E-lmis

E-lmis This is the Official page of the Ministry of Labor and Skills of Ethiopia.

Committed to promoting skills development, expanding job creation, ensuring decent work, and strengthening industrial peace to support sustainable national prosperity.

ለማህበራዊ ፈተናዎች፣ ዘላቂ የፈጠራ መፍትሄዎች!የጠብታ አምቡላንስ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክቡር አቶ ክብረት አበበ እና መላው የጥቢታ አምቡላንስ አመራርና ሠራተኞች፤ የ2026 የሽዋብ...
21/01/2026

ለማህበራዊ ፈተናዎች፣ ዘላቂ የፈጠራ መፍትሄዎች!

የጠብታ አምቡላንስ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ክቡር አቶ ክብረት አበበ እና መላው የጥቢታ አምቡላንስ አመራርና ሠራተኞች፤ የ2026 የሽዋብ ፋውንዴሽን የማህበራዊ ሥራ ፈጠራ (Schwab Foundation Award for Social Entrepreneurship) ተሸላሚ በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ!

ይህ ዓለም አቀፍ እውቅና፤ ማህበራዊ ችግሮችን በሥራ ፈጠራ ሀሳቦች ለሚፈቱ ውጤታማ የተቋማት መሪዎች የሽዋብ ፋውንዴሽን ከዓለም የኢኮኖሚ ፎረም ጋር በመተባበር የሚሰጥ ትልቅ ዓለም አቀፍ ሽልማት ነው። ክቡር አቶ ክብረት አበበ በዚህ ዓመት ከተመረጡት 21 ዓለም አቀፍ መሪዎች መካከል አንዱ ሲሆኑ፣ በመድረኩም ብቸኛው ኢትዮጵያዊ ተሸላሚ በመሆን የአገራችንን የፈጠራ አቅም በዓለም አደባባይ አስመስክረዋል።

ይህ ስኬት፤ የኢትዮጵያ የሥራና ፈጠራ ሥነ-ምህዳር ፈተናዎችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ዕድል በመቀየር ረገድ ያለውን አቅም በተግባር ያሳየ ነው። ይህም ለዜጎች ምቹ ሁኔታ ከተፈጠረላቸው፣ አገር በቀል መፍትሄዎች አገራዊ ፍላጎትን ከመሸፈን አልፈው ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን እንደሚችሉ ተጨባጭ ማሳያ ነው።

በድጋሚ ክቡር አቶ ክብረት አበበ እና መላው የሥራ ባልደረቦቻቸውን እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ፣ ይህ ስኬት ለሌሎች ሥራ ፈጣሪዎች የብርታት ምንጭ እንደሚሆን እምነቴ የፀና ነው።

የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

አንተርፕረነርሽፕ፤ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞ ስኬትየሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የአንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።ፖሊሲው በዘር...
21/01/2026

አንተርፕረነርሽፕ፤ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞ ስኬት

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 52ኛ መደበኛ ስብሰባ፣ የአንተርፕረነርሽፕ ልማት ፖሊሲን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ፖሊሲው በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራት ለሀገራዊ የልማት ግቦች ስኬት አስቻይ ሚና እንዲጫወቱ፣ ጤናማ የሥራና የፈጠራ ባህልን ለማጎልበት እንዲሁም ፈጠራና ፍጥነትን ታሳቢ በማድረግ እሴትን መጨመር የሚያስችል ምቹ የአንተርፕረነርሽፕ ሥነ-ምህዳር ለመገንባት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ነው፡፡

ይህም የሥራና የሥራ ፈጠራ ሥነ-ምህዳሩን ከማሻሻል ባሻገር የኢትዮጵያን ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት በባለቤትነት ሊመራና በፍጥነት እየተለወጠ ካለው ዓለም ጋር እኩል የሚሄድ፤ በእውቀትና በክህሎት የበለፀገ፣ በፈጠራ የታነፀና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ሚናው የጎላ ብቁና በቂ የሰው ኃይል ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ነው፡፡

የሥራ ባለቤት እርስዎ ነዎት!

