07/09/2026
"የማንሠራራት ቀን" በአራዳ ፓርክ በደመቀ ሁኔታ ተከበረ
ጳጉሜ 2/2018ዓ.ም (ቱሪዝም ኮሚሽን)
"የማንሠራራት ቀን" በዛሬው ዕለት በርካታ ወጣቶችና የብስክሌት ስፖርት አፍቃሪዎች በተገኙበት በአራዳ ፓርክ በተለያዩ ስፖርታዊ ኩነቶች በደመቀ ሁኔታ ተከበረ።
ስፖርታዊ ኩነቱን ያስጀመሩት የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ሁንዴ ከበደ፤ በአዲስ አበባ በተከናወኑት ስር ነቀል የቱሪዝም የልማት ስራዎች ዘርፉ በከፍተኛ ደረጃ ከማንሰራራት ባሻገር የከተማዋን ኢኮኖሚ በመደገፍ መሠረታዊ እመርታ እያሳየ መሆኑን ገልጸዋል::
በተለይም በከተማዋ በተሰሩት በርካታ የስፖርት መሠረተ ልማቶች የህብረተሰቡን አኗኗር ከማሻሻል አልፈው አዲስ አበባ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል እንድትሆን ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል::