Addis Ababa Tourism Commission

Addis Ababa Tourism Commission Addis Ababa Tourism Commission

08/05/2026
አፍሪካውያን ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልበአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬ...
07/05/2026

አፍሪካውያን ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከል

በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎበኙ።

አዲስ አበባ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል!
አህጉራዊ ትስስር በዲጂታል አለም!

Addis Ababa Tourism Commission
Visit Addis Ababa

አፍሪካዊያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በአዲስ አበባ ንግድ ሥራዎች ድርጅት ስር የሚገኘውን የጉለሌ እንጀራ ማምረቻ ማዕከልን ጎበኙ። ተጽዕኖ ፈጣሪዎቹ በማዕከሉ ተወዳጅ የኢትዮጵያን ም...
07/05/2026

አፍሪካዊያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በአዲስ አበባ ንግድ ሥራዎች ድርጅት ስር የሚገኘውን የጉለሌ እንጀራ ማምረቻ ማዕከልን ጎበኙ።

ተጽዕኖ ፈጣሪዎቹ በማዕከሉ ተወዳጅ የኢትዮጵያን ምግብ የሆነውን እንጀራ የመጋገር ሂደትን የተመለከቱ ሲሆን ይህ በዲጂታል መድረኮች ላይ የሀገራችንን ባህልና የምግብ ስርአታችንን በስፋት ለማስተዋወቅ ያግዛል።

Addis Ababa Tourism Commission
Visitaddis_etX

የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ።ሚያዝያ 29/2018 (ቱሪዝም ኮሚሽን)የአፍሪካን እውነተኛ ገጽ...
07/05/2026

የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ተሳታፊዎች የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኙ።

ሚያዝያ 29/2018 (ቱሪዝም ኮሚሽን)

የአፍሪካን እውነተኛ ገጽታ ለዓለም ለማስተዋወቅና የዲጂታል ትርክቱን በባለቤትነት ለመምራት ያለመው የመጀመሪያው የአፍሪካ ማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ (ASMIS 2026) በአዲስ አበባ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ነገ ይካሄዳል።

በጉባኤው ለመታደም ከ30 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ 321 ሚሊዮን በላይ የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮች ያሏቸው 61 ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባን እየጎበኙ ይገኛሉ።

Addis Ababa Tourism Commission

አፍሪካዊያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ "ASMIS 2026 Summit" የፊታችን ሚያዝያ 29-30/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።አዲስ አበባ የአፍሪካን ታሪክ የሚናገሩ ...
06/05/2026

አፍሪካዊያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ "ASMIS 2026 Summit" የፊታችን ሚያዝያ 29-30/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

አዲስ አበባ የአፍሪካን ታሪክ የሚናገሩ በአፍሪክ ጉዳይ የሚመክሩ የማህበራዊ ሚዲያ ተጽእኖ ፈጣሪዎችን እየተቀበለች ትገኛለች።

Visitaddisababa Et

This weekend is all about creatives!The African Social Media Influencers Summit (ASMIS) 2026 is happening this week in A...
06/05/2026

This weekend is all about creatives!

The African Social Media Influencers Summit (ASMIS) 2026 is happening this week in Addis Ababa and Africa’s top creators have gotten the memo.

Stay tuned as you get to see your favorites in a new light with Visit Addis Ababa!

Addis Ababa Tourism Commission

06/05/2026
ታሪካዊቷ -አዲስ አበባ የአህጉራችን የዲፕሎማሲ ልብ ከመሆን ባለፈ፣ አሁን ላይ እየተገነቡ ባሉ ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችና አረንጓዴ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አማካኝነት ይበልጥ ማራኪ፣ ንፁህና...
06/05/2026

ታሪካዊቷ -አዲስ አበባ የአህጉራችን የዲፕሎማሲ ልብ ከመሆን ባለፈ፣ አሁን ላይ እየተገነቡ ባሉ ዘመናዊ መሠረተ ልማቶችና አረንጓዴ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች አማካኝነት ይበልጥ ማራኪ፣ ንፁህና ለኑሮ ተስማሚ እየሆነች ትገኛለች።
​ከተማችን ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን፣ ትልልቅ የባህልና የስፖርት ሁነቶችን እንዲሁም የተለያዩ አህጉራዊ መድረኮችን በብቃት በማስተናገድ MICE ቱሪዝም ዋነኛ ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ነው።


05/05/2026
እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል አደረሳችሁ! የአርበኞች ቀንን በደማቅ ሁኔታ ክቡር የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አፅቀስላሴ፣ የባህር ሃይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ፣ የጥ...
05/05/2026

እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል አደረሳችሁ!

የአርበኞች ቀንን በደማቅ ሁኔታ ክቡር የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አፅቀስላሴ፣ የባህር ሃይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ፣ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን እና ጀግኖች አርበኞች በተገኙበት ልዩ ሆኖ በኮሪደር ልማት በተዋበው የአራት ኪሎ ፕላዛ ላይ አክብረናል።

አባቶቻችን እና እናቶቻችን ለሕይወታቸው ሳይሳሱ ራሳቸውን አሳልፈው በመስጠት፣ ዛሬ በነጻ ሕዝቦች ፊት በኩራት የምትጠራዋን ሉዓላዊት ሀገራችን ኢትዮጵያን አቆይተውልናል።
ይህንን ዘመን ተሻጋሪ እውነት እና ምትክ የማይገኝለት የታሪክ መስዋዕትነት ትውልድ ፈጽሞ አይዘነጋውም።

የዛሬው ዘመን ትውልድ የአባቶቹን መታወሻ እና የታሪክ ቅርስ ከመዘከርና ከመጠበቅ ባሻገር ሌላ አዲስ የአርበኝነት አውድ ሊፈጥር ይገባዋል።
የትላንቱ አርበኝነት ሀገርን ከባዕድ ወራሪ ማዳን እንደነበር ሁሉ፣ የዛሬው አርበኝነት ደግሞ ሀገርን ከድህነት፣ ከኋላቀርነት እና ከተመጽዋችነት ማላቀቅ ነው።

ጀግኖች አባቶቻችን ወራሪውንም ሆነ የውስጥ ባንዳውን ታግለው አሸንፈው ሀገር እንዳቆዩልን ሁሉ፣ እኛም ዛሬ የልማት እና የሰላም ጉዟችንን ለማደናቀፍ የሚሞክሩትን የዘመኑን ባንዳዎች በአንድነት፣ በንቃት እና በሥራ ማሸነፍ ግድ ይለናል።

በድጋሚ እንኳን ለ85ኛው የጀግኖች አርበኞች የድል በዓል አደረሳችሁ!
ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኑር !

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ

በአዲስ አበባ አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር - “Miss African Essence International Pageant 2026” በወዳጅነት ፓርክ ተካሄደሚያዝያ 26/2018 ዓ.ም (ቱሪዝም ኮሚ...
04/05/2026

በአዲስ አበባ አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር - “Miss African Essence International Pageant 2026” በወዳጅነት ፓርክ ተካሄደ

ሚያዝያ 26/2018 ዓ.ም (ቱሪዝም ኮሚሽን)

የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ከማሂ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር፣ የአፍሪካውያን ሴቶችን ባህል እና ውበት የሚያስተዋውቅ ዓለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር “Miss African Essence International Pageant 2026” በወዳጅነት ፓርክ ተካሂዷል።

በመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጋና አምባሳደር ክቡር ዶ/ር ሮበርት አፍርዬ በክብር እንግድነት ተገኝተው ለተወዳዳሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል::

የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሁንዴ ከበደ ዝግጅቱን አስመልክተው የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል። የማሂ ኢቨንትስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ማህሌት ገ/ዮሐንስ በበኩላቸው የእንኳን ደህና መጡ ንግግር በማቅረብ ተሳታፊዎችን ተቀብለዋል።

በዚህ ዓለም አቀፍ መርሐ ግብር ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገሮች የመጡ ተወዳዳሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፣ ወክለው የመጡትን ባህላዊ ትርኢት አቅርበዋል።

Addis Ababa Tourism Commission
Visitaddisababa Et

Address

Flamingo
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Ababa Tourism Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share