አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network

አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network ለተጨቆነው ህዝብ ድምጽ ለመሆን የተቋቋመው የሚድያ ስለሆነ አድማጭ ተመልካቾቻችን ኮፒ ሼር ላይክ ኮሜንት በማድረግ ቤተሰብ እንድትሆኑ የአክብሮት ግብጀችን ነው ።

በማዕከላዊ ጎንደር በጭልጋ በአይከል ከተማ በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 9 በሀሰተኛ የብር ኖት ሲገበያይ የተያዘ አጭበርባሪ ነው። በጥሬ ገንዘብ የሚደረጉ ግብይቶች ላይ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።
16/08/2026

በማዕከላዊ ጎንደር በጭልጋ በአይከል ከተማ በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 9 በሀሰተኛ የብር ኖት ሲገበያይ የተያዘ አጭበርባሪ ነው። በጥሬ ገንዘብ የሚደረጉ ግብይቶች ላይ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

ሰበር መረጃ📍እስክንድር ነጋ ማረፉን የሚያመላክቱ  መረጃዎች በስፋት እየወጡ ነው!"አፋብን" የሚባል የወያኔ ስሪት ሲመሰረት የተሰጠውን የጫካ ስልጣን አይመጥነኝም በማለት እምቢ ያለው እስክንድ...
16/08/2026

ሰበር መረጃ
📍እስክንድር ነጋ ማረፉን የሚያመላክቱ መረጃዎች በስፋት እየወጡ ነው!

"አፋብን" የሚባል የወያኔ ስሪት ሲመሰረት የተሰጠውን የጫካ ስልጣን አይመጥነኝም በማለት እምቢ ያለው እስክንድር ነጋ በነአስረስ ማረ ትዕዛዝ ከሸዋ ታፍኖ ወደጎጃም ከተወሰደ በኋላ በእስር ላይ ቆይቶ ሰሞኑን ስለመሞቱ ከቡድኑ አፈትልከው የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

እስክንድር ነጋ ጎጃም አገው ምድር ጫራ በሚባል አካባቢ ታስሮ እንደቆየ እና መከላከያ ሰራዊቱ በአካባቢው ከሚንቀሳቀሰው የፋኖ ታጣቂ ጋር ባደረገው ውጊያ መሞቱን የደረሰን መረጃ ያመላክታል፡፡

እንደደረሰን መረጃ ከሆነ እስክንድር በታሰረበት አካባቢ ሲጥብቁት የነበሩት የፋኖ ታጣቂዎች በሙሉ ያለቁ ሲሆን እስክንድርም ልክ ከዚህ በፊት በሸዋ እንደሞተው ተስፋዬ መካሻ በታሰረበት ሞ ቷል፡፡ ነገር ግን እስክንድርን አፍነውት የቆዩት እነአስረስ ማረ ስለሞቱ ምንም መረጃ እንዳይወጣ እየተፍጨረጨሩ ነው፡፡

ትንሽ ቆይተው በድሮን በተወሰደ እርምጃ ተገድሏል የሚል መግለጫ ለመስጠት ውስጥ ለውስጥ እንቅስቃሴ ጀምረዋል፡፡ እስክንድር ነጋ ሰሞኑን በሚዲያ በስፋት ከምንመለከው የሸዋ ፋኖ ውስትም የጠፋው ጎጃም ተወስዶ ታፍኖ ስለቆየ ነው፡፡ የሚገርመው እነዘመነ ካሴ እስክንድርን ካፈኑት በኋላ በሚዲያ "እስክንድር" የመንግስት ተላላኪ የሚል ዘመቻ ከፍተውበት የቆዩትም እንዲሁ ቀስ አድርገው ከራሳቸው ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማሰናበት ስለፈለጉ ነው፡፡ ለማንኛዉም እስክንድር እቺን አለም ተሰናብቷል! የሽብር እንቅስቃሴ መጨረሻስ ይኼውም አይደል!!!

ለሠላም ተስፋ ሰጭ መረጃ‼የፌዴራል መንግስት እና ህወሓት በናይሮቢ ሊወያዩ ነው ተባለ‼የፌዴራል መንግስት እና የህወሓት አመራሮች በሚቀጥለው ሳምንት በኬንያ ናይሮቢ ለዳግም ውይይት ቀጠሮ መያዛ...
16/08/2026

ለሠላም ተስፋ ሰጭ መረጃ‼

የፌዴራል መንግስት እና ህወሓት በናይሮቢ ሊወያዩ ነው ተባለ‼

የፌዴራል መንግስት እና የህወሓት አመራሮች በሚቀጥለው ሳምንት በኬንያ ናይሮቢ ለዳግም ውይይት ቀጠሮ መያዛቸው ተሰምቷል።

📌 በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ትግራይ አነፃራዊ ሰላም ሰፍኖ የቆየ ቢሆንም፣ በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ክንፍ ስምምነቱን በመጣስ ዳግም የጦርነት እንቅስቃሴ በመጀመሩ እና የትግራይ ህዝብ "ጦርነት ይበቃናል" ጥሪ በማቅረቡ ነው።

📌 ሂደቱን ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ፣ ዊሊያም ሩቶ፣ እና ኡሁሩ ኬንያታ ይመሩታል ተብሏል።

📌ከሰሞኑ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌማን ደደፎ "ከሕወሓት ጋር ምንም ዓይነት ድርድር ሊደረግ አይገባም" በማለት መግለፃቸው የድርድር መንገድ መጀመሩን ጠቋሚ ነው በሚል ብዙዎች ሲገልፁ ነበር።
👉በየትኛውም መንገድ ይሁን ብቻ ጦርነትን የሚያስቀር ነገር ይፍጠርልን‼ሠላም ለሀገራችን ሠላም ለህዝባችን‼

“በሸረሪና ለሞቱ ወጣቶች ተጠያቂው ህወሓት ነው”❗ስምረት ፓርቲ በትግራይ ሸረሪና እና ራያ አካባቢ በተከሰተው ጦርነት የተጎዳውን የትግራይ ወጣት በተመለከተ ሕወሓትን ተጠያቂ አድርጓል።ፓርቲው ...
13/08/2026

“በሸረሪና ለሞቱ ወጣቶች ተጠያቂው ህወሓት ነው”❗
ስምረት ፓርቲ በትግራይ ሸረሪና እና ራያ አካባቢ በተከሰተው ጦርነት የተጎዳውን የትግራይ ወጣት በተመለከተ ሕወሓትን ተጠያቂ አድርጓል።

ፓርቲው ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ በትግራይ የሚንቀሳቀሰው ሕወሓት ከሕግደፍና ከሌሎች ጸረ-ሰላም ኃይሎች ድጋፍ አገኛለሁ በሚል የተሳሳተ ስሌት በሸረሪና እና በራያ ጦርነት መክፈቱን ገልጿል።

በዚህም በተከሰተው የአጸፋ ምላሽ ሕይወታቸውን ላጡ የትግራይ ወጣቶች ሕወሓት ተጠያቂ እንዲሆን ፓርቲው ጠይቋል። በተጨማሪም የትግራይ ሕዝብና ወጣቶች ለጥቂት ግለሰቦች የሥልጣን ፍላጎት ሲባል የጦርነት ሰለባ መሆናቸው እንዲያበቃ እና ተጠያቂዎችም በሕግ እንዲጠየቁ አሳስቧል።

የሸረሪና ምስሎች‼ 📌ከራያ አላማጣ አዲስ መረጃ ተካቷል።በሱዳን ድንበር ሸረሪና አካባቢ የህወሓት አርሚ 70ና ሌሎችም በቅንጅት ትንኮሳ መክፈታቸውን ተከትሎ የፌደራል መንግስቱ የፀጥታ ኃይሎች ...
13/08/2026

የሸረሪና ምስሎች‼

📌ከራያ አላማጣ አዲስ መረጃ ተካቷል።

በሱዳን ድንበር ሸረሪና አካባቢ የህወሓት አርሚ 70ና ሌሎችም በቅንጅት ትንኮሳ መክፈታቸውን ተከትሎ የፌደራል መንግስቱ የፀጥታ ኃይሎች ጥቃቱን በመመከት ከህውሃት የሸረሪና ካምፕ የተማረኩ እና በአሰሳ የተገኙ የጦር መሳሪያዎች ምስል ይፋ ሆኗል።

​ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የህወሓት አርሚ 70 በሱዳን ድንበር ሸረሪና አካባቢ ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ፣ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በወሰደው የተቀናጀ የአፀፋ እርምጃ አካባቢውን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ሥር ማዋል ችሏል።

​በተካሄደው የአፀፋ እርምጃና ቀጣይ አሰሳ በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ቁሳቁሶች የተማረኩ ሲሆን፣ የደረሱት የምስል መረጃዎችም በቦታው የተያዙ ታጣቂዎችን፣ የተማረኩ መሳሪያዎችን እና ተሽከርካሪዎችን የሚያሳዩ ናቸው።

