ላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - Laska District Prosperity Party Office

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - Laska District Prosperity Party Office

ላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - Laska District Prosperity Party Office ይህ የላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ህጋዊ የማህበራዊ ድረ_ገጽ ነው ማነኛውም በዚህ ገጽ የሚለቀቁ ኃላፊነቱ ለጽ/ቤቱ ይሁን!

የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በባስኬቶ ዞን በመገኘት የበጎ ተግባር መርሐ-ግብር አካሄደነሐሴ 28/2018 ዓ/ምበጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎ ተጠቃሚነት በሚል መሪ ቃል ድን...
03/09/2026

የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ በባስኬቶ ዞን በመገኘት የበጎ ተግባር መርሐ-ግብር አካሄደ

ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም

በጎነት ለእህትማማችነት ለሴቶች ተሳትፎ ተጠቃሚነት በሚል መሪ ቃል ድንበር ተሻጋሪ የበጎ አድራጎት መርሐ-ግብር ነው የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ያካሄደው።

በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ክንፉ ሻቦ ብልጽግና ፓርቲ እንደ ሀገር ሰውን ታሳቢ ያደረገ ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አቅመ ደካሞችን ፈልጎ በመድረስ በልዩ ትኩረት እውነትን መሰረት ያደረገ በጎ ተግባር ላለፋት ሰባት አመታት እየተሰራ ቆይቷል ስሉም አቶ ክንፉ አክለዋል።

ይህ የበጎነት ተግባር በአንድ አካባቢ ተወስኖ እንዳይቀር መስፋት አለበት በማለት የወንድም አሪ ህዝብ ላደረገው ድንበር ተሻጋሪ በጎ አድራጎት አመስግነዋል።

የአሪ ዞን ህዝብ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ፓርቲ ነው ያሉ ስሆን ይህን መርህ በማድረግ በጎነት ድንበር ብሔር ሀይማኖት የለውምና ይህን ታሳቢ በማድረግ ወደ ባስኬቶ ዞን መጥተናል ብለዋል።

በበጎ ስራ ከዚህ ቀደም በርካታ አቅመ ደካሞች ተገልግለዋል ስሉም አክለዋል።

መደጋገፍና በጎ ተግባር አብሮነትን ከማጠናከር አንጻር ፋይዳው የጎላ መሆኑን የገለፁት የላስካ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጳውሎስ ሀይሌ ከበጎነቱ ባሻገር አሪ ዞን ለወንድም ባስኬቶ ሁለተኛዋ ከተማ ናት ብለዋል።

የአሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ወ/ሮ ይመኙሻል ተፈሪ በበኩላቸው እንደገጹት በጎ ተግባር ዘር፣ ሀረግ፣ ብሄርንና ኃይማኖትን ባለመለየት ሰው ለሆነው ሁሉ በልግስና የሚከወን መልካም ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ኃላፊ ወ/ሮ መብተ ግሮ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሴቶች ክንፍ በርካታ የበጎነት ስራዎች ተሰርተዋል ስሉ ገልጸዋል።

በጎነት የህዝብ ለህዝብ ያለውን መስተጋብር ከማጠናከር አኳያ ያለው ፋይዳ የጎላ ነው ያሉ ስሆን ይህ በሁሉም ማሕበረሰብ ተጠናክሮ የኢትዮጵያን የቀደመ አንድነት መስተጋብር ማጠናከር ይገባል ስሉም ወ/ሮ መብተ አክለዋል።

የበጎ ተግባር ስራው በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ አስተዳደር የአንድት አቅመ ደካማ ቤት ስራ ያስጀመረ ስሆን በላስካ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመገኘት ለወላድ እናቶች እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አድርጓል።
ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም
#ላስካ

ለህዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት የሚያጠናከር ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገለፀ።ላስካ፦ነሐሴ 28/2018 ዓ/ምየባስኬቶ ዞን ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት...
03/09/2026

ለህዝቡ የሚሰጠውን አገልግሎት የሚያጠናከር ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተገለፀ።

ላስካ፦ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም

የባስኬቶ ዞን ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 ዕቅድ ዝግጅት እንዲሁም የዕውቅናና ሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ ዋና አስተዳደር ኢ/ር በዛብህ ገበየሁ መንግሥት አገልግሎት አሰጣጡን በተሳለጠ መንገድ ለመስጠት ጠንካራ ሲቪል ሰርቫንት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ጠንካራ ሲቪል ሰርቫንት ለመፍጠር የተጀመረውን ሪፎርም ሥራዎችን እንደ ዞን ተግባራዊ እንዲሆን በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

በባለፈው ዓመት የተመዘገቡ ጠንካራ ሥራዎችን በማስቀጠል ደካማ ጎኖችን ለማሻሻል ልዩ ትኩረት በመስጠት የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን አመላክተዋል።

ሲቪል ሰርቫንቱ የተሰጠውን ተልዕኮ በአግባቡ ስወጣ የተገልጋዩ እርካታ ከፍ የሚያደርግና በህዝቡ ዘንድ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ዓይነተኛ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ሲቪል ሰርቫንቱ ይህንን አውቆ አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል።

የተሻለ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ማበረታቻ ሽልማትና እውቅና መስጠት ተገቢ መሆኑን ያመለከቱት አስተዳዳሪው የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተቋማት እውቅና ማበረታቻ ሽልማት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

የባስኬቶ ዞን ሲቪል ሰርቪስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባዩ በሽር ለህዝቡ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት አሳታፊና ግልጽ የሆነ ዕቅድ ማዘጋጀት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

በሲቪል ሰርቨስ ሴክቴሩ በኩል የሚወርዱ አሰራር መመሪያዎች እና አደረጃጀቶችን በተገቢዉ ሁኔታ መፈፀም ለዕቅድ አፈፃፀም ውጤታማነት የሚያበረከቱት አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ ጊዜያት ለህዝቡ ውጤታማ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት የሥራ ባህላችን በመቀየር የተገልጋይ እርካታ ለማሳደግ በትኩረት የሚሰራ መሆኑን ጠቁመዋል ።

መንግሥት የህዝቡን አገልግሎት አሰጣጥ ሥራን ለማሳለጥና ጠንካራ ሲቪል ሰርቪንት ለመገንባት በርካታ አሰራር ሥርዓቶችን እየዘረጋ መሆኑን አመላክተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ባለፈው በጀት ዓመት ተግባራት ስያከናወኑ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና መልካም ተሞክሮች ላይ በስፋት አንስተው ውይይት አድርገዋል።

በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ተቋማት እውቅናና ሽልማት በማበርከት መድረኩ ተጠናቋል።
ነሐሴ 28/2018 ዓ/ም
ላስካ

በዶኮ ጨሬ እና በሱባ ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ ያሉ የሞዴል ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግንባታ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኝ ተገለፀ።ላስካ፦ነሐሴ28/2018ዓ.ምበዶኮ ጨሬ እና በሱ...
03/09/2026

በዶኮ ጨሬ እና በሱባ ትምህርት ቤቶች እየተገነቡ ያሉ የሞዴል ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግንባታ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እንደሚገኝ ተገለፀ።

ላስካ፦ነሐሴ28/2018ዓ.ም

በዶኮ ጨሬ እና በሱባ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከ17.7 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት በመገንባት ላይ የሚገኘው የሞዴል ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የግንባታ ሥራ ምልከታ እና ግምገማ ተካሂዷል።

በዚህ የግንባታ ምልከታ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ የመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ሲሆን የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በቦታው ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ባደረጉት ምልከታ የግንባታው ሂደት በጥራት እና በፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው አፈጻጸሙን በጠንካራ ጎን ገምግመዋል።

የዞኑ ም/አስተዳዳሪ እና የትምህርት መምሪያ ኃላፊ ሰላምነሽ ጌታቸው(ዶ/ር) ከክልሉ ባለሙያዎች የተሰጠውን አስተያየት አበረታች እንደሆነ ገልፀው ይህ የሞዴል ቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ለህጻናት ጤናማ እና ምቹ የመማሪያ አከባቢን ይፈጥራል ብለዋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ሽብልቶ ፕሮጀክቱ ያለምንም መጓተት አሁን ላለበት ደረጃ እንዲደርስ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

