27/08/2026
ንቁ ወጣቶች ለሀገር ግንባታ!
ወጣቶች የአንድ ሀገር ኃይል፣ የለውጥ አራማጆች እና የነገዋ ሀገር መሰረቶች ናቸው፣ንቁ ወጣትነት በሀገር ጉዳይ ላይ በባለቤትነት ስሜት በመሳተፍ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፎካካሪነትን በማሳደግ ለአዎንታዊ ለውጥ ዝግጁ የሆነ ትውልድን ይፈጥራል። ወጣቱ ክፍል ባለው አዲስ ጉልበት፣ ያልተገደበ አቅም እና ተነሳሽነት ተጠቅሞ በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ ከፊት መስመር ሲሰለፍ፣ የሀገራችን እድገት ፈጣን፣ ዘላቂ እና አስተማማኝ ይሆን።
ፈጠራ እና አዳዲስ ሀሳቦችን ማፍለቅ ደግሞ የወጣቶች ትልቁ የኃይል ምንጭ ነው። በአሁኑ የቴክኖሎጂ እና የእውቀት ዘመን፣ ባህላዊ አሰራሮችን በአዳዲስ ዘዴዎች መተካት፣ የማህበረሰብ ችግሮችን በፈጠራ መፍታት እና በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ መሰማራት የሀገርን ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል። ወጣቶች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኪነ-ጥበብ እና በማህበራዊ ዘርፎች የሚያሳይዋቸው አዳዲስ የፈጠራ ስራዎች ሀገርን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ ቁልፍ መሳሪያዎች ናቸው።
በተጨማሪም፣ ወጣቶች በማህበራዊ ሀላፊነት፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች፣ በአካባቢ ጥበቃ እና በማህበረሰብ ልማት ስራዎች ላይ ንቁ ተሳትፎ ሲያደርጉ የሰላም እና የአንድነት አምባሳደር በመሆን የሀገርን ዘላቂ ህልውና ያረጋግጣሉ። ዛሬ በምንገኝበት የዲጂታል ዘመን፣ ማህበራዊ ሚዲያ የወጣቱን አቅም፣ እውቀት እና አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለትውልድ ግንባታ እና ለሰላም ማስፈን ለማዋል ትልቅ አስተማሪና አስተሳስሪ መሳሪያ እየሆነ መጥቷል።
መንግስት፣ ማህበረሰቡ እና የሚመለከታቸው አካላት የወጣቶችን የፈጠራ አቅም የሚያበረታቱ እድሎችን ማመቻቸት ይኖርባቸዋል። ወጣቶች ሀገራዊ ራዕይን አንግበው፣ ሰላምን፣ አንድነትን እና ልማትን በማጠናከር በቁርጠኝነት ሲንቀሳቀሱ የበለፀገች እና ጠንካራ ሀገርን እውን ማድረግ ይቻላል።
የክረምት በጎ ፍቃድን ምክንያት በማድረግ የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ከጤና ሚኒስትር፣ከየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት እና ሚድያ ዘርፍ እና የወጣቶች ክንፍ ጋር በጋራ በመሆን ንቁ ወጣቶች ለሀገር ግንባታ በሚል ርእስ ከ300 በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች ስልጠና ሰተዋል።