በሌላ በኩል በራያ አላማጣ ከሰሞኑ መረዋና አካባቢው ጠንካራ የተባለ የድሮን ጥቃት መፈፀሙን ተከትሎ የህውሃት ወደፊት ተራምዶ ውጊያን አፍጥኖ የመጀመሩ ሂደት ተቀዛቅዞ መታየቱን ምንጮች ጠቁመዋል።ባለፉት ቀናት ሊጀመር ይችላል በሚል ስጋት ፈጥሮ የነበረው አሁን በመጠኑም ቢሆን ሰከን ማለት እየታየ በመሆኑ ደስ ይላል።ሁሉንም ወደ ሰላም ይቀይርልን ።

Agew Media Network የህዝብ ድምፅ

«ህወሓት 27 ዓመት ለዋግ ህዝብ ያተረፈው በደልና መገለልን ብቻ ነው» - አቶ አላምረው ይርዳውህወሓት በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ በነበረበት 27 ዓመታት ውስጥ ለዋግ ኽምራ ህዝብ ያከናወነው ም...
12/08/2026

«ህወሓት 27 ዓመት ለዋግ ህዝብ ያተረፈው በደልና መገለልን ብቻ ነው» - አቶ አላምረው ይርዳው

ህወሓት በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ በነበረበት 27 ዓመታት ውስጥ ለዋግ ኽምራ ህዝብ ያከናወነው ምንም አይነት ጠቃሚ የልማትም ሆነ የማህበራዊ አገልግሎት ስራ አለመኖሩን የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ሊቀመንበር አቶ አላምረው ይርዳው ገለጹ።

ሊቀመንበሩ ከአዲስ ሪፖርተር ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፣ ህወሓት ሀገር በገዛበት ረጅም ጊዜ ውስጥ የአገው ህዝብ ከመገለልና ከበደል ውጭ ያገኘው አዎንታዊ ነገር የለም። አካባቢው በኢኮኖሚ፣ በጤና እና በትምህርት መሰረተ ልማቶች ወደ ኋላ እንዲቀር መደረጉንም አብራርተዋል።

አክለውም ህወሓት ዛሬ ከስልጣን ከተወገደ በኋላ ህዝቡን ወዳጅ ለማስመሰልና ለመቃረብ የሚያደርገው ጥረት ፍጹም የማታለያ ስልት መሆኑን ተናግረዋል። ቡድኑ በአሁኑ ወቅት ከህዝቡ ጋር ወዳጅነት ለመፍጠር የሚጥረው ለህዝቡ አስቦ ሳይሆን፣ ለራሱ የጥፋት አላማ የሚሰለፍና መጠቀሚያ የሚሆን ኃይል ለመፈለግ ብቻ እንደሆነ አስገንዝበዋል።

እንደ አቶ አላምረው ገለፃ፣ በአካባቢው ከተከናወኑ ጥቂት ስራዎች ይልቅ ህዝቡ ያጣውና ያጣጣመው በደል ይበልጣል።

በተለይም በዋግ ኽምራ ዞን የሚኖረው ህዝብ ላለፉት አያሌ ዓመታት የንጹህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድ እና የጤና ተቋማት እጥረት ሲፈታተነው መቆየቱ በወቅቱ የነበረው አስተዳደር ለህዝቡ ትኩረት አለመስጠቱን በግልጽ ያሳያል ብለዋል።

በመጨረሻም የአገው ህዝብ ላለፉት ዓመታት ያነሳቸውን የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና የፍትህ ጥያቄዎች ዘላቂ በሆነ መንገድ ለመመለስ የተቀናጀ ጥረት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

 !!የክልሎች አወቃቀር ይቀጥላል:- የአገው፣የወሎ፣የወላይታ እና የጉራጌ ጥያቄዎች በአስቸኳይ እልባት ሊያገኙ ነው።የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን ሰላም ለማረጋገጥ መላው የኢትዮጵያ ብ...
12/08/2026

!!
የክልሎች አወቃቀር ይቀጥላል:- የአገው፣የወሎ፣የወላይታ እና የጉራጌ ጥያቄዎች በአስቸኳይ እልባት ሊያገኙ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያን ሰላም ለማረጋገጥ መላው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችን እያወያየ(እያመካከረ እንደሚገኝ ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ ተመካካሪዎች የሀገሪቱ ወሳኝ አጀንዳ በሆነው " " ስር ተመካካሪዎች የክልሎች አወቃቀር ይቀጥል በሚለው የ500 ቡድን የሀገራዊ ምክክር ተመካካሪዎች ተስማሙ፡፡

