መሪዎች የጦርነት ጋዜጠኝነትን፣ ቀስቃሽ ፕሮፓጋንዳዎችን፣ የጥላቻ ንግግሮችን፣ የተሳሳቱ መረጃዎችን፣ የግዳጅ ንቅናቄ ትረካዎችን እና የሕዝብ አስተያየትን ለቡድን ፍላጎት ማጭበርበርን እንዲያወግዙና ውድቅ እንዲያደርጉ እንጠይቃለን። መገናኛ ብዙኃን የፍርሃት፣ የወታደራዊ አስተሳሰብ ወይም የማህበራዊ መከፋፈያ መሣሪያ መሆን የለባቸውም። ይልቁንም እውነትን፣ ሰላምን፣ ተጠያቂነትን፣ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትን፣ የሕዝብ ውይይትን፣ የሰብአዊ ንቃተ-ህሊናን እና ዲሞክራሲያዊ ኃላፊነትን በማስተዋወቅ ሕዝብን ማገልገል አለባቸው።

6. የሕዝብን እውነተኛ ስጋቶች ስለማንጸባረቅና የግዳጅ ምልመላን ስለማውገዝ፦ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እና የማህበረሰብ አንቂዎች (አክቲቪስቶች) የሕዝቡን መሠረታዊና እውነተኛ ስጋቶች ድምፅ እንዲሆኑ አበክረን እናሳስባለን። በዚህ መሠረት፣ በምንም ዓይነት ሁኔታና ምክንያት በትግራይም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች ወደ አዲስ የጦርነት አዙሪት የሚመራ ግጭት እንዳይቀሰቀስ ለመከላከል በጽኑ እንሠራለን።

6.1 የመሬት ላይ እውነታው እንደሚያሳየው፣ በተለያዩ ምክንያቶች የትግራይ ወጣቶች ለተደጋጋሚ መክሸፍና ለከፋ እልቂት ሲዳረጉ የቆዩበት ታሪካዊ ምዕራፍ በአስቸኳይ ሊያበቃ ይገባል። በመሆኑም፣ በምንም ዓይነት መስፈርት ተገቢነት፣ ሕጋዊ መሠረት እንዲሁም ሰብአዊ ክብር በሌለው መልኩ በትግራይ ክልል ወጣቶች ላይ እየተፈጸመ ያለው አፈና እና የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላ (Forced Conscription) በአስቸኳይ እንዲቆም በጽኑ እንጠይቃለን፤ ለዚህም መርህ መከበር በሙያችንና በተሰማራንበት የማኅበራዊ መድረክ መስክ ሁሉ አስፈላጊውን ሁለንተናዊ ጥረት እናደርጋለን።

6.2 የመገናኛ ብዙኃን አጀንዳዎች በሙሉ በዋናነት በትግራይ ሕዝብ እውነተኛና አንገብጋቢ ፍላጎቶች ላይ ሊያተኩሩ ይገባል፤ እነኝህም፦ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በዘላቂነት መመለስ፣ የኑሮ መሠረቶችን ማደስ፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የጤና እና የትምህርት መሠረተ-ልማቶችንና አገልግሎቶችን በይፋ ማግኘት፣ የወጣቶች ደኅንነት ጥበቃ፣ የኢኮኖሚ ማገገም፣ የመንግሥት ሠራተኞች የተከማቸ ደሞዝ ክፍያ መፈጸም፣ በጦርነት የተጎዱ ማህበረሰቦችን መልሶ ማቋቋም፣ ማህበራዊ ፈውስ (Social Healing) እና የተጋላጭ ዜጎችን ሁለንተናዊ ደኅንነት መጠበቅ ናቸው። የሕዝቡ ጥልቅ ሥቃይና ዘላቂ ፍላጎት ከፖለቲካ መፈክሮች ወይም ከወታደራዊ ንግግሮች (Military Rhetoric) በስተጀርባ ሊደበቅ ወይም ሊታጠፍ አይገባም።

7. ለፖለቲካ ተዋናዮች የቀረበ ጥሪ፦ ሁሉም የትግራይ የፖለቲካ ተዋናዮችና ቡድኖች የሕዝቡን ሕልውና፣ ክብር እና የወደፊት ዕጣ ፈንታ ከፓርቲ ፍላጎት በላይ እንዲያስቀድሙ አበክረን እንጠይቃለን። ቀጠናውን ወደ አዲስ ጦርነት ሊገፋፉ ከሚችሉ ድርጊቶች፣ መግለጫዎች እና ቅስቀሳዎች እንዲቆጠቡ እናሳስባለን። በተጨማሪም የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት፣ በሕጋዊ አካሄዶች፣ በሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቶች እና በአካታች የዜጎች ተሳትፎ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