ከተለመደ  እሳቤና አሠራር በመውጣት  የላቀ ውጤትን ለማስመዝገብ የሚያስችል ሰፊ ርብርብ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በአፋር፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችና በኦሮሚያ ክልል ፣ጅማ ዞን  የዘርፉ ...
21/01/2026

ከተለመደ እሳቤና አሠራር በመውጣት የላቀ ውጤትን ለማስመዝገብ የሚያስችል ሰፊ ርብርብ

በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በአፋር፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችና በኦሮሚያ ክልል ፣ጅማ ዞን የዘርፉ ሥራዎች ላይ ድጋና ክትትል ሲያደርግ የቆየው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በኦሮሚያ ክልል፣ ጅማ ዞን፣ በአጋሮና በጅማ ከተሞች ባደረገው ምልከታ ቆይታውን አጠቃሏል፡፡

የጅማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጅማ ከተማ የሚገኘውን የተርን ኪ ወርክሾፕ ተረክቦ የተለያዩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እያመነጨ እንደሚገኝ የተስተዋለ ሲሆን ለገጠር ሞዴል መንደሮች ግንባታ የሚውል የጡብና ማምረቻ ማሽኑን በስፋት እያመረተ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል የአጋሮ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወደ ውጭ ሀገራት ለሥራ ለሚጓዙ ዜጎች ስልጠና የሚሰጥበት ማዕከል በተሻለ ሁኔታ አደራጅቶ በአምስት ዙር ከአንድ ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ስልጠና መስጠቱ ተገልጿል፡፡

በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ መሰረት የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን የኩባንያ መፈልፈያ ለማደረግ እንዲቻል በወርክሾፖቻቸው የሚገኙ ማሽኖችን ሙሉ በሙሉ በስፋት ማምረት እንደሚኖርባቸው ተጠቁሟል፡፡

በተለይም ጅማ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እያስተዳደረው የሚገኘው የተርን ኪ ወርክሾፕ በርካታ ማሽኖች ያሉት በመሆኑ ያለውን አቅም አሟጦ በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማላቅ እንዲሁም በዙሪያው የሚገኙ ክላስተር ኮሌጆችን መደገፍ እንደሚኖርበት የድጋፍና ክትትል ቡድኑ አሳስቧል፡፡

የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሀገራችንን የልማት ፍላጎት የሚመልስ ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኋይል የማፍራት ተልዕኳቸውን መወጣት የሚችሉት የሥልጠና ጥራት በአግባቡ ሲያረጋግጡ በመሆኑ የስልጠና አሰጣጣቸውን ጥራት መቆጣጠር እና አሰልጣኝና ሰልጣኞቻቸውን በየጊዜው ማስመዘን እንደሚኖርባቸውም ተጠቁሟል፡፡

"በእውቀትና በስነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና መሰረት ነው" – ከንቲባ ከድር ጅዋር ​የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሶማሌና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም  በድሬዳዋ አስተዳደር የዘርፍ ...
21/01/2026

"በእውቀትና በስነ-ምግባር የታነጸ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና መሰረት ነው" – ከንቲባ ከድር ጅዋር

​የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሶማሌና በሐረሪ ክልሎች እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳደር የዘርፍ የ6 ወር አፈጻጸም እና የሪፎርም አጀንዳዎች አተገባበር አስመለክቶ ሲያካሄደው የነበረው የመስክ ምልከታ ማጠቃለያ መርሃ ግብር በድሬዳዋ ከተማ ተካሄዷል።

​በመርሃ ግብሩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር ከድር ጅዋር፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዳንኤል ተሬሳ እንዲሁም የሶማሌ እና የሀረሪ ክልል እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

​ከንቲባ ከድር ጅዋር በማጠቃለያ መድረኩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገር ብልጽግና የሚረጋገጠው በስነ-ምግባር እና በእውቀት በበለጸጉ ወጣቶች መሆኑን ገልጸዋል። አስተዳደሩም ይህንን እውን ለማድረግ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የሥራና ክህሎት ዘርፍ ወደ አንድ መጥቶ በተደራጀ መልኩ ወደ ሥራ መግባቱ ወጣቶች በሰለጠነ መንገድ ወደ ሥራ ለማሰማራት ትልቅ አቅም ፈጥሯል ብለዋል::