አገሪቱ የምትከተለው የመንግስት ሥርዓት ምን ይሁን? ለሚለው ተመካካሪዎቹ ኢትዮጵያ በፕሬዚዳንት ትመራ በሚለው ላይ ሙሉ ለሙሉ ተስማምተዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ከየት ይመረጥ? ሥርዓቱ ፓርላምታዊ ሆኖ ከፓርላማ ይመረጥ? ወይስ ሙሉ በሙሉ ሥርዓቱ ፕሬዚዳንታዊ ሆኖ በህዝብ ቀጥታ ይመረጥ የሚለው ግን ሁሉምን አስማሚ አልሆነም ፡፡

በዚህም በመንግሥት አደረጃጀት እና ቅርፅ በፖለቲካ ሥርዓት፣ ውክልና የምርጫ ሥርዓት ስር ሲመከር የሰነበተው ተመካካሪ ቡድን እነዚህ አጀንዳዎች በልዩነት ወደ ቀጣይ ምዕራፍ እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ውክልና ምን ይምሰል? የሚለውም ሌላው በልዩነት ያለፈ ንዑስ አጀንዳ ነው ፡፡ ምንጭ:- ያሬድ እንዳሻው
Agew Media Network የህዝብ ድምፅ

መንግስት ያቀረበውን የይቅርታ ሰነድ አንፈርምም ያሉ ተከሳሾች ታወቁ።መንግስት ያቀረበውን የይቅርታ ሰነድ አንፈርምም ያሉ ተከሳሾች እነማን እንደሆኑ የሚያመላክት ስም ዝርዝር የወጣ ሲሆን በዋና...
12/08/2026

መንግስት ያቀረበውን የይቅርታ ሰነድ አንፈርምም ያሉ ተከሳሾች ታወቁ።
መንግስት ያቀረበውን የይቅርታ ሰነድ አንፈርምም ያሉ ተከሳሾች እነማን እንደሆኑ የሚያመላክት ስም ዝርዝር የወጣ ሲሆን በዋናነት የቀድሞው የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል ዮሐንስ ቧያለው፣ ዶ/ር ወንደወሰን አሰፋ፣ ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው፣ መምህርት መስከረም አበራ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ጎበዜ ሲሳይ፣ ገነት አስማማው ይገኙበታል፡፡

ሙሉ ዝርዝራቸው ተከታዩ ነው፡-

1. አቶ ዮሐንስ ቧያለው
2. ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም
3. ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው
4. ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ
5. ዶ/ር መሠረት ቀለመወርቅ
6. ዶ/ር ዘሪሁን ባህሪው
7. ጋዜጠኛ መስከረም አበራ
8. ጋዜጠኛ ገነት አስማማው
9. ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው
10. ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ
11. ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ
12. አቶ አለልኝ ምህረት
13. አቶ መንበር አለሙ
14. አቶ ማይክ መላክ
15. አቶ አሳምነው ታደሠ
16. አቶ ደሳለኝ እጅጉ
17. አቶ እሱባለው በለጠ
18. አቶ እስክንድር ሽፈራው
19. አቶ መሰለ ቸሩ
20. ኢ/ር ፍርዱ ተፈራ
21. አቶ ጫኔ ዘየደ
22. ወ/ት ሃሊማ አህመድ
23. ወ/ት ህይወት አለማየሁ
24. አቶ ሲሳይ መልካሙ
25. አቶ ታደሰ ወዳይነው
26. አቶ በላይ ሲሳይ
27. አቶ ያሬድ ግርማ
28. አቶ ማረው ስለሺ
29. አቶ ሠለሞን ተፈሪ
30. አቶ ሙሉቀን ተስፋዬ

ደብዳቤው እንደሚያመላክተው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ከመንግስት ጋር በጀመረው ውይይት በመጨረሻ ፈርሙ የተባሉት ተከታዮቹን ጉዳዮች ያካትታል፡-

“በአማራ ክልል ለተፈጠረው ቀውስ ኃላፊነት ውሰዱ፤ በአማራ ክልል በተፈጠረው ቀውስ ለሞቱ ሰዎች፣ ለቆሰሉ ሰዎች (በየመዝገብ ቁጥሩ ይለያያል) ፈጽመናል ብላችሁ እመኑ፤ ለወደመው በበሊዮን የሚገመት ንብረት
ፈጽመናል ብላችሁ እመኑ፤ ሀገሪቱ በአማራ ትውፊቶችና እና እሳቤ ካልተመራች ማለታችሁን ወንጀል ነው በሉ፤ ያለ አግባብ የተወሰዱ የአማራ ርስቶች መመለስ አለባቸው ስለማለታቸው እና ይህም ወንጀል መሆኑን እንዲያምኑ” በቅድመ ሁኔታ እንደቀረበላቸው አዲስ ማለዳ የተመለከተችው ያመላክታል፡፡