8. ለፌዴራል መንግሥት የቀረበ ጥሪ፦ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት የትግራይ ሕዝብ ሥቃይ ለማቆም በሕገ-መንግሥታዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ሰብአዊ፣ አስተዳደራዊ እና በሞራል ሥልጣኑ የተቻለውን ሁሉ እንዲያደርግ የጠነከረና አስቸኳይ ጥያቄ እናቀርባለን። የፌዴራል መንግሥቱ አዲስ ግጭትን ለመከላከል፣ ሰላማዊ ዜጎችን ለመጠበቅ፣ የሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ መልሶ ማገገምን ለመደገፍ፣ የሰላም ስምምነቶች መፈጸማቸውን ለማረጋገጥ እና በትግራይ ሕጋዊ፣ አካታችና ሰላማዊ አስተዳደር እንዲሰፍን ሁኔታዎችን ለማመቻቸት በአስቸኳይ፣ በጥበብ፣ በራስ የመግታት ስሜት፣ በርኅራኄ እና በኃላፊነት መንፈስ መንቀሳቀስ አለበት።

9. ልዩ ትኩረት የሚሹ ተግባራት፦ በተለይም የፌዴራል መንግሥቱ የሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነትና ክብር ለማረጋገጥ፣ ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታን ለማመቻቸት፣ የአገር ውስጥ ተፈናቃዮችን መልሶ ለማቋቋም፣ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለመመለስ፣ የምግብ ዋስትና ምላሾችን ለማጠናከር፣ ወጣቶችን ከአዲስ ወታደራዊ ቅስቀሳ ለመጠበቅ እና ሰላማዊና ሕገ-መንግሥታዊ የፖለቲካ እልባት ለማምጣት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ያለውን ጥረት እንዲያጠናክር እንጠይቃለን።

10. የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ፦ የፌዴራል መንግሥቱ እምነትን ለመገንባት፣ ውጥረትን ለመቀነስ እና ዘላቂ የሰላም ሂደትን ለመደገፍ የማህበረሰብ ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት መሪዎችን፣ ሴቶችን፣ ወጣቶችን፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተዋናዮችን፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን እና ሕጋዊ ተቋማዊ አካላትን ጨምሮ ሁሉንም ሰላማዊ ባለድርሻ አካላት እንዲያሳትፍ እናሳስባለን። የሕዝቡ ሥቃይ የተራዘመ የፖለቲካ ድርድርን ሊጠብቅ አይችልም። አስቸኳይ እና ተግባራዊ እርምጃ ያስፈልጋል።

11. ለልማት አጋሮች እና ለማህበረሰቡ የቀረበ ጥሪ፦ የልማት አጋሮች፣ ሰብአዊ ድርጅቶች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሴቶች ማህበራት፣ የወጣቶች ተወካዮች እና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግራይ ሕዝብ ለሰላም፣ ለክብር፣ ለማገገም እና ለዲሞክራሲያዊ መረጋጋት የሚያቀርበውን ጥያቄ እንዲደግፉ እና ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ እናቀርባለን። ለትግራይ የሚደረገው ድጋፍ ለሰላማዊ ዜጎች ጥበቃ፣ ለሰብአዊ ማገገም፣ ለተቋማዊ መደበኛ አሠራር፣ ለኑሮ መሠረት መታደስ፣ ለሥነ-ልቦና ፈውስ እና አዲስ ጦርነትን ለመከላከል ቅድሚያ መስጠት አለበት።

12. በማጠቃለያው፣ ሰላም ማለት ዝምታ ብቻ እንዳልሆነ ደግመን እናረጋግጣለን። ሰላም እውነትን፣ ፍትሕን፣ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓትን፣ ዲሞክራሲያዊ ውይይትን፣ ተጠያቂነት ያለበትን አመራር እና ለሰው ልጅ ሕይወት ክብር መስጠትን ይጠይቃል። ፍርሃት በነገሠበት የሕዝብ ሕይወት ውስጥ ዲሞክራሲ ሊኖር አይችልም። የጦርነት ፉከራ በሕዝብ አገልግሎት ምትክ በሰፈነበት ቦታ ልማት ሊታሰብ አይችልም። የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት ትርጉም የሚኖረው ሕዝብን ከተንኮል፣ ከጥላቻ እና ከዓመፅ ሲጠብቅ ብቻ ነው።

