Lemi Kura wereda 03 Communication

Lemi Kura wereda 03 Communication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Lemi Kura wereda 03 Communication, Government Organization, Ayat to Summit, Addis Ababa.

01/06/2026
01/06/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት በማስፈጸም ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ 12:00 ሰዓት ሠልፍ ላይ የነበረው ድምፅ ሰጪ ድምፅ ሰጥቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እንደሚቀጥል ያሳውቃል።

ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49 (4) መሠረት ቦርዱ በልዩ ሁኔታ የድምፅ መስጫ ሰዓት ሊያራዝም እንደሚችል ይደነግጋል።

01/06/2026

በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

01/06/2026

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው - የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

ምክር ቤቱ ይህንን የገለጸው በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተቋቋመውና የምርጫ ሂደቱን በቀጥታ በሚከታተልበት የክትትል ክፍል በሰጠው መግለጫ ነው።

በመግለጫው፤ መራጩ ሕዝብ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲሰፍን ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ከቤቱ በመውጣት ድምፅ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሶ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውንና ርዕዮተ-ዓለማቸውን በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት ካስተዋወቁ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ለመራጭነት መመዝገቡን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ባለው ሂደትም ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ መዋሉን ገልጿል።

ምክር ቤቱ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ባለው መዋቅር አማካኝነት መረጃዎችን ሲለዋወጥና ሂደቱን ሲከታተል እንደነበር የጠቆመ ሲሆን፤ እስካሁን ባለው ሂደት የጸጥታ አካላት፣ ታዛቢዎች እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች እያደረጉ ባለው ገለልተኛ አገልግሎት መደሰቱንም አስታውቋል።

በቀሪው የድምፅ አሰጣጥ ሂደትም ህዝቡ እስካሁን ባለው ጨዋነትና ትዕግሥት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጋራ ምክር ቤቱ ጥሪውን አቅርቧል።

01/06/2026

የመራጩ ህዝብ ሌሊት በነቂስ ወጥቶ መምረጥ በአገሩ ጉዳይ ላይ ያለዉን የእኔነት ስሜት የሚገልጽ ነው - ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

የመራጩ ህዝብ በለሊት በነቂስ ወጥቶ መምረጥ በአገሩ ጉዳይ ላይ ያለዉን የእኔነት ስሜት የሚገልጽ መሆኑን ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ገለጹ።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማሕበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በምርጫ ክልል 28 በዛጎል ትምህርት ቤት አካባቢ የምርጫ ጣቢያ ተገኝቸዉ ድምጽ ሰጥተዋል።

ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በዚሁ ወቅት እንደገለጹት መራጩ ህዝብ ከለሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ተሰልፎ እና ወረፋ ጠብቆ በመምረጥ ለምርጫዉ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት አሳይቷል።

የመራጩ ህዝብ በለሊት በነቂስ ወጥቶ መምረጥ በአገሩ ጉዳይ ላይ ያለውን የእኔነት ስሜት የሚገልጽ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ህዝቡ ለመምረጥ የማንም ቅስቀሳ እንደማያስፈልገው ያሳየ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ምርጫ አገር የምናስቀጥልበት የምናጸናበት እንዲሁም ዲሞክራሲ የምንለማመድበት ነው ያሉት ሙዓዘ ጥበባት ዳንኤል፣ ለአገር ዋጋ የሚከፍለው እና የማይከፍለው የሚለይበትም ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።

Address

Ayat To Summit
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura wereda 03 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share