Addis MESOB - One Center Digital Government Service

Addis MESOB - One Center Digital Government Service Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis MESOB - One Center Digital Government Service, Public & Government Service, Adwa Street, Arada SC, Addis Ababa.

Addis MESOB is a public office for one-stop service center designed to serve the residents of Addis Ababa with multiple public services under one roof making government services faster, more efficient, and citizen-focused.

11/04/2026



The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

10/04/2026



The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

ህዝብን በታማኝነት ማገልገል የተቋማችን መገለጫ ነው፤  ለተቋማት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ በተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ።"Addis MESOB: መጋቢት  30/20...
08/04/2026

ህዝብን በታማኝነት ማገልገል የተቋማችን መገለጫ ነው፤ ለተቋማት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ በተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ ላይ የምክክር መድረክ ተካሄደ።"

Addis MESOB: መጋቢት 30/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ

የአዲስ መሶብ የአንድ ማእከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ሰራተኞችና አመራሮች፣ በከተማ ደረጃ ለተቋማት በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ በተዘጋጀ የንቅናቄ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄዱ። መድረኩ ተቋሙ እየሰጠ ያለው ዲጂታልና የተማከለ አገልግሎት አሰጣጥ ቀጣይነትና ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋት ያለመ ነው።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የማእከሉ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ደሳለኝ ተረፈ እንደገለጹት አዲስ መሶብ አገልግሎትን በማዘመንና ተደራሽነቱን በማስፋት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ መቻሉን ገልፀዋል።

በተጨማሪም ህዝብን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል ትልቅ ክብር መሆኑን አሳስበዋል።

የአዲስ መሶብ የአንድ ማእከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የፅህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ደመቁ ካሳሁን የውይይት መነሻ ሰነዱን ያቀረቡ ሲሆን አዲስ መሶብ አገልግሎት አድማሱን በማስፋት የተገልጋይን ፍላጎት ለማሟላት ጥራት ያለው አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንና የአገልጋይነት ስነ-ምግባር፡ ሰራተኞች ተገልጋዮችን በትህትና፣ በአክብሮት እና በታማኝነት በማስተናገድ ይበልጥ ማላቅ እንደሚገባ ገልፀዋል።

Addis MESOB
The New Horizon of Service

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

Telegram: https://t.me/addismesob ቤተሰብ ይሁኑን

የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስትራቴጂክ ካውንስል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ተወያየ!አዲስ መሶብ (Addis MESOB)...
06/04/2026

የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ስትራቴጂክ ካውንስል ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ተወያየ!

አዲስ መሶብ (Addis MESOB): መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ደሳለኝ ተረፈ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለተቋሙ እያዘጋጀው የሚገኘውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ያለበትን ደረጃ ገመገሙ።

ይህ ስትራቴጂክ ዕቅድ ተቋሙ ለማሳካት ላቀደው የ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ ስኬት ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ ተገልጿል። በተጨማሪም ተቋሙ በስትራቴጂክ ዕቅድ መመራቱ ወደፊት ላስቀመጠው ግብ እንዲደርስ የሚያግዘው ሲሆን፣ ዕቅዱም በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተመላክቷል።

Addis MESOB
The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

Telegram: https://t.me/addismesob ቤተሰብ ይሁኑን

ዘውትር ሰኞ የሚካሄደው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና የአብሮነት መርሀ-ግብር ተካሄደ  Addis MESOB: መጋቢት 28/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ     አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል ...
06/04/2026

ዘውትር ሰኞ የሚካሄደው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና የአብሮነት መርሀ-ግብር ተካሄደ

Addis MESOB: መጋቢት 28/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚያካሂደውን ወርቃማው ሰኞ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና አብሮነት መርሀ-ግብሩን የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት አካሂዷል፡፡

የግዥና ንብረት ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር/ ተወካይ / የሆኑት አቶ ናትናኤል ለገሰ ከተውኔት እስከ እውቀት በሚል ርዕስ ዙሪያ የዕውቀት ሽግግራቸውን ያካፈሉ ሲሆን ማንኛውም ማህበረሰብ ወደ እውነተኛ እድገት መሄድ ከፈለገ፣ ከተውኔት ወደ እውቀት መሸጋገር እንዲሁም ለተቋማቱ መቻቻል ማዳበር አስፈላጊ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

አያይዞም አቶ ታደለ አብርሃም መቻቻል ለተቋማት የሚጠቅማቸው መረጋጋት፣ የተለያዩ አመለካከቶች እንዲካተቱ ማድረግ፣ ህጋዊ ሥርዓት ማጠናከር፣ የህዝብ እምነት ማግኘት እና ከሙስና መከላከል ነው ብለዋል።

Addis MESOB

The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

የአዲስ መሶብ ስትራቴጂክ ካውንስል እና መላው የተቋሙ ሰራተኛ ለቀድሞው የአዲስ መሶብ ዋና ዳይሬክተር ለአቶ ዮናስ አለማየሁ የመልካም የስራ ዘመን ተመኙ!Addis MESOB: መጋቢት 27/201...
05/04/2026

የአዲስ መሶብ ስትራቴጂክ ካውንስል እና መላው የተቋሙ ሰራተኛ ለቀድሞው የአዲስ መሶብ ዋና ዳይሬክተር ለአቶ ዮናስ አለማየሁ የመልካም የስራ ዘመን ተመኙ!

Addis MESOB: መጋቢት 27/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የቀድሞው የአዲስ መሶብ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የመሶብ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው በክብር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ መሾማቸው ይታወሳል ።

ይህን ተከትሎ የአዲስ መሶብ ስትራቴጂክ ካውንስል እና መላው የተቋሙ ሰራተኛ ተቋም መልካም የስራ ዘመን ተመኝተዋል እንዲሁም ለአዲስ መሶብ ዋና ዳይሬክተር ሆነው ለተሾሙት ኢ/ር ደሳለኝ ተረፈ እንኳን ደህና መጡ መርሀ ግብር አካሂደዋል።

Addis MESOB

The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

Telegram: https://t.me/addismesob ቤተሰብ ይሁኑን

03/04/2026
03/04/2026
በሀገራዊ ለውጡ ስምንተኛ ዓመት ዋዜማ ላይ፣ በአዲስ አበባ አምስተኛውን የ"አዲስ መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል በይፋ ሥራ አስጀምረናል።አዲስ አበባ አሁን የደረሰችበት ሁለ...
01/04/2026

በሀገራዊ ለውጡ ስምንተኛ ዓመት ዋዜማ ላይ፣ በአዲስ አበባ አምስተኛውን የ"አዲስ መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል በይፋ ሥራ አስጀምረናል።

አዲስ አበባ አሁን የደረሰችበት ሁለንተናዊ ለውጥና ዕድገት፣ በለውጡ መንግሥት ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የመጋቢት 24 ውጤቶች ናቸው። ከኢትዮጵያ መዲናነት ተሻግራ የአፍሪካ ኩራት የሆነችውን አዲስ አበባን በተግባርም እንደ ስሟ ውብ ለማድረግ፣ የለውጡ መንግሥት ገቢር ያደረጋቸው የልማት ሥራዎች ታሪካዊና ዘመን ተሻጋሪ ስኬትን አስመዝግበዋል።

ከለውጡ መንግሥት ስኬቶች መካከል አንዱ የ"አዲስ መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። የመንግሥት ሥርዓታት በተለዋወጡ ቁጥር ቃል እየተገባ ለመለወጥ ጥረት ቢደረግም፣ ሳይለወጥ ቆይቶ ተገልጋዩን ሲያማርር የኖረውን፣ ስር የሰደደና በተንዛዛ ቢሮክራሲ የተተበተበውን አሰራር ከመሠረቱ የሚቀይር ነው። ጊዜ፣ ወጪና ጉልበት የሚባክንበትን እንዲሁም ጥራትና ቅልጥፍና የራቀውን አገልግሎት አሰጣጥ በተግባር በመለወጥ አዲስ ምዕራፍ መክፈት ተችሏል።

"ማገልገል ክብር ነው" በሚል መርህ በንጹህ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች፣ በንጹህ አዕምሮ እና በንጹህ እጅ ማገልገልን ይዞ መጥቷል።
ይህ ዛሬ ያስጀመርነው የአዲስ መሶብ ማዕከል፣ መርካቶን ጨምሮ ሰፊ የንግዱ ማህበረሰብ የሚንቀሳቀስበት አካባቢ በመሆኑ፣ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ረገድ ትልቅ እፎይታን የሚፈጥር ይሆናል።
እያሰፋን ያለነው የዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ ከከተማችን ነዋሪዎች ባሻገር ለዲፕሎማቶች፣ ለቱሪስቶችና ለኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ጭምር ነው።
ይህ የአንድ መስኮት ዲጂታል አገልግሎት በታለመለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ለደገፋችሁ በሙሉ፣ በራሴ እና በተገልጋዩ ሕዝብ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
https://www.facebook.com/share/p/17JR8raSHF/

በአዲስ መሶብ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ለሚጀምሩ አዳዲስ ቅርንጫፎች የተመደቡ ባለሙያዎች በአቬሽን አካዳሚ ሁለተኛ ዙር ስልጠና እየተሠጠ ይገኛል ።Addis MESOB: መጋቢት/2018ዓ.ምአዲ...
01/04/2026

በአዲስ መሶብ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ለሚጀምሩ አዳዲስ ቅርንጫፎች የተመደቡ ባለሙያዎች በአቬሽን አካዳሚ ሁለተኛ ዙር ስልጠና እየተሠጠ ይገኛል ።

Addis MESOB: መጋቢት/2018ዓ.ም
አዲስ አበባ

በአቪዬሽን የኒቨርሲቲ በቀጣይ ለሚከፈቱ የአዲስ ሞሶብ የአንድ ማዕከል ደጂታል የመንግስት አገልግሎት ቅርጫፎች የግዜ አጠቃቀም ፣የደበኞች አገልግሎት ፣ የተግባቦት እንዲሁም ከስነምግባር ጋር በተያያዘ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የሁለተኛ ዙር ስልጠናው የአዲስ መሶብ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ደሳለኝ ተረፈ ተገኝተው ስልጠና ማስጀመሪያ እና የስራ መመሪያ መልእክት አስተላልፈዋል።

ይህ ስልጠና የሚሰጠው አዲሶቹ ሰራተኞች ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ሙያዊ ብቃታቸውን እንዲያሳድጉ፣ ደንበኞችን በአግባቡ ማስተናገድ እንዲችሉ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ታሳቢ ያደረገ ነው።

Addis MESOB

The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

Telegram: https://t.me/addismesob ቤተሰብ ይሁኑን

ዘውትር ሰኞ የሚካሄደው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና የአብሮነት መርሀ-ግብር ተካሄደ  Addis MESOB: መጋቢት 21/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ     አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል ...
30/03/2026

ዘውትር ሰኞ የሚካሄደው የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና የአብሮነት መርሀ-ግብር ተካሄደ

Addis MESOB: መጋቢት 21/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት ዘወትር ሰኞ ማለዳ የሚያካሂደውን ወርቃማው ሰኞ የሰራተኞች የእውቀት ሽግግርና አብሮነት መርሀ-ግብሩን የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት አካሂዷል፡፡

በፕሮግራሙ የተገኙት የአዲስ ሞሰብ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ደሳለኝ ተረፈ እራሳቸውን በማስተዋወቅ ለአመራሮችና ለሠራተኞች ወደፊት ትልቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው የሚገልጽ መልእክት አስተላልፈዋል። ስለቀጣይ ስራዎች ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በሁሉም ስራዎች ላይ በጋራ መስራት እንሚቀጥሉ ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም የካሜራ ደህንነት ባለሙያ የሆነችው አበባየሁ ታምሬ የስሜት ልህቀት (Emotional Intelligence) ምንድን ነው በሚል ርዕስ የእውቀት ሽግግራቸውን ያካፈለች ሲሆን የስሜት ልህቅ ማለት አንድ ሰው ራሱን እና ሌሎችንም የሚረዳበት፣ ስሜቱን የመለየት፣ የመግዛት እና በግንኙነቶች ላይ ውጤታማ በሆነ መንገድ የመጠቀም ችሎታ ነው በማለት ገልጻለች።

Addis MESOB

The New Horizon of Service!

ለተጨማሪ መረጃ ወይም አስተያየት:

Contact Center: በ9838 ኦፕሬተሮቻችንን ያግኙ

Website: addis.mesobcenter.et

Address

Adwa Street, Arada SC
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 21:00
Tuesday 08:00 - 21:00
Wednesday 08:00 - 21:00
Thursday 08:00 - 21:00
Friday 08:00 - 21:00
Saturday 08:00 - 21:00
Sunday 08:00 - 21:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis MESOB - One Center Digital Government Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share