13. በዚህ መድረክ ማጠቃለያ ላይ፣ ኃላፊነት የተሞላበት ተግባቦትን፣ ለግጭት ተጋላጭ ያልሆነ (Conflict-sensitive) ጋዜጠኝነትን፣ በእውነታ ላይ የተመሰረተ ዘገባን፣ የዜጎች ትምህርትን እና ሕዝብ-ተኮር የውይይት ምህዳርን ለማሳደግ ቃል እንገባለን። ጦርነትን፣ የግዳጅ ምልመላን፣ ሳንሱርን፣ የጥላቻ ንግግርን እና የፖለቲካ ማስፈራራትን የተለመደ የሚያደርጉ ትረካዎችን ለመቋቋም ቁርጠኝነታችንን እንገልጻለን። መገናኛ ብዙኃንን እና አክቲቪዝምን ለሰላም፣ ለዲሞክራሲ፣ ለልማት፣ ለተጠያቂነት እና ለሰብአዊ ክብር መሣሪያ አድርገን ለመጠቀም እንስማማለን።

14. የትግራይ ሕዝብ ሰላም ይገባዋል ብለን እንያውጃለን። ደኅንነት ይገባዋል። ምግብ፣ መጠለያ፣ ትምህርት፣ ጤና ጥበቃ፣ የኑሮ መሠረት፣ ፍትሕና ተስፋ ይገባዋል። የሚጠብቀው አመራር፣ እውነትን የሚነግረው መገናኛ ብዙኃን እና የወደፊት ሕይወቱን የሚያገለግሉ ተቋማት ይገባዋል።

ይህ የአቋም መግለጫ የጋራ ጥሪያችን ነዉ፦

ወደ ጦርነት መመለስ የለም! በሥቃይ ፊት ዝምታ አይኖርም! ሕዝብን ለፖለቲካ ወይም ለወታደራዊ ዓላማ መጠቀሚያ ማድረግ ይብቃ! የትግራይ ሕዝብ ሥቃይ ሊቆም ይገባል፤ እያንዳንዱ ኃላፊነት ያለበት ተቋም አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ አለበት። በትግራይ ሰላም፣ ዲሞክራሲና ልማት ላይ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ተሳታፊዎች የጸደቀ።

ሰኔ 30 2018 አዲስ አበባ
Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ ፤ የውል እድሳት ምዝገባም ከዛሬ ሐምሌ 1 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና ...
08/07/2026

በአዲስ አበባ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ ፤ የውል እድሳት ምዝገባም ከዛሬ ሐምሌ 1 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት ታላቅ እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።

ከዚህ ቀደም በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።

ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት በይፋ መተግበር ይጀምራል።

ቢሮው እንዳመለከተው ፣ ይህ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔ በዘፈቀደ የተወሰነ ሳይሆን በከተማዋ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ተካሂዶ የነዋሪውን እውነተኛ የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ የተዘጋጀ ነው።

ይህ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ወቅቱንና የኢኮኖሚ ሁኔታውን ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያረጋግጥ ሲሆን ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ በመክፈል ከተደጋጋሚ መፈናቀልና ከስነ-ልቦና ስጋት ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያደርጋል።

ውሳኔው በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ ረገድ የጎላ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ቢሮው አረጋግጧል።


የአከራይ-ተከራይ ግንኙነትን በሕግ ማዕቀፍ በመምራት የጋራ ተጠቃሚነትን እናረጋግጣለን!!


Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party

የኢትዮጵያ እድገት!በድምሩ ኢትዮጵያ 10 ነጥብ 2 አካባቢ እድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል፡፡ ይሄ በአፍሪካ ትልቅ እድገት ነው፡፡ በሪፎርም ቃል የገባነው አስተማማኝ እድገት እናመጣለን ብለ...
07/07/2026

የኢትዮጵያ እድገት!

በድምሩ ኢትዮጵያ 10 ነጥብ 2 አካባቢ እድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል፡፡ ይሄ በአፍሪካ ትልቅ እድገት ነው፡፡ በሪፎርም ቃል የገባነው አስተማማኝ እድገት እናመጣለን ብለን ነው፤ ፈጣሪ ይመስገን ተሳክቶልናል፡፡ ተሳካልን ሲባል ግን እሩጫችን አለቀ ማለት አይደለም፡፡ የሩጫችን አቅጣጫ ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠናል፡፡ ገና ብዙ ስራ ይጠበቅብናል፡፡

ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ዶ/ር) ማብራሪያ የተወሰደ

#የጠሚሩምላሾች

Address

WWW. FIRITCH. COM
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nifas Silk Lafto Woreda 05 Prosperity Party posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share