FDRE TVT Institute Prosperity Party የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብልጽግና ፓርቲ

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • FDRE TVT Institute Prosperity Party የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብልጽግና ፓርቲ

FDRE TVT Institute Prosperity Party የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብልጽግና ፓርቲ this is official facebook of FDRE TVT Institute prosperity party community

24/08/2026

እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ

የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡

ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡

ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡

ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡

የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡

በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን።

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም

22/08/2026
22/08/2026
22/08/2026
22/08/2026

"...በቀውስ መሐል ፈውስ፣ በመፈራረስ ውስጥ መታደስ፣ ተበታትኖ በመጥፋት መካከል ተሰባስቦና ተጣምሮ በአዲስ ጉልበት መነሣት የመደመር መንገድ ነው።"

(የመደመር_መንግሥት_ገጽ_113)

05/08/2026
04/08/2026

እንኳን ደስ አለን! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ቃሏን አክባሪዋ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 805.3 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ደማቅ ክብረ ወሰን አስመዘገበች።

ኢትዮጵያ ዛሬ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ 805.3 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ታላቁን ሀገራዊ ዕቅድ በላቀ ስኬትና በታላቅ ድምቀት ማሳካቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ አደረጉ።

ይህ ታሪካዊ ድል የዛሬው ዕለት ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለተከታታይ ስምንት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ያቀደችውን ግብ ያለምንም መጓደል በተግባር እያሳካች መሆኗን በድጋሚ ያረጋገጠ ነው።

03/08/2026
03/08/2026

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FDRE TVT Institute Prosperity Party የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብልጽግና ፓርቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category