እነዚህ ትምህርት ቤቶች ግንባታቸው በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እና ጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንድበቁ የምመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጥብቅ ክትትል ልያደርጉ እንደምገባ ተጠቁሟል።

ናታኒያ ኮንስትራክሽንም አስተባባርም እንደገለፁት እስካሁን ባለው ሥራ ሂደት በጥሩ ሁነኔታ እየሄደ እንደሆነ ገልፀዋል።
በዶኮ ጨሬ የምገነባው ትምህርት ቤት በፌደራል ትምህርት ሚኒስትር ሲሆን በሱባ ትምህርት ቤት የምገነባው ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክልሉ ትምህርት ቢሮ እንደሆነ ነው የተገለፀው።
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
ላስካ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት ወሰን ተሻጋሪ የክረምት የበጎ አገልግሎት ተግባር ለማከናወን ባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ እየገቡ ይገኛሉ።...
03/09/2026

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት ወሰን ተሻጋሪ የክረምት የበጎ አገልግሎት ተግባር ለማከናወን ባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ እየገቡ ይገኛሉ።

ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም

"በጎነት ለእህትማማችነት፣ ለሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት" በሚል መሪ ቃል የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሴቶች ክንፍ አስተባባሪነት ወሰን ተሻጋሪ የክረምት በጎ አገልግሎት ተግባር ለማከናወን በባስኬቶ ዞን ላስካ ከተማ እየገቡ ይገኛሉ።

በዚህ በጎ ተግባር ቆይታቸው የአንድ አቅሜ ዳካማ ቤት ግንባታ፤ ረጂ ሌላቸው ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፤ በሆስፒታል ያሉ ህሙማን ጉብኝት በማድረግ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ዋና ኃለፊ አቶ ክንፉ ሻቦ፤ የኣሪ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካ አቅም ግንባታ ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሕዝቅኤል ጋርዳ፤ የኣሪ ዞን ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ስመኝ ተስፋዬን ጨምሮ የሁለቱም መዋቅር በላድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
#ላስካ

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ የምግብ ሥርዓት ማጠናከር(PSRP) ፕሮጀክት በዓመት ውስጥ የተከናወኑ ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመላስካ፦ነሐሴ 28/2018ዓ/ምበባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ የ...
03/09/2026

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ የምግብ ሥርዓት ማጠናከር(PSRP) ፕሮጀክት በዓመት ውስጥ የተከናወኑ ዕቅድ አፈጻጸም ተገመገመ

ላስካ፦ነሐሴ 28/2018ዓ/ም

በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ የምግብ ሥርዓት ማጠናከር ፕሮጀክት (FSRP) በወረዳ ደረጃ ያከናወናቸው ሥራዎችና ያስመዘገባቸው ውጤቶች ተገምግሟል።

የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢንጂነር በዛብህ ገበየሁ የልማት ፕሮግራሞች ተጨባጭ የሕዝብ ጥቅም እንዲያመጡ በተግባር የሚታይ ውጤት ላይ ትኩረት ተደርጎ መሠራት እንዳለበት ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ የመስኖ መሠረተ ልማቱን በአግባቡ በመጠቀም የምርታማነት ደረጃውን እንዲያሳድግ ተጨማሪ የግንዛቤና የድጋፍ ሥራዎች መጠናከር እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፈለው በለጠ ፕሮጀክቱ ለሕዝቡ ከፍተኛ ጥቅም የሚያስገኙ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸው ማህበረሰቡ የተገነቡትን የመስኖ ልማት ሥራዎች በአግባቡ በመጠቀም የእርሻ ሥራውን በማስፋት ምርታማነቱን ማሳደግ እንዳለበት ጠቁመዋል።

በውይይቱ ወቅት ከተነሱ ሀሳቦች መካከልም የመስኖ ልማት ሥራዎች አጠቃቀምን በተመለከተ ለሕብረተሰቡ የግንዛቤ ሥራ መስጠት፣ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ተቋማት (APTC) ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የአርሶ አደሩን አቅም ማጎልበትና የግብርና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቁሟል።

የግብርና ባለሙያዎችም ከአርሶ አደሩ ጎን በመቆም የሚያስፈልገውን የቴክኒክና የሙያ ድጋፍ በወቅቱ ለመስጠት ብቁና ተግባራዊ አቅም ያላቸው ባለሙያዎችን የመገንባት ሥራ ትኩረት ልሰጠው እንደሚገባም አመልክተዋል።

የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት የምግብ ሥርዓት ማጠናከር ሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ታጋይ ገረሙ በወረዳ ደረጃ በፕሮጀክቱ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችንና የተገኙ ውጤቶችን የያዘ ዝርዝር ሪፖርት ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።

በመድረኩ የባስኬቶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኢ/ር በዛብህ ገበየሁ እና የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፈለው በለጠን ጨምሮ የዞን፣የዙሪያ ወረዳ፣የላስካ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
ላስካ

ወ/ሮ ፀሐይ ፋውንዴሽን በዙሪያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌዎች ለተወጣጡ አቅመ ደካሞች እና ወላጆቻቸውን ላጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።ላስካ፦ነሐሴ 27/2018ዓ.ምበክረምት ወራት ...
02/09/2026

ወ/ሮ ፀሐይ ፋውንዴሽን በዙሪያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌዎች ለተወጣጡ አቅመ ደካሞች እና ወላጆቻቸውን ላጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ።

ላስካ፦ነሐሴ 27/2018ዓ.ም

በክረምት ወራት እየተስፋፋ የመጣው የበጎ ተግባራት ስራ ዛሬም በወ/ሮ ፀሐይ ፋውንዴሽን በዙሪያ ወረዳ ከተለያዩ ቀበሌዎች ለተወጣጡ አቅመ ደካሞች እና ወላጆቻቸውን ላጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

የባስኬቶ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ በሀይሉ ባባሮ ይህ ተግባር ከምድር ብቻ ሳይሆን ከፈጣሪም ዘንድ ትልቅ በረከትን የሚያስገኝ መልካም ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር ተግባራትን የሚያከናውኑ ግለሰቦችንና ተቋማትን ሁሌም የሚያበረታታ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፈለው በለጠ ፋውንዴሽኑ በወረዳችን ለስድስት ዓመታት በሰብዓዊና በጎ ፈቃድ ሥራዎች ላይ በስፋት እየተሳተፈ እንደሚገኝ ጠቁመው በወረዳችን ለሚገኙ አቅመ ደካሞች ሰብዓዊ የሆኑ ድጋፎችን በማድረጋቸው አመስግነዋል።

በቀጣይም ፋውንዴሽኑ የሚያከናውናቸውን ድጋፎች ላይ በጋራ ለመስራት እና ለመደገፍ ቃል ገብተዋል።

የወይዘሮ ፀሐይ ፋውንዴሽን አስተባባሪ ወ/ሮ እታፋራው ትዕዛዙ በዛሬው ዕለትም ለ50 አቅመ ደካሞች የበዓል ማዋያ የሚሆን ለእያንዳንዳቸው 1,000 (አንድ ሺህ) ብር ጥሬ ገንዘብ እንዲሁም ለ26 ወላጅ አልባ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በዕለቱ የተደረገው ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን 152,800 (አንድ መቶ ሃምሳ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ) ብር መሆኑን ወ/ሮ እታፋራው ገልጸዋል።

በቀጣይም በየቀበሌው ችግር ውስጥ ላሉ ወገኖች ካለው በተሻለ የድጋፍ ሥራዎችን እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የወረዳው ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ደጄን፣የወረዳው ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አማረች አበራ ተገኝተዋል።
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም
ላስካ

በላስካ ዙሪያ ወረዳ የማህጸን ጫፍ ካንሰር የምርመራና የልየታ ሥራ ተከናወነላስካ፦ነሐሴ 27/2018ዓ.ም( በላስካ ዙሪያ ወረዳ ዶኮ ጫሬ ቀበሌ የማህጸን ጫፍ ካንሰር የምርመራና የልየታ ሥራ ተ...
02/09/2026

በላስካ ዙሪያ ወረዳ የማህጸን ጫፍ ካንሰር የምርመራና የልየታ ሥራ ተከናወነ

ላስካ፦ነሐሴ 27/2018ዓ.ም(

በላስካ ዙሪያ ወረዳ ዶኮ ጫሬ ቀበሌ የማህጸን ጫፍ ካንሰር የምርመራና የልየታ ሥራ ተከናወነ።

የላስካ ዙሪያ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አድመኘው ሚስሎ የማህጸን ጫፍ ካንሰርን በጊዜ መለየትና መከላከል የእናቶችን ሞት ለመቀነስ ወሳኝ በመሆኑ ለምርመራና ልየታ ሥራዎች ልዩ ትኩረት መሰጠት እንዳለበት ገልጸዋል።

የላስካ ዙሪያ ወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አማረች አበራ የክረምት በጎ ፍቃድ የትኩረት መስክ አካል የሆነዉ የማህጸን ጫፍ በር ካንሰር ለመከላከል ሁሉም ሴቶች የተሰጠውን የምርመራ ዕድል በመጠቀም በምርመራው በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ስለበሽታው አስከፊነት መከላከያና በጊዜ የሚደረግ ምርመራ ለሴቶች ጤና ጥበቃ ያለውን ጠቀሜታ ማስገንዘብም አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

የላስካ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የማህጸን ጫፍ ካንሰር ምርመራ ሥራ ሂደት አስተባባሪ ወ/ሮ ህልና ገዛህኝ ሁሉም ሴቶች የማህጸን ጫፍ ካንሰር ምርመራን በመውሰድ የጤናቸውን ሁኔታ በወቅቱ ማወቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል።

በዶኮ ጫሬ ቀበሌ የተጀመረውን የምርመራና የልየታ ሥራ በማጠናቀቅ በቀጣይ በወረዳው ሌሎች ቀበሌያትም ለማከናወን መርሃ ግብር መያዙን ገልጸዋል።
የማህጸን ጫፍ ካንሰርን በጊዜ መለየት ሕይወትን ማዳን ነው።
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ማንሰራራት !የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች የሚከበር ይሆናል።ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስ...
02/09/2026

የኢትዮጵያ ማንሰራራት !

የዘንድሮው የጳጉሜን ወር "የኢትዮጵያ ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ መርሃ-ግብሮች የሚከበር ይሆናል።

ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ዘርፈ-ብዙ ድሎችን እያስመዘገበች፣ ውስብስብ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ፈተናዎችን በፅናትና በፈጠራ በመሻገር፣ በአሁን ወቅት በማንሠራራት ምዕራፍ ላይ የምትገኝ ሀገር ሆናለች።

የጳጉሜን ወር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ዘይቤ ውስጥ ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ ድልድይ በመሆን የተገኙ ወረቶች የሚደመሩበት እንዲሁም ለቀጣዩ ዓመት የከፍታ ጉዞ አዲስ ተስፋ የሚሰነቅበት ልዩ ሀገራዊ መለያችን ነው።

የዘንድሮው የጳጉሜን ቀናት አከባበር የነበሩ ጥንካሬዎችን የሚያስቀጥል፣ የታዩ ክፍተቶችን የሚያርም፣ አዳዲስ የፈጠራ ስልቶችን ታሳቢ ያደረገ፣ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በሚገባ የሚጠቀም፣ የተመዘገቡ ትላልቅ ስኬቶችን የሚያስታውስ፣ አዳዲስ ብስራቶችን የሚያበስር በመሆሃ በሳቢ ኹነቶችና የንቅናቄ መንገዶች የሚመራ ይሆናል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀናት አከባበር ከቀደሙት ዓመታት በተለየ መልኩ በብሥራት፣ በተስፋ እና በሁለንተናዊ የብልጽግና ራዕይ ላይ ያተኮረ እንደሚሆንም በቀረበው የማስፈፀሚያ ዕቅድ ተመላክቷል።

የ 2018 ዓ.ም የጳጉሜን ቀና፤ ጳጉሜን 1 (የእመርታ ቀን)፣ ጳጉሜን 2 (የማንሰራራት ቀን)፣ ጳጉሜን 3 (የጽናት ቀን)፣ ጳጉሜን 4 (የኅብር ቀን) እንዲሁም ጳጉሜን 5 (የነገ ቀን) በሚሉ መርሃ-ግብሮች በድምቀት የሚከበሩ ይሆናል።

የባስኬቶ ዞን አስተዳደር የወላይታ  ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ላይ ለመታደም ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከላቸውን ጥሪ ተቀብለዋል።ጊፋታ በዩኔስኮ( UNESCO) ከመመዝገቡ ጋር ተያይ...
01/09/2026

የባስኬቶ ዞን አስተዳደር የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ላይ ለመታደም ከወላይታ ዞን አስተዳደር የተላከላቸውን ጥሪ ተቀብለዋል።

ጊፋታ በዩኔስኮ( UNESCO) ከመመዝገቡ ጋር ተያይዞ "የጊፋታ ብስራቶች ለህዝባችን ከፍታ!!" በሚል መሪ ቃል በመስከረም 10/2019 ዓ.ም የወላይታ ብሔር ተወላጆችና ከሀገር ውስጥና ውጪ የተጋበዙ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይከበራል።

በላስካ ዙሪያ ወረዳ ህገ-ወጥ የቡና ዝውውርን በመቆጣጠር ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የፀጥታ አካላት ዕውቅና ተሰጠላስካ፦ነሐሴ 26/2018/ዓ.ምበላስካ ዙሪያ ወረዳ በቡና ግብረ ኃይል አዘጋጅነት...
01/09/2026

በላስካ ዙሪያ ወረዳ ህገ-ወጥ የቡና ዝውውርን በመቆጣጠር ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የፀጥታ አካላት ዕውቅና ተሰጠ

ላስካ፦ነሐሴ 26/2018/ዓ.ም

በላስካ ዙሪያ ወረዳ በቡና ግብረ ኃይል አዘጋጅነት በ2017/2018 ዓ.ም በህገ-ወጥ የቡና ንግድ እና ዝውውር ላይ ጠንካራ ቁጥጥር በማድረግ አበረታች ውጤት ላስመዘገቡ የፀጥታ አካላት የዕውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በዚህ የዕውቅና እና የማበረታቻ መርሃ ግብር ላይ የላስካ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፈለው በለጠ ጨምሮ የቡና ግብረ ኃይል አባላት ተገኝተዋል።

የዕውቅናው የተሰጠው በወረዳው ውስጥ ህገ-ወጥ መንገዶችን በመጠቀም በቡና ንግድ እና ዝውውር ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎችን እንዲሁም ግለሰቦችን በከፍተኛ ክትትል በቁጥጥር ስር በማዋል ሀብትን ከብክነት በመታደግ ለላቀ ተግባር ለፈጸሙ የፀጥታ አካላት ነው የተደረገው።

የላስካ ወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፈለው በለጠ፣ የፀጥታ አካላቱ የቡና ምርት በህገ-ወጦች እጅ እንዳይወድቅ ሌት ተቀን ያደረጉትን ጥረት እና የተገኘውን ውጤት አድንቀዋል።

በቀጣይም ይህንኑ የሀገርን ኢኮኖሚ የመጠበቅ እና ህገ-ወጥነትን የመከላከል ስራ ይበልጥ አጠናክረው እንዲቀጥሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአሁኑ ወቅትም እጅግ በጣም ቁጥር ያላቸው በህገ ወጥ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች እንዳሉ በመገንዘብ የፀጥታ አካላት ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በመጠበቅ እና በመቆጣጠር ሙያዊ ግደታቸውን እንድወጡ አሳስበዋል።
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
ላስካ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ላስካ ዙሪያ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - Laska District Prosperity Party Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share