ይህንን ተከትሎ ተከሳሾቹ በሰጡት ምላሽ “እኛ ወንጀለኛ ነን ብለን አንፈርምም፤ በህግም፣ በሞራልም፣ በታሪክም ተቀባይነት የለውም ብለን አንፈርምም” ብለዋል፡፡

አክለውም፤ “የአማራ ህዝብ ጥያቄዎችም ህጋዊ ናቸው ብለው እንደሚያምኑ በመግለጽ የ60 ሚሊዮን ህዝብን መልካም እሴት ወንጀል ነው ብለን አውቀን አንሰጥም ወንጀልም አይደለም፤ በህገመንግስት እና በዓለምአቀፍ ህጎች ነፃ ሆኖ የመኖር መብታችንን ፈቅደን አንተውም፤ በህግ የተከለከለውን ራስን መከላከል እና ራሳችንን ወንጀለኛ አናደርግም” ሲሉ ምላሽ መስጠታቸውን መመልከት ተችሏል፡፡

ሰበር‼️ከ600 በላይ የህውሓት ታጣቂዎች ከምሽግ አመለጡ‼️በህውሓት  አርሚ 15 ፣ 22 እና 26 ውስጥ የነበሩ ከ600 በላይ ታጣቂዎች በዛታ አካባቢ ለጦር'ነት ዝግጅት ወደ ምሽግ ተገደው ገ...
12/08/2026

ሰበር‼️
ከ600 በላይ የህውሓት ታጣቂዎች ከምሽግ አመለጡ‼️

በህውሓት አርሚ 15 ፣ 22 እና 26 ውስጥ የነበሩ ከ600 በላይ ታጣቂዎች በዛታ አካባቢ ለጦር'ነት ዝግጅት ወደ ምሽግ ተገደው ገብተው የነበር ቢሆንም ፤ ሌሊት ምሽጉን ጥለው መኮብለላቸው ታውቋል፡፡
አጥፊው የህውሓት ቡድን ወጣቱን አስገድዶ ወደ ጦር'ነት ማዕበል በመክተት ስልጣኑን ለማስቀጠል ያደመመው እኩይ እቅድ፣ በታጣቂዎቹ የበሰለ ውሳኔ አ'ፈ'ር ድ'ሜ በል'ቷል::

አብን ከሀገራዊ ምክክሩ ሊወጣ እንደሚችል አስጠነቀቀ‼የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳለው ገልጾ፣ አፋጣኝ ማስተካከያ ካልተደረ...
11/08/2026

አብን ከሀገራዊ ምክክሩ ሊወጣ እንደሚችል አስጠነቀቀ‼

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት ላይ ከፍተኛ ስጋት እንዳለው ገልጾ፣ አፋጣኝ ማስተካከያ ካልተደረገ ከምክክሩ ሊወጣ እንደሚችል አስጠነቀቀ።

ፓርቲው ለኮሚሽኑ ባስገባው አቤቱታ፤ በሂደቱ ላይ አካታችነት፣ ገለልተኝነት እና ተዓማኒነት መጎደሉን ጠቅሷል። በተለይም ያልተመጣጠነ የተሳታፊዎች ስብጥር፣ የመንግሥትና የብልፅግና አመራሮች ያልተገባ ተፅዕኖ፣ የባለሙያዎች ፓነል ገለልተኝነት ማጣት እንዲሁም የአዲስ አበባን ጉዳይ በተደራጀ የቁጥር ብልጫ ለመወሰን የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ተቃውሟል።

በመሆኑም አብን አዳዲስ ተሳታፊዎችን መጨመር በአስቸኳይ እንዲቆም፣ በገለልተኛ አካል የሂደት ኦዲት እንዲደረግ እና በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ የሚደረገው ውይይት እንዲቆም ጠይቋል። ኮሚሽኑ ጥያቄዎቹን ችላ ብሎ ወደ ቀጣይ ምዕራፍ የሚሸጋገር ከሆነ ከምክክሩ የመውጣት እርምጃ እንደሚወስድ አሳስቧል።

Agew Media Network የህዝብ ድምፅ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አገው ሚድያ ኔትዎርክ Agew Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share