በዚህይም የከተማ አስተዳደሩ ትልቁ ፈተና የነበረው የሥራ እድል ፈጠራ ሥራን በማቀላጠፍ በኩል ውጤታማ ሥራ ማከናወን እንዳስቻለ ገልፀዋል::

​የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዳንኤል ተሬሳ በበኩላቸው፣ ሚኒስቴሩ የቀረጻቸው አዳዲስ የሪፎርም አጀንዳዎች በተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን በመስክ ምልከታው መረጋገጡን ገልጸዋል።

​በመስክ ምልከታው በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ውጤታማ ኢንተርፕራይዞች ፣ የሥራ ሥምሪት የሚሳለጥባቸው የሥራ ማዕከላት፣ የግልና የመንግስት ኮሌጆች ፣ ኢንዱስትሪዎች እና የሙያ ብቃት ምዘና ማዕከላት የመሳሰሉ ተቋማት መዳሰሳቸውን ተናግረዋል::

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው እና በ36.7 ሄክታር የጥብቅ ደን እና የተፈጥሮ ኃብት ስጦታ የተዘረጋው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። ...
21/01/2026

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የገበታ ለትውልድ ሥራ የመጀመሪያው መዳረሻ የሆነው እና በ36.7 ሄክታር የጥብቅ ደን እና የተፈጥሮ ኃብት ስጦታ የተዘረጋው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በይፋ ተመርቋል። ኢኮ ሎጁ የሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍ ባለፉት ሰባት አመታት ዘላቂነትን፣ የቅርስ ኃብትን እና ለዘመናት የሚዘልቅ አለምአቀፍ ደረጃን የመጠበቅ እድል መፍጠርን በማዋሃድ ምን ያህል እንደተለወጠ ማሳያ ነው።

የገበታ ለትውልድ ሥራ አለምአቀፍ ደረጃን የጠበቁ መዳረሻዎችን በማልማት የሀገራችንን እምቅ አቅም ለማውጣት የሚደረገው የሰፊው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ስትራቴጂ አካል ነው። በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተጀመረው ይኽ ሥራ በስኬት ከተተገበሩት የገበታ ለሸገር እና ገበታ ለሀገር መርሃ ግብሮች የቀጠለ እና ሥራዎቹን ወደአዳዲስ አካባቢዎች የወሰደ ሲሆን የተፈጥሮ ውበትን፣ የባሕል ቅርስን እና ዘላቂ ልምድን በማቀናጀት የተከናወነም ነው። እነዚህ ሥራዎች የከተማ እና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎችን ወደ ሳቢ የቱሪዝም ማዕከልነት የለወጡ ናቸው።

እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት ይሁንላችሁ! ጥር 11/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
19/01/2026

እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት ይሁንላችሁ!

ጥር 11/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

🌏✈️የውጭ ሀገር የስራ የስራ እድል  🚀በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በቀረበው የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ኃይል የዜጎች መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ ...
18/01/2026

