የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት-Werabe City Agricultural Development

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት-Werabe City Agricultural Development

የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት-Werabe City Agricultural Development ​"የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት።
ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ፣ አምራችነትን በማሳደግ እና አርሶ አደሩን በመደገፍ የከተማዋን እና የአካባቢዋን የግብርና ልማት ለማፋጠን እንሰራለን!"

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽን ቡድን በከተማዉ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አደረገ!የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ...
29/08/2026

የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽን ቡድን በከተማዉ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አደረገ!

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የኢንስፔክሽን ቡድን በወራቤ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ቀበሌዎች ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ላይ የመስክ ምልከታ አድርጓል።

ምልከታው በዋናነት ትኩረት ያደረገው ዜጎችን ከተረጅነት ወደ ምርታማነት ለማሸጋገርና የሰብዓዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ላይ ነው።

በምልከታው ወቅት ቡድኑ በከተማው ከተረጂነት ወደ አምራችነት የተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ማሳን እና በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎችን ተዘዋውሮ ምልከታ በማድረግ በሂደቱም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ምክክር አድርገዋል።

እነዚህ የልማት ስራዎች የነዋሪዎችን ኑሮ ከመደገፍ ባለፈ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ረገድ እያሳዩት ባለው ለውጥ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

የቡድኑ አባላት በሰጡት አስተያየት፡ በከተማዋ የተረጅነት አስተሳሰብን በመስበር ዜጎች በራሳቸው አቅም እንዲያመርቱ እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች መሆኑን ተናግረዋል።

የሰብዓዊ እርዳታ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና በምግብ ራሳችንን ለመቻል የሚደረገው ጉዞ በተግባር እየታየ መሆኑም ተመላክቷል።

ረጂ ተቋማት እየቀነሱ መምጣታቸዉ የተገለጸ ሲሆን መስራት የማይችሉና የሚደገፉ አካላትን በመለየት ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ በማድረግ እኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ ይገባል ተብሏል።

የተረጅነት ስነ-ልቦናን በማስወገድ ህዝቡን የልማቱ ባለቤትና አምራች ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸዉም ተጠቁሟል።

የኢንስፔክሽን ቡድኑ በከተማ አስተዳደሩ ከተረጂነት ወደ አምራችነት ለመሸጋገር እየተደረጉ ባሉ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ድጋፍና ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ መዘገባችን የሚታወስ ነው።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ነሃሴ 22፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]

23/08/2026
በወራቤ ከተማ የ2018/19 የምርት ዘመን በማዳበርያ አቅርቦት፣ስርጭት እና አስተዳደር ዙሪያ ባጋጠሙ ፈተናዎች እና በተወሰዱ የመፍትሄ ዕርምጃዎች እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የውይይት መ...
18/08/2026

በወራቤ ከተማ የ2018/19 የምርት ዘመን በማዳበርያ አቅርቦት፣ስርጭት እና አስተዳደር ዙሪያ ባጋጠሙ ፈተናዎች እና በተወሰዱ የመፍትሄ ዕርምጃዎች እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የውይይት መድረክ ተካሄደ!

በወራቤ ከተማ አስተዳደር የ2018/19 የምርት ዘመን በማዳበርያ አቅርቦት፣ስርጭት እና አስተዳደር ዙሪያ ባጋጠሙ ፈተናዎች እና በተወሰዱ የመፍትሄ ዕርምጃዎች እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የውይይት መድረክ ከከተማው አመራር አካላት ጋር የዉይይት መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩም የ2018/19 የምርት ዘመን በማዳበርያ አቅርቦት፣ስርጭት እና አስተዳደር ዙሪያ ባጋጠሙ ፈተናዎች እና በተወሰዱ የመፍትሄ ዕርምጃዎች እንዲሁም የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ የተዘጋጀ ሰነድ በከተማ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ሃላፊ በሆኑት በአቶ ነስሬ አማን ቀርቦ ሰፊ ዉይይት ተደርጎበታል።

የዉይይት መድረኩን የመሩት የወራቤ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ያሲን ከሊል የአርሶአደሩን ማህበራዊና እኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደ መንግስት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ በመግለጽ በስርጭት ሂደት ላይ የሚስተዋሉ ጉድለቶችን በማረም የግብርና ተግባራትን ዉጤታማ ማድረግ እንደሚገባ አመላክተዋል።

እንደ ሀገር የዝናብና የአፈር ማዳበሪያ እጥረት በግብርናዉ መስክ ፈተና እየሆነ መምጣቱን ያነሱት አቶ ያሲን ከሊል በዘርፉ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ ሁሉንም አይነት የመፍትሄ መንገዶችን በመጠቀም ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል ብለዋል።

ያለዉን አማራጭ ሁሉ በመጠቀም የአርሶአደሩን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ያሉት ከንቲባዉ በዚህ ሂደትም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል የወራቤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ናስር ቡሽራ በበኩላቸው በመጋዘንና በስርጭት ማዕከላት ላይ ያለ ማዳበሪያን በአግባቡ በማሰራጨትና አርሶ አደሩ እንዲጠቀም በማድረግ በቀጣይ የተሻለ ምርት እንዲገኝ በማድረግ ሊከሰቱ የምችሉ ችግሮችን አስቀድሞ መከላከል ይገባል ብለዋል።

አርሶአደሩን በቴክኖሎጂና በሌሎችም ግብዓቶች በመደገፍ ምርትና ምርታማነቱን እንዲጨምር በማድረግ እኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱን ማረጋገጥ ይገባል ነዉ ያሉት አቶ ናስር ቡሽራ።

በቀጣይ በጉዳዩ ላይ በየደረጃው ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር መሰል ዉይይቶች የሚደረጉ መሆኑም ተመላክቷል።

~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ነሃሴ 12፣ 2018 [ወራቤ ከተማ ኮሙኒኬሽን]

11/08/2026
11/08/2026
11/08/2026
11/08/2026

Address

Central
Addis Ababa
NO

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:30
Tuesday 08:00 - 17:30
Wednesday 08:00 - 17:30
Thursday 08:00 - 17:30
Friday 08:00 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የወራቤ ከተማ አስተዳደር ግብርና ልማት ጽሕፈት ቤት-Werabe City Agricultural Development posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share