Libo Kemkem Woreda Court/ሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት

Libo Kemkem Woreda Court/ሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት "Our vision is excelling to become a model judiciary in Ethiopia!"
"ራዕያችን በአገር አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት የሆነ ፍርድ ቤት መገንባት ነው!

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት ሰኔ 11/2018 ዓ/ም በአዲስ ዘመን ከተማ ቀበሌ 01 የህዝብ    የምክክር መድረክ ተካሄደየሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤትፕሬዚዳንትና የህዝብ ግንኙነት እና የ...
19/06/2026

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት ሰኔ 11/2018 ዓ/ም
በአዲስ ዘመን ከተማ ቀበሌ 01 የህዝብ የምክክር መድረክ ተካሄደ
የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤትፕሬዚዳንትና የህዝብ ግንኙነት እና የኮምንኬሽን ባለሙያ በተገኙበት የህዝብ የምክክር መድረክ በስፋት ተካሂዷል፡፡በመጀመሪያም የፍርድ ቤቱን የ11ወራት የስራ እንቅስቃሴ እንዲሁም የፍርድ ቤቱን ተደራሽነት በምክክር መድረኩ በስፋት ዉይይት የተደረገበት አጀንዳ ነዉ፡፡
እንዲሁም የባህል ፍርድ ቤቶችንም አስፈላጊነትና አላማ በድጋሜ በህዝብ የምክክር መድረኩ ዉይይት ተደርጓል፡፡የተመረጡ የባህል ፍርድ ቤቶችም የማህበረሰቡን ወግና ባህል መሰረት አድርገዉ በዳበረ የሽምግልና ስርዓት ሰላምን ማስፈን አስፈላጊ መሆኑን እንዲሁም ባህላዊ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታት እንደሚቻል ግንዛቤ ተፈጥሯል፡፡
ቀጣይ ወደ ስራ ለሚገቡ የባህል ፍርድ ቤት ሽማግሌዎች አጋር አካላት በማቶሪያል፤በቢሮ ማስቻያ፤እንዲሁም የአቅም ግንባታ ስልጠናም በመስጠት ከጎናችን መሆን እንደሚጠበቅባቸዉ ፕሬዚዳንቷ መልክት አስተላልፈዋል፡፡

ሰኔ 11/2018 ዓ/ም
አ/ዘመን

18/06/2026

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት የ2018 ዓም በጀት አመት የ11 ወራት የስራ አፈጻፀም ግምገማ
ግንቦት 28/2018 ዓ.ም
/አዲስ ዘመን/
የሊ/ከ/ወ/ፍ/ቤት ማኔጅመንት የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የ11 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በዝርዝር ገምግሟል በግምገማው ላይም የእቅድ ዝግጅትና በጀት ክትትል ባለሙያ የሆኑት አቶ ባንታየሁ ላቂያው በእቅድ ከተቀመጡ 11 ግቦች አንጻር በዝርዝር አቅረበዋል፡፡
የዳኝነት ነጻነትና ገለልተኝነትን ማረጋገጥ ፤ስነ-ምግባርን ማሻሻልና ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ፤የዳኝነት አገልግሎት ውጤታማነትን ማሳደግ ፤የቴክኖሎጅን አቅርቦትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ፤የሰው ሃብት ልማትና ተቋማዊ አቅም ግንባታ ማሳድ ፤ቅንጅታዊ አሰራርና ማሳደግ ፤የህግ ግንዛቤና የህብረተሰብ ተሳፎ ማረጋገጥ ፤ብዝሃ/ህግ ፍትህ መስቻ ስራቶችን ማጠናከር ፤ ሰባዊ መብቶችን ማሳወቅ /ማክበር /ማስከበርና እንዲሟሉ ማድረግ የፍ/ቤቱን አካላዊ ተደራሽነትን ስራ መስራት፤ የሴቶች /ህጻናት /አረጋዊና /አካል ጉዳተኛ ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ በሚሉ ግቦች በዚህ 11 ወራት ውስጥ በተከናወኑ የዳኝነት ስራዎች ውስጥ የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የ11 ወራት የስራ አፈጻጸም ያከናወናቸው ነጥቦች ማለትም በበጀት ዓመቱ የነበሩ ጠንካራ ጎኖች ፤ያጋጠሙ ችግሮች የተወሰዱ መፍትሄዎችንም ጭምር ገምገሟ ተደርጓል በመጨረሻም ለቀጣ በጀት አመት የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ ግምገማው ተጠናቋል ፡፡
ግንቦት 28/2018 ዓ.ም
/አዲስ ዘመን /

09/06/2026

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍ/ቤት የባህል ፍርድ ቤት ለማቋቋም ከአስፈፃሚዎች ጋር ዉይይት አደረጉ
በአማራ ክልል ባህላዊ ፍርድ ቤቶች እንዲቋቋሙ በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ዓ/ም መሰረት የባህል ፍርድቤቶችን ወደ ስራ ለማስገባት የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አበዛሽ አድማሱ እንዲሁም የባህልና ቱሪዝም ሃላፊ አቶ ዮሀንስ ጊዜዉ እና የአዲስ ዘመን ከተማ አራቱ የቀበሌ አስተዳደሮች በመሰብሰብ ስለባህላዊ ፍርድ ቤቶች ለተቋቋሙበት አላማ እና አስፈላጊነትን በተመለከተ ከአስፈጻሚዎች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት አደረጉ፡፡

05/06/2026

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍ/ቤት 8ኛ ዙር የዳኞች ዉይይትየአብክመ አዋጅ ቁጥር 310/2018 አንቀጽ /1/የመንግስት ወይም የወል ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ የያዘ ሰው ይርጋን እንደ መከራከሪያ ሊያነሳ አይችልም በሚል ይደነግጋል ፡፡ በቅፅ 13/ሰ/መ/ቁ/69291ቅጽ 14/79394ላይ ህግ-ወጥ ውል በይርጋ እንደማይታገድ ትርጉም ተሰጥቷል ፡፡በአዲሱ የመረገት አዋጅ መሰረት ህገ-ወጥ ውልን መሰረት አድርጎ የገጠር መሬት የያዘ የሚይዝ ሰው ይርጋን እንደ መከራከሪያ አድርጎ ማንሳት ይችላል ወይ?ይርጋ ይቆጠራል አይቆጠርም ?ካላይ የተጠቀሰው የአዋጅ አንቀጽ ከህገ ምንግስቱ አንጻር 40/3/ ጋር እንዴት ይታያል ?
2. የመሬት ውል ፎርም ፈቃጅ አዛዥ እና አስገዳጅ ናቸው ?ከዚህ ጋር ተያይዞ ስለ ክራይ ፤ስጦታ ፤ለውጥ በተመለከተ የፌራሉ መሬት አዋጅ 324/2016 አዛዥ አድርጎ ሲያስቀምጥ የክልሉ 310/2018ደግሞ አስገዳጅ ፎርም አድርጎ አስቀምጧል ተከራካሪዎች የውል ፎርምን እንደመከራከሪያ ቀርቡ ተግባራዊ ማድረግ ያለብን ህግ የክልሉን ነው ወይስ የፌደራሉን ?የክልሉ መሬት ህግ ከፌደራሉ የተለየ ፎርም ማስቀመጡ የማስተዳደር ስልጣንስ ተጠቅመን ነው የሚባል ወይስ የመሬት ህግ አወወጣ ሊባል ይችላል ? የትኛውን ህግ ተፈጻሚ እናድርግ ?
3.ከከተማ መሬት ጋር ተያይዞ የከተማ አስተዳርር እና መሰረተልማት ተቋማት የግንባታ ፍቃድ ሲጠየቁ እና ወይም ቤት በአፈጻጸም ሲያዝ ግምቱ ግምቱ ሲባሉ በከተማው ማስተር ፕላን /የዕድገት ፕላን መሰረት ቦታውን መንገድ ያገኘዋል ወይም ወደ ፊት ቦታው ላይ የሚሰራው በልማት ስራ አለ እና የግንባታ ፍቃድ አንሰጥም ?አይገመትም ይላሉ ?ሌላ ይዞታው የግንባታ ፍቃድ እንደሰጠው ወይም የሁከት ክስ ቢያቀርብ እንዴት እናስተናግዳው ተቋማቱ ከላይ የተጠቀሰውን ምክንያት በመስጠት የግናባታ ፍቃድ አንሰጥም አንገምትም ባለቤቱ መሸጥ አይችልም ማለት ይችላሉ ወይ?ከህገ መንግስቱ አንቀጽ 40ጋር እንዴት ይታያል ?
4.በአንቀጽ ቁጥር 310/2018 አንቀፅ 16/3/የመሬት ስጦታ አካለመጠን ያልደረሱትን እና የቤተሰብ አባላትን ሙሉ በሙሉ የሚጎዳ /ድርሻውን /የሚያስቀር ከሆነ ተቀባይነት የለውም ይላል?ይህ ማለት አካለ መጠን የደረሱትን ልጆች ያለምክንያት መቀነስ ይችላል ማለት ነው ?ከዚህ ቀደም ከህግ ጋር ተያይዞ የተሰጡ ሰበር ትርጉሞች ለአዲሱ ህግ ሊሰራ ይችላሉ?
5.ደብተር ይሰረዝልኝ /ካርታ ይሰረዝልኝ በሚል የሚቀርቡ ክሶች ከአስተዳደር ስነ-ስራትአዋጅ 292/2017 አንጻር ጉዳዩን የማየት ስልጣን የማን ነው ?
6.የገጠር መሬት ውርስ ክርክር ተፈጻሚነት ያለው ህግ ሟች የሞተበት ጊዜ የነበረው ህግ ነው ፡፡የውርስ ማስረጃ ይሰጠኝ በአንድ ወገን የማቅረብ አቤቱታ ቢሆንም ሟች አዲሱ ህግ 310/2018 ከመውጣቱ በፊት የሟች ቢሆን ማስረጃ የሚሰጠው በሞተበት ጊዜ ባለው ህግ ወይስ በአሁኑ ነው? የገጠር መሬት ወራሽነት ማስረጃ ከፍ//ቤታችን አንዴት እየተሰጠ ነው ?

05/06/2026

የ/ሊ/ከ/ወ/ ፍ/ቤት ሰባተኛ ዙር የዳኞች የህግ ውይይት
ቅድመ ሙግት (pre trial}
ቅድመ ሙግት በፍትሐብሔር ክርክር ሂደት ጭብጥ ተይዞ ማስረጃ ማሰማት ከመጀመሩ በፊት ያለውን ሂደት የያዘ ሲሆን በዋነኛነት ክስና ማስረጃ ማቅረብን፤ መጥሪያ ማድረስን፤ መልስና ማስረጃ ማቅረብን፤የቃል ክርክርን እና የክስ መቃወሚያ ላይ መወሰንን የካትታል፡፡
የመወያያ ሀሳብ አንድ፡- በፍትሐብሔር ክርክር የክስ መጣመር እና መነጠል(joinder and mis joinder}
ማለትም በአንድ ክስ ውስጥ ብዙ ከሳሾች፤ብዙ ተከሳሾች፤አንድ አይነት የክስ ምክንያቶች፤የተለያዩ የክስ ምክንያቶች እና የሶስተኛ ወገኖች በክሱ መካፈል(መጣመር)የያዘ ሲሆን አላማውም ክርክርን አጭር፤ግልጽ፤ጊዜና ወጭ ቆጣቢ በሆነ መንገድ መምራት፤ ተቃራኒ ውሳኔዎችን መከላከል፤ እና ፍትሀዊ መፍትሔ መስጠትነው፡፡ይህም በፍ/ብ/ስ/ስሕ/ቁ /35-43 የተቀመጠ ነው፡፡በዚህም አግባብ መጣመር የሌለባቸው ተከራካሪዎች ተጣምረው ክስ ሲያቀርቡ ወይም መጣመር የሌለባቸው የክስ ምክንያቶች ተጣምረው ሲቀርቡ ልክ እንደማያስከስስ ምክንያት ወይም የስረ ነገር ስልጣን ሳይኖር እንደቀረበ ክስ መጥሪያ መላክ ሳያስፈልግ ተነጣጥለው ያቅርቡ ወይም ተነጣጥሎ ይቅረብ ተብሎ ፋይል ይዘጋል፡፡ ነገር ግን የግድ ተጣምረው መክስስ ያለባቸው ሲሆን ወይም ክሱ ተጠቃሎ መቅረብ ያለበት ሲሆን ለምሳሌ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ216 እና ሌሎች ባስቀመጡት አግባባ የውርስ ወይም የባል እና ሚስት ጉዳይ ሲሆን እና ከዚህ ክርክር ላይ ጣልቃ የሚገቡ ወይም በክርክሩ የሚጣመሩ ተከራካሪዎች የክሰ ምክንያታቸው የተለያ ሆኖ አቤቱታው በአንድ ላይ ቢቀርብ አቤቱታቸሁን ነጣጥላችሁ አቅርቡ ማለት ይቻላል ወይ? ክስን ነጣጥሎ ማቅረብ ከሚያሳካው አላማ አንፃር እንዴት ይታያል? የአቤቱታው መጣመር ሆነ መነጣጠል ክርክርን ከማሳለጥ አንጻር በውጤት ደረጃ የተለየ ሊሆን ይቸላል ወይ?
የመወያያ ሀሳብ ሁለት፡-በፍትሀብሔር ክርክር የሰነድ(የጽሁፍ) ማስረጃዎች
ሙሉ ክርክሩን መስማት ናምስክሮችን መመርመር ከመጀመሩ በፊት እነዚህ ማስረጃዎች ተጠቃለው መቅረብ እና የመዝገቡ አካል መሆን አለባቸው(የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/234)፡፡እንዲሁም ዳኛ በራሱ ተነሳሽነት ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት ከፍርድ በፊት በማንኛውም ጊዜ አንዲቀርብ ትዛዝ ለመስጠት ይችላል(የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/164)፡፡ነገር ግን በተከራካሪ ወገኖች ጠያቂነት የሚቀርቡ የሰነድ(የፅሁፍ) ማስረጃዎች መቸና በምን ሁኔታ ሊቀርቡ ይችላሉ? የፍርድ ቤታችን አሰራርስ በምን አግባብ እና ሁኔታ እያስተናገድናቸው ነው? የአሰራር ክፍተት ካለ በምን አግባብና በህግ አግባብ እንዴት ይስተካከል?
ለምሳሌ 1ኛ .በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/137 መዝገቡ ለቃል ክርክር ከተቀጠረበት ቀን ቀድሞ ወይም በተቀጠረበት ቀን ቀርበው ከመዝገቡ ጋር ይያያዛሉ፤ክርክርም ይደረግባቸዋል፤ በሚል የተቀመጠው ምን አይነት ማስረጃዎች እንዲያያዙ ለመፍቀድ የተቀመጠ ነው? በምንስ አግባብ ከመዝገቡጋር ሲያያዙ ነው የቃል ክርክር የሚደረግባቸው?
2ኛ .በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ145 መሰረት በፍርድ ቤት ትዛዝ የሚቀርቡ ማስረጃዎችን ፍ/ቤቱ እንዲቀርቡ የሚያዘውበምን ሁኔታ የሚገኙ ማስረጃወችን ነው? እንዲቀርቡ መታዘዝ ያለበት መቸ ነው?
3ኛ .በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/256 መሰረት ከባድ እና በቂ በሆነ ምክንያት ከክሱ ወይም ከመልሱ ጋር ያልተያያዙ ወይም በቃል ክርክር ወቅት ያልቀረቡ ቢሆንም ማስረጃው እንዲያያዝ ሊፈቀድ እንደሚችል የተቀመጠው ምን አይነት

02/04/2026

ዜና ችሎተ
ከባድ ስርቆት እና መሸሸግ ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች በ3 ዓመት ከ 9 ወር እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል
ከሳሸ አቃቢ ህግ
ተከሳሽ 1 ቻሌ ሞላ አሰሜ
2. ሲሳይ አለምነው እምሬ አድራሻቸዉ በለሳ ወረዳ ዋርካ ቀበሌ የሆኑት ግለሰቦች በ1996 ዓ/ም ተደንግጎ የወጣዉን የኢፌደድሪ የወንጀል ህግ ድንጋጌ አንቀፀ 32/1/ /ሀ/እና 669 /3/ /ለ/ ን በመተላለፍ ተገቢ ያልሆነ ሃብት ለማግኘት በማሰብ አንድ ካልተታዘ ግለሰብ ጋር በመሆን በቀን 18 /06 /2018 ዓ ም ከሌሊቱ 7 00 ስዓት ሲሆን በአዲስ ዘመን ከተማ ቀበሌ 03 ልዪ ቦታዉ ፍተሻ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራዉ ቦታ የግል ተበዳይ የአቶ ጌታቸዉ በእዉቀትን የኮንቲነር ሱቅ ሰብረዉ በመግባት የተለያዪ የሱቅ እቃዎችን የወሰዱ በመሆኑ በፈፀሙት ስርቆት ወንጀል ተከሰዋል ተከሳሾችም በተባለዉ ቀንና ስዓት ድርጊቱን አልፈፀምነም ብለዉ ክደዉ ተከራክረዋል ፍ/ቤቱም አቃቢ ህግ ምስክሮችን እንዲያቀርብ ብይን ተሰጥቶ የአቃቢ ህግ ምስክሮችም እንደክሱ አስረድተዋል፡፡ ተከሳሾችም የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ ቢጠየቁም ክሱን ማስተባበል አልቻሉም ፡፡ ፍርድ ቤቱም በ10 /7/2018ዓ.ም ይዞት በዋለው ችሎት ጥፋተኞችን ያርማል ያስተምራል መሰል የማሀበረሰብ ክፍሎችንም ያስጠነቅቃል በሚል በ3 ዓመት ከ 9 ወር እንዲቀጡ ፍረድ ቤቱ ወስኗል

31/03/2026

የ/ሊ/ከ/ወ/ ፍ/ቤት የዳኞች የህግ ውይይት
7ኛ ዙር
ቅድመ ሙግት (pre trial}
ቅድመ ሙግት በፍትሐብሔር ክርክር ሂደት ጭብጥ ተይዞ ማስረጃ ማሰማት ከመጀመሩ በፊት ያለውን ሂደት የያዘ ሲሆን በዋነኛነት ክስና ማስረጃ ማቅረብን፤ መጥሪያ ማድረስን፤ መልስና ማስረጃ ማቅረብን፤የቃል ክርክርንና የክስ መቃወሚያ ላይ መወሰንን ያካትታል፡፡
የመወያያ ሀሳብ አንድ፡- በፍትሐብሔር ክርክር የክስ መጣመር እና መነጠል(joinder and mis joinder}
ማለትም በአንድ ክስ ውስጥ ብዙ ከሳሾች፤ብዙ ተከሳሾች፤አንድ አይነት የክስ ምክንያቶች፤የተለያዩ የክስ ምክንያቶች እና የሶስተኛ ወገኖች በክሱ መካፈል(መጣመር)የያዘ ሲሆን አላማውም ክርክርን አጭር፤ግልጽ፤ጊዜና ወጭ ቆጣቢ በሆነ መንገድ መምራት፤ ተቃራኒ ውሳኔዎችን መከላከል፤ እና ፍትሀዊ መፍትሔ መስጠት ነው፡፡ይህም በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ /35-43 የተቀመጠ ነው፡፡በዚህም አግባብ መጣመር የሌለባቸው ተከራካሪዎች ተጣምረው ክስ ሲያቀርቡ ወይም መጣመር የሌለባቸው የክስ ምክንያቶች ተጣምረው ሲቀርቡ ልክ እንደማያስከስስ ምክንያት ወይም የስረ ነገር ስልጣን ሳይኖር እንደቀረበ ክስ መጥሪያ መላክ ሳያስፈልግ ተነጣጥለው ያቅርቡ ወይም ተነጣጥሎ ይቅረብ ተብሎ ፋይል ይዘጋል፡፡ ነገር ግን የግድ ተጣምረው መክስስ ያለባቸው ሢሆን ወይም ክሱ ተጠቃሎ መቅረብ ያለበት ሲሆን ለምሳሌ የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ216 እናሌሎች ባስቀመጡት አግባባ የውርስ ወይም የባልና ሚስት ጉዳይ ሲሆን እና ከዚህ ክርክር ላይ ጣልቃ የሚገቡ ወይም በክርክሩ የሚጣመሩ ተከራካሪዎች የክሰ ምክንያታቸው የተለያየ ሆኖ አቤቱታው በአንድ ላይ ቢቀርብ አቤቱታቸሁን ነጣጥላችሁ አቅርቡ ማለት ይቻላል ወይ? ክስን ነጣጥሎ ማቅረብ ከሚያሳካው አላማ አንፃር እንዴት ይታያል? የአቤቱታው መጣመር ሆነ መነጣጠል ክርክርን ከማሳለጥ አንጻር በውጤት ደረጃ የተለየ ሊሆን ይቸላል ወይ?
የመወያያ ሀሳብ ሁለት፡-በፍትሀብሔር ክርክር የሰነድ(የጽሁፍ) ማስረጃዎች
ሙሉ ክርክሩን መስማትና ምስክሮችን መመርመር ከመጀመሩ በፊት እነዚህ ማስረጃዎች ተጠቃለው መቅረብ እና የመዝገቡ አካል መሆን አለባቸው(የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/234)፡፡እንዲሁም ዳኛ በራሱ ተነሳሽነት ትክክለኛ ፍርድ ለመስጠት ከፍርድ በፊት በማንኛውም ጊዜ አንዲቀርብ ትእዛዝ ለመስጠት ይችላል(የፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/264) ነገር ግን በተከራካሪ ወገኖች ጠያቂነት የሚቀርቡ የሰነድ(የፅሁፍ) ማስረጃዎች መቸና በምን ሁኔታ ሊቀርቡ ይችላሉ? የፍርድ ቤታችን አሰራርስ በምን አግባብ እና ሁኔታ እያስተናገድናቸው ነው? የአሰራር ክፍተት ካለ በምን አግባብና በህግ አግባብ እንዴት ይስተካከል?
ለምሳሌ1ኛ በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/137መዝገቡ ለቃል ክርክር ከተቀጠረበት ቀን ቀድሞ ወይም በተቀጠረበት ቀን ቀርበው ከመዝገቡ ጋር ይያያዛሉ፤ክርክርም ይደረግባቸዋል፤ በሚል የተቀመጠው ምን አይነት ማስረጃዎች እንዲያያዙ ለመፍቀድ የተቀመጠ ነው? በምንስ አግባብ ከመዝገቡጋር ሲያያዙ ነው የቃል ክርክር የሚደረግባቸው?
2ኛ .በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ145 መሰረት በፍርድ ቤት ትእዛዝ የሚቀርቡ ማስረጃዎችን ፍ/ቤቱ እንዲቀርቡ የሚያዘው በምን ሁኔታ የሚገኙ ማስረጃወችን ነው? እንዲቀርቡ መታዘዝ ያለበት መቸ ነው?
3ኛ .በፍ/ብ/ስ/ስ/ሕ/ቁ/256 መሰረት ከባድ እና በቂ በሆነ ምክንያት ከክሱ ወይም ከመልሱ ጋር ያልተያያዙ ወይም በቃል ክርክር ወቅት ያልቀረቡ ቢሆንም ማስረጃው እንዲያያዝ ሊፈቀድ እንደሚችል የተቀመጠው ምን አይነት ማስረጀዎችን ለማካተትና እንዲያያዙ ለመፍቀድ ነዉ?ማስረጃዉ የተገኘዉ /የተፈጠረዉ/ ክስ ከተመሰረተ ወይም ክርክር ከተደረገበት በኋላ ቢሆንስ እንዲያያዝና እንዲመረመር ይፈቅዳል ወይ?

የሊቦ ከምከም  ወረዳ  ፍ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና የኮምንኬሽን ባለሙያ ለተገልጋዪ /ለባለጉዪ/ ስለአገልግሎት አሰጣጡ ትምህርት ሲሰጥ---
12/03/2026

የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍ/ቤት የህዝብ ግንኙነትና የኮምንኬሽን ባለሙያ ለተገልጋዪ /ለባለጉዪ/ ስለአገልግሎት አሰጣጡ ትምህርት ሲሰጥ---

04/03/2026

ቀን 20/06/2018ዓ/ም
የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍ/ቤት የዳኞች
የህግ ውይይት
የመወያያ ዕርስ
1. ተገዶ የመያዝን ህጋዊነት ለማጥራት/አካልን ነጻ ማውጣት /application for habeas corpus/
አቤቱታን በተመለከተ
2. ማህበራትን / cooperatives/ጉዳይ በተመለከተ
3. አክሲዮኖች / shares በባልና ሚስት ክርክር ፍችን ተከትሎ የሚመጣው ውጤት ክፍፍል ሲጠየቅ እና በውርስ ማጣራት ጥያቄ ላይ ፍ/ቤቱ ሊከተለው የሚገባው ስነ ስርአት ምንድን ነው? እንዴትስ ነው በኛ ፍ/ቤት እየተሰራ ያለው? ተመሳሳይነት አለ ወይ ?
 ለምሳሌ አማራ ባንክ አክስዮን ብር10000/10 እጣ/በባል ስም የተመዘገበ ቢሆን እና ሚስት ለመካፈል ብትጠይቅ ሂደቱ ምን ይሆናል?
 ወራሽ የሆነ ወላጆች ልጃቸው በአማራ ባንክ 10000 /10 እጣ /ቢኖረው እና በውርስ ማጣራት ሪፖርት ተጣርቶ ቢቀርብ ፍ/ቤቱ እንዴት ነው የሚያፀድቀው?

23/02/2026

አገራዊ እራያችን
የወረዳዉ ህብረተሰብ እየገነባ ባለዉ ፍትሃዊና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እኩል ተጠቃሚ እንዲሆን መልካም አስተዳደርና ማህበራዊ ፍትህ ሰፍኖ ለክልላችን ብሎም ለሃገራችን ልማት መሳለጥ የፍርድ ስርዓቱን አጋዥ እንዲሆን ማድረግ ፣
 የሊ/ከ/ወ/ፍ/ቤት
ራዕይ፡-በወረዳዉ የህግ የበላይነት ተረጋገጦ ፍትህ ሰፍኖ ማየት
ተልዕኮ ፡-በወረዳዉ ፍትህን ለማሰፈን ዲሞክራሲያን መልካም አስተዳደርን ለመመስረት ፈጣን ወጭን ያገናዘበና ሚዛናዊ ዳኝነት መስጠት
የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍ/ቤት በሁለት ዋና የስራ ሂደት ያሉት በዉስጡ 12 ወንድ ዳኛ 3 ሴት ዳኛ የሸሪ ዳኛ 1 ሪጅስትራር 1 ድጋፍ ሰጭ ሰራተኛ ወንድ 19 ሴት 27 በድምሩ 63 ሰራተኛ አሉት ፡፡
በ2018 ዓ/ም የመጀመሪያዉ 6 ወር በፍትሃብሔርና በወንጀል ዉሳኔ ለመስጠት የተያዘ እቅድ 1458 መዝገብ ሲሆን የተከናወነዉ 1157መዝገብ ወይም የእቅዱን 79.4% ነዉ፡፡ ይህ አፈፃፀም ለስራ ከቀረበዉ ጠቅላላ 1519 መዝገብ አንጻር ሲታይ 76.2% ይሆናል ፡፡
• በተናጥል ሲታይ ፦
የወንጀል ጉዳይ ፦
በ2018 ዓ/ም የመጀመሪያ 6 ወር ዉሳኔ ለመስጠት የተያዘ እቅድ 111 መዝገብ ሲሆን የተከናወነ 105 መዝገብ ወይም የእቅዱን 95.0 % ነዉ፡፡ይህ አፈፃፀም ለመስራት /ለመታየት ከቀረበዉ ጠቅላላ 111 መዝገብ አንፃር ሲታይ 91.0% ነዉ፡፡
 የፍትሐብሄር ጉዳይ ፦በ2018 ዓ/ም የመጀመሪያዉ 6 ወር ዉሳኔ ለመስጠት የተያዘ እቅድ1347 መዝገብ ሲሆን የተከናወነዉ 1052 መዝገብ ወይም የእቅዱን 78.1 % ነዉ፡፡ ይህ አፈጻፀም ለስራ ከቀረበዉ ጠቅላላ 1347 መዝገብ አንፃር ሲታይ 75.0 ነዉ፡፡
 በእርቅ የተዘጉ መዝገቦች
በዚህም መሰረት በ2018 ዓ/ም የመጀመሪያዉ 6 ወር ዉስጥ 28 መዝገቦች ቀርበዉ ሙሉ በሙሉ በእርቅ ተዘግተዋል ፡፡
በሸሪዓ /የቃዲ ችሎትን በተመለከተ
በወረዳችን ከመደበኛ ችሎቶች ዉጭ የእስልምና ጉዳዮች ስለሚታዪ በዚሁ ችሎት 7 መዝገቦች ቀርበዉ ሁሉም በ6 ወር ዉስጥ ዉሳኔ አግኝተዋል፡፡
በዳኝነት ስራ ለመንግስት ገቢ የተደረገ ገንዘብን በተመለከተ
ፍ/በቱ የዳኝነት ስራ በሚያከናዉንበት ጊዜ ወይም አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት ከዳኝነት ክፍያ እና ከመቀጫ ገቢዎችን ይሰበስባል፡፡በዚህም መሰረት በ2018 ዓ/ም የመጀመሪያዉ 6 ወር ዉስጥ የተገኘ ገቢ ብር 973‚652.40/ዘጠኝ መቶ ሰባ ሶስት ሽ ስድስት መቶ ሃምሳ ሁለት ብር ከአርባ ሳንቲም በመሰብሰብ ለወረዳዉ ግንዘብና ኢ/ል/ጽ/ቤት ገቢ ያደረገ ነዉ፡፡
በቅሬታ አገልግሎት ላይ በተመለከተ
 የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል የእርካታ ደረጃዉ 64.0%ደርሷል
 በአስተያየት መስጫ የተሰጡ አስተያየቶችን ግብረ መልሰ መለጠፍ
 ቀጠሮ የጠፋባቸዉን ባለጉዳዮች ማስተናገድ
 በህዝብ ግንኙነትና በኮምንኬሽን ባለሙያ
 አስተማሪ የሆኑ የወንጀል ቅጣቶችን ለሌሎች ትምህርት
 እንዲሆኑ ለኮምንኬሽ ጽ/ቤት እና ለሌሎች ተቋሞችም እየተላከ ይገኛል፡፡
 ባለጉዳዮች የሚገለገሉባቸዉን ፎርሞች በመጠቀም ባለጉዳዮችን ከወጭ አድነናል
 ባለጉዳዮች በፍርድ ቤቱ ላይ አመኔታ እንዲኖራቸዉ ጥዋት ጥዋት ትምህርት ይሰጣል፡፡
 የፍትህን ተደራሽነት ለማስፋት ይፋግ ከተማ የምክከር መድረክ ተካሂዷል፡፡
 በቋሙ ድረ-ገጽ ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን እንለቃለን፡፡
 የሰዉ ሃይልንበተመለከተ
በፍርድ ቤቱ ያሉ መደቦች 52
በሰዉ ሃይል የተሸፈነ 46 መደብ በጀት ያላቸዉ መደቦች 2 በጀት የሌላቸዉ መደቦች 4
በአጠቃላይ የሚመጡ መመሪያዎች ተግባር ላይ ይዉላሉ፡፡ የሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አበዛሽ አድማሱ ከዳኞችና ከሰራተኞች ጋር ስለ ስራ ዉይይት ሲያካሂዱ በወረዳችን አንፃራዊ ሰላም በመምጣቱ በርካታ የባለጉዳይ ፍሰት ስላለ ስዓትን በማክበር በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸዉ ውይይት አደረጉ፡፡ እንዲሁም የዳኞችና የሙየያተኛ አለመመጣጠን ክፍተት እንዳይፈጠር ባለጉዳዮችን እያስተናገዱ ይገኛሉ፡፡

Address

Amhara, South Gondar, Addis Zemen
Addis Zemen

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Libo Kemkem Woreda Court/ሊቦ ከምከም ወረዳ ፍርድ ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share