🌏✈️የውጭ ሀገር የስራ የስራ እድል
🚀በሥራና ክህሎት ሚንስቴር በቀረበው የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ኃይል የዜጎች መብት፣ ደህንነት እና ጥቅም አስጠብቆ በማሰማራት የቤት ተግባራት ትልቅ ምልክት መመዝገቡ ይታወቃል። አሁንም በዚሁ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ/UAE/ እና በአውሮፖ በተለያዩ የሞያ አካባቢዎች የሰው ኃይል ይፈለጋል።
የስራ ዘርፍ ብዛት
📍አሽከርካሪ 350
📍የብስክሌት ነጂ 350
📍ግንበኛ 540
📍የፅዳት ሰራተኛ 520
📍የህንፃ ግንባታ የቀን ሰራተኛ 1050
📍የተካኑ የህንፃ የግንባታ ባለሙያዎች 700
📍መካኒክ እና ኤሌክትሪክ ባለውያዎች 600
📍አትክልተኞች ሰራተኞች 700
📍ነዋና ገንዳ ጠባቂዎች 200
📍የመጋዘን እቃ አደራጅ ሰራተኞች 700
📍የሴት እና ወንድ የፅዳት ሰራተኛ 900
📍የወንድ አጽጂዎች 200
📍የምግብ ዝግጅት ሰራተኞች 2000
📍እቃ አድራሽ በእግር/ብስክሌተኛ 400
📍የጥበቃ ሰራተኛ 600
📍የፋብሪካ ሰራተኞች 400
📍የግንባታ ሰራተኞች 100
📍የሲቪል ፎርማን 100
📍የሲቪል ቻርጅጌዎች 200
📍የመዝጊያ አናጢዎች 100
📍የብረት ጠጋኞች 1000
📍የብረት ጠጋኞች 1000
📍የግንባታ ረዳት 500
📍የክፍያ ሻጭ 100
📍የፎርማን 100
📍አናጢዎች 100
📍የብረት ጠጋኞች 100
📍ከባድ መኪና ሹፌር 2000
📍መንገድ ጠጋኞች 1000
📍የእርሻ ሰራተኛ 1000
📍የቤት ጠጋኞች 1600
📍የመኪና ጠጋኞች 500
📍የመዝጊያ አናጢዎች 140
📍ቀለም ቀቢ 20
📍ቀላል መኪና 2000
📍ሴልስማን 100
📍ቼከር መራጭ 30
📍የዓሣ ማጥመጃ ሰራተኞች 20
📍የቡቸሪ ሰራተኞች 20
📍ደህንነት 40
📍ረዳት 40
📍የድስት ማጠቢያዎች 40
📍ሰራተኞችን መጫን እና መጫንን 40
📍የጡብ ሜሰን 100
📍የግንባታ አናጢ 200
📍የብረት ጥገና 100
📍የጡብ ረዳት 100
📍የህንፃ ማጽጃዎች 200
📍የብረት ማስተካከያ 50
📍ሊሞዚን ሹፌር 100
📍ቆፋሪ 500
📍የመስኖ ቧንቧ መገጣጠሚያ 500

🏫ስለሆነም ይሆንን እድል ስትጠቀሙ የምትፈልጉ በመጀመሪያ https://t.me/molsgovet ብላችሁ በመመዝገብ
ፖስፖርት
ፎቶግራፍ
ስልክ ቁጥር በመላክ ከላይ ባለ የአገልግሎት መስጫ ማዕከል (ወረዳ ወይም ቀበሌ) ተመድባችሁ ስልጠና የምትሰለጥኑ ይሆናል የባዮሜትሪክስ መረጃ በማስመልከት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር ELMIS OTP የምትፈልጉ ይሆናል::

በዚህ ይመዝገቡ https://t.me/molsgovet ትክክለኛ መረጃዎችን አሞልተው መላክ ይኖርባቹሃል በላይ ባለው link እናሳውቃለን።

በክልሉ የ100 ቀን ዕቅድ ውስጥ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ በንቅናቄ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው - ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞየሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ ...
18/01/2026

በክልሉ የ100 ቀን ዕቅድ ውስጥ የክህሎት ልማትና የሥራ ዕድል ፈጠራ በንቅናቄ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ቀዳሚዎቹ ናቸው - ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ

የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ከኢፌደሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ቡድኑ በክልሉ ያደረገውን የድጋፍና ክትትል ሥራን አጠናቆ ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩ በተገኙበት ግብረ-መልስ ሰጥቷል።

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ እንደገለጹት፤ በአፈጻጸም የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል እና በእትረት የተለዩ ጉዳችን ለማሻሻል በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

ከክህሎት ልማት፣ ከሥራ እድል ፈጠራ፣ ከአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት እንዲሁም ከተቋም ግንባታ አንፃር የቀረቡ ጉዳዮች አፈጻጸም በጥንካሬና እንዴ ተሞክሮ መቅረቡን ጠቁመው በቀጣይም የሚደረግ አሰፈላጊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል ።

ክልሉ የዜጎችን ኑሮን ለማሻሻል የ100 ቀን እቅድ አቅዶ በትኩረትና በንቅናቄ የሚመሩትን ተግባራት በመለየት ወደ ሰራ መግባቱን ጠቅሰው በትኩረትና በንቅናቄ እንዲመራ አቅጣጫ ከተቀመጠባቸው ተግባራት መካከል የሥራና ክህሎት ቢሮ ተግባራት ውስጥ የክህሎት ልማትና የስራ እድል ፈጠራ ስራዎች መሆናቸውን ገልጸዋል ።

በሱፐርቪዥን ቡድኑ የቀረበውን ግብአት መነሻ በማድረግ ልዩ እቅድ በማዘጋጀት መስራት ተገቢ ስለመሆኑም ርዕሰ መስተዳድሩ አመላክተዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በበኩላቸው፤ በክልሉ በነበራቸው የአጭር ጊዜ ቆይታ በክልሉ በሁሉም ዘርፍ ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንና እንደተሞክሮ መቀመር ያለባቸው አፈጻጸሞች ተለይተው መያዛቸውን ተጠቁመዋል።

የተቀናጀ ጥረት፤ ለውጤታማነት...በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ኡስማን ሱሩር እና...
18/01/2026

የተቀናጀ ጥረት፤ ለውጤታማነት...

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርናና ገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ኡስማን ሱሩር እና ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ውጤታማ ውይይት አካሂደናል።

በውይይታችን፣ የእሴት ሰንሰለትን መሠረት ባደረገ የገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ የክልሉን እምቅ አቅም አሟጦ ለመጠቀም በሚያስችሉ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች ላይ በጥልቀት መክረናል። በመስኩ በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ዜጎችን በላቀ ሁኔታ ተጠቃሚ ለማድረግ፤ በየደረጃው ካሉ ባለድርሻ፣ አጋር እና አስፈፃሚ አካላት ጋር በተቀናጀ አግባብ መረባረብና ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚገባም ተግባብተናል፡፡

እሴት ሰንሰለትን መሠረት ያደረገ የገጠር የሥራ ዕድል ፈጠራ፤ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ እንደ ሀገር የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ከማገዝ አኳያ ፋይዳው ሰፊ ነው። በመሆኑም በመስኩ በሁሉም ክልሎች የተጀመሩ ሥራዎችን አጠናክረን የምናስቀጥል ይሆናል።

ክቡር አቶ ኡስማን ሱሩር፤ በቅንጅት በመሥራት የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ላሳዩት ዝግጁነትና ላደረጉልን ደማቅ አቀባበል ምስጋናዬ የላቀ ነው።

የሥራው ባለቤት እርስዎ ነዎት!

የገጠር ኮሪደር የአርሶ አደሮችን እና አርብቶ አደሮችን ሕይወት በመለወጥ ረገድ ትልቅ ሚና የሚጫወት ሀገራዊ ሥራ ነው። ዛሬ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ በጠቅላይ ሚኒስትር ...
18/01/2026

የገጠር ኮሪደር የአርሶ አደሮችን እና አርብቶ አደሮችን ሕይወት በመለወጥ ረገድ ትልቅ ሚና የሚጫወት ሀገራዊ ሥራ ነው። ዛሬ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጉራፈርዳ ወረዳ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እና ተጠሪ ተቋማት የተሰሩትን የሞዴል ገጠር ኮሪደር ስፍራ ጎብኝተናል። ሞዴል ሥራው እያንዳንዳቸው ሳሎን፣ መኝታ ቤቶች፣ የእንስሳት ክፍል እና የውጭ መጸዳጃ ክፍሎች ያላቸው አስር ዘመናዊ ቤቶችን ያካተተ ነው። ቤቶቹ ከኤሌክትሪክ መስመር ጋር የተገናኙና የሳተላይት ዲሽ የተገጠመላቸው ናቸው። በተጨማሪም ጊቢው የዶሮ ማርቢያዎች፣ የእንስሳት በረት፣ የንብ ቀፎዎች ብሎም በፍራፍሬ እና አትክልት የተሞሉ ጓሮዎች አሉት። የፀሐይ ኃይልን፣ ባዮጋዝ እና ሌሎች የልማት ሥራዎችን በመጠቀም ተቀናጅቶ የተተገበረው የገጠር ኮሪደር ልማት ሥራ ለማኅበረሰቡ ዘመናዊ፣ ጤናማ፣ ጽዱ እና ለተሻሻለ የአኗኗር ዘይቤ ጠንካራ እድል የሚሰጥ ነው። ይኽ የለውጥ ሥራ በሁሉም ዘርፍ ረገድ እንዲስፋፋ ሁሉም የየድርሻውን ሊወጣ ይገባል።

በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በሱርማ ወረዳ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባ ትምህርት ቤት ርክክብ ሥነሥርዓት ላይ ስንገኝ በአካባቢው የትምህርት መስክ እድገት ረገድ ዐቢይ ተግባር ...
18/01/2026

በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት በሱርማ ወረዳ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባ ትምህርት ቤት ርክክብ ሥነሥርዓት ላይ ስንገኝ በአካባቢው የትምህርት መስክ እድገት ረገድ ዐቢይ ተግባር በመሆኑ ደስታ ይሰማናል።

ትምህርት ቤቱ በቀዳሚነት ከአካባቢው ለሚመጡ ተማሪዎች የአዳሪ ትምህርት ቤት በመሆን ያገለግላል። ግቢው ማደሪያ ክፍሎችን፣ መማሪያ ክፍሎችን፣ በፀሃይ ኃይል የሚሰሩ በቂ ኮምፒውተሮች ያሉት የኮምፒውተር ላብራቶሪ፣ የንፁህ ውሃ ጉድጓድ፣ የተሟላ የምግብ ማብሰያ ክፍል፣ ቤተ መፃሕፍት እና የአስተዳደር ሕንፃን አካትቶ የተገነባ ነው። ይኽ ምሉዕነት ያለው የትምህርት ከባቢ የተማሪዎችን አካዳሚያዊ ልህቀት እና ደኅንነት ለማረጋገጥ ታስቦበት የተሰራ፣ ለወጣት ተማሪ ልጆቻችን ሁሉን አቀፍ እድገት አዲስ እድል የፈጠረ ተቋም ነው።

ምርትና ምርታማነትን በማላቅ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ጉዞየሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በጅማ ዞን በክላስተር ማዕከላት  በከብትና ዶሮ እርባታ የተደራጁ ኢንተርፕራይ...
17/01/2026

ምርትና ምርታማነትን በማላቅ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ጉዞ

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በጅማ ዞን በክላስተር ማዕከላት በከብትና ዶሮ እርባታ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን ጎብኝቷል፡፡

በሌማት ቱሩፋት ኢኒሺየቲቭ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በመንግስት የተያዘው አቅጣጫ በዘርፉ የተሰማሩ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢንተርፕራይዞችን ለማፍራት እንዳስቻለ ተገልጿል፡፡

በዶሮና በከብት እርባታ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ምርታማነት ለማረጋገጥ የሚያስችል አጫጭር ስልጠና እንዲሁም የግብርና ባለሙያዎችን ቋሚ ክትትልና ድጋፍ ማመቻቸት እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

የመኖ ማዘጋጃና ማቀናበሪያ ማሽኖች በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ተመርተው ለመኖ አምራች ኢንተርፕራይዞች እንዲተላለፉ በማድረግ ከመኖ አቅርቦት አንፃር የሚታዩ እጥረቶችን መፍታት መ፣ በሂደቱም ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እ እንደሚቻል ተመላክቷል፡፡

ከኢመደበኛ ወደ መደበኛ ዘርፎች ማሸጋገርን በተመለከተም በሰቃ ከተማ በየቤታቸው እንጀራ በመጋገርና በመሸጥ ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ 60 ሴቶችን በማደራጀትና ንፁህና ምቹ የሥራ ቦታ በማመቻቸት ትርፋማነታቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

የክትትልና ድጋፍ ቡድኑ በአሰንዳቦና ሰቃ ከተሞች የሚገኙ የሥራ ማዕከላትን የጎበኘ ሲሆን ሥራ የሚፈጠርላቸው ዜጎች የክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ በልዩ ትኩረት መሥራት፣ የሥራ ማዕከላቱ ለወጣቶች ሳቢና ማራኪ ማድረግ፣ የመንግስታዊ ድጋፎችን ተደረራሽነትና ውጤታማነት ማረጋገጥና ኢንተርፕራይዞች በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (LMIS) ላይ እንደሚዘገቡ ክትትል ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው በአፅንኦት ተናግረዋል

Address

Ethiopian
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when E-lmis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share