04/09/2026
የኢትዮ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሃሳብ የችግኝ ተከላ አካሄደ
የኢትዮ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ “ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሃሳብ በ8ኛው ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በአዳማ የክፍያ መንገድ ዳር የችግኝ ተከላ አካሂዷል።
በመርሃ ግብሩ ከ120 በላይ የወረዳው ወጣቶች በንቃት ተሳትፈዋል። በዕለቱ የታየው የወጣቶች ተሳትፎና መነሳሳት መርሃ ግብሩ በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን ያመላከተ ነበር።
ለመርሃ ግብሩ በድምቀት መሳካት የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ላደረገው አስተዋጽኦ የኢትዮ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የወጣቶች ክንፍ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
የችግኝ ተከላው በአካባቢ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ልማት እና በቀጣይ ትውልድ ላይ የሚኖረውን የጋራ ኃላፊነት ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፣ ወጣቶች በአካባቢ ጥበቃ ተግባራት ላይ ያላቸውን ተሳትፎም የሚያጠናክር ነው።