በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት

በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት, Public & Government Service, ሀላባ ዞን በሸኖ ከተማ, Alaba K'ulito.

ፕላኑን መሰረት ያደረጉ ከተሞችን ከመፍጠር በሻገር ለነዋሪው ሰብና ማረክ ከተማ ለማድረግ ፕላኑን ማስጠበቅና የማስዋብ ስራ መስራት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው።በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀ...
02/09/2026

ፕላኑን መሰረት ያደረጉ ከተሞችን ከመፍጠር በሻገር ለነዋሪው ሰብና ማረክ ከተማ ለማድረግ ፕላኑን ማስጠበቅና የማስዋብ ስራ መስራት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ፕላኑን መሰረት ያደረጉ ከተሞችን ከመፍጠር በሻገር ለነዋሪው ሰብና ማረክ ከተማ ለማድረግ ፕላኑን ማስጠበቅና የማስዋብ ስራ መስራት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር እንደሆነ ተገለፀ።

በመሆኑም በወረዳው ማዕከል በበሸኖ ከተማ ፕላኑን መሰረት በማድረግ ከዚህ ቀደም በተላይ በዋና ዋና መንገዶች ላይ ተነሺ የሆኑ ቤቶችን በመንሳት ፕላኑን የማስጠበቅ ስራ መሰረቱ ይታወቃል በመሆኑም ቀሪ ስራዎችን በመጠናቀቅ መልሶ ለማልማትና ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ ለመከናወን በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

በዚህም በዛሬው ቀን የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር ማህድ አህመድና የከተማው ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ሱራጅ በተገኙበት ቀሪ የሆኑ ስራዎችን የመስራትና በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን መከናወን ተችሏል።

ዘገባው የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ነው።

የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አድሱ ጽህፈት ቤት ግንባታ በወረዳው ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ ምልከታ ተደረገ።በዌራ ዲጆ ወረዳ የ...
29/08/2026

የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አድሱ ጽህፈት ቤት ግንባታ በወረዳው ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ ምልከታ ተደረገ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ የምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት አድሱ ጽህፈት ቤት ግንባታ ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ባሙድ ጡሚሶ፣የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ መሐመድ ጃተኖን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳ ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 23/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

ከዞን የተሰማራው ሱፐርቪዥን ቡዱን   ኢንሼቲቭ አከል የሆነዉን የቡና ልማት በበሸኖ ከተማ ነዋሪ ጓሮ ምልከታ ተደረገ።ሶስተኛዉን ቀን ያየዘዉ ከሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የተሰማራው...
29/08/2026

ከዞን የተሰማራው ሱፐርቪዥን ቡዱን ኢንሼቲቭ አከል የሆነዉን የቡና ልማት በበሸኖ ከተማ ነዋሪ ጓሮ ምልከታ ተደረገ።

ሶስተኛዉን ቀን ያየዘዉ ከሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የተሰማራው የሱፐርቪዥን ቡድን ኢንሼቲቭ አከል የሆነዉን የቡና ልማት በበሸኖ ከተማ ነዋሪ ጓሮ ምልከታ አድርጓል።

የሀላባ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ ምክትል ሀላፊ ወይዘሪት ሙሉ ሸንቆ፤ የሀላባ ዞን ኢንተርፕራይዝና ስራ እድል ፈጠራ መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ በድሩ ሎምብሶ እንዲሁም የወረዳዉ ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ተገኝተዉ ምልከታ አድርጓል።

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ማዕከል በበሸኖ ከተማ የህገ ወጥ መሬት ወረራን ለመከላከል የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።በዌራ ዲጆ ወረዳ ማዕከል በበሸኖ ከተማ የህገ ወጥ መሬት ወረ...
19/08/2026

በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ማዕከል በበሸኖ ከተማ የህገ ወጥ መሬት ወረራን ለመከላከል የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ነው።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ማዕከል በበሸኖ ከተማ የህገ ወጥ መሬት ወረራን ለመከላከል የተዘጋጀ የንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

ለንቅናቄው መድረክ የተዘጋጀ ሰነድ በወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ምክትልና የመሬት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ያሲን ቦርጎቶ አማካኝነት በዝርዝር እየቀረበ ነው።

በንቅናቄው መድረክ የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አ/ረህማን ጀማል፣የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ስራአስኪያጅ አቶ ኤልያስ ሱራጅን ጨምሮ የከተማ ልማትና የማዘጋጃ ቤት ባለሙያዎች፣የከተማው ነዋሪዎችና ነጋዴዎች ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሐሴ 13/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የሀላባ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው። የሀላባ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀላባ ቁሊቶ ከ...
18/08/2026

የሀላባ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው።

የሀላባ ዞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።

በጉባኤ ላይ በመክፈቻው ንግግር ያደረጉት የሀላባ ዞን ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ረውዳ ዘይኔ ምክር ቤቱ ባደረገው ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ በበጀት ዓመቱ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት መገለጫ መሆኑን በመግለፅ በዞኑ የህዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ አበክሮ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ምክር ቤቱ ባለፉት ወራት የህዝብ ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኝ፤ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን ብሎም በህዝብና በመንግስት መካከል መተማመን እንዲጎለብት ሲተጋ መቆየቱን ጠቁመዋል።

በዞኑ እስከ ታችኛው መዋቅር የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተነደፉ ዕቅዶች በአግባቡ መተግበራቸውን ምክር ቤቱ በየጊዜው በመገምገም እና ጉድለቶችን እንዲታረሙ በመስራቱ ባለፉት የ12 ወራት ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግቧል ብለዋል።

በዞኑ የህዝቡ ተጠቃሚነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ የመጣ መሆኑን በጥልቀት ጠቅሰዋል።

ይህንን የተጀመረ መልካም የልማት ጉዞ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ምክር ቤቱ በዞን አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የእቅድ አፈጻጸምና ሌሎችም አጀንዳዎች ላይ እየተወያየ እንደሚገኝ የዞኑ ኮሙኒኬሽን አስታውቋል።

 የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 12-13/2018 ዓ/ም ይካሄዳል - ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ረውዳ ዘይኔ=====ነሀሴ 8...
14/08/2026


የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 12-13/2018 ዓ/ም ይካሄዳል - ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ረውዳ ዘይኔ
=====

ነሀሴ 8/2018 የሀላባ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት የስራ ዘመን 21ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከነሐሴ 12-13/2018 ዓ/ም እንደሚካሄድ የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ ክቡር ወይዘሮ ረውዳ ዘይኔ አስታውቀዋል።

ምክር ቤቱ በሚያካሂደው መደበኛ ጉባኤ በሚቀርቡለት ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ ምክትል አፈ-ጉባኤዋ ገልጸዋል።

በዚህም የዞን ካቢኔ አባላት፣ የክልልና የዞን ምክር ቤት አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ነሀሴ 12/2018 ዓ.ም በሀላባ ዞን አዲሱ አስተዳደር ህንጻ አዳራሽ በሚካሄደው በዚሁ ጉባኤ ላይ በዕለቱ ልክ ከጠዋቱ 1፡30 ጀምረው እንድትገኙ በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

እንዲሁም ከጉባኤው በፊት አንድ ቀን አስቀድሞ ማለትም ሰኞ ዕለት ነሀሴ 11/2018 ዓ/ም በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን የመስክ ምልከታ በምክር ቤት አባላት እንደሚደረግም ገልጸዋል።

ለዚህም በዞኑ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን በመስክ ምልከታ ለማድረግ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ምክትል አፈ ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የምክር ቤት አባላትም በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በሀላባ ዞን አዲሱ አስተዳደር ጽ/ቤት በመገኘት በመስክ ምልከታው እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የሀላባ ዞን መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ

"ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ "በሚል መሪ ቃል በ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ላይ በፓርቲ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለከተማና ለአርሶአደሩ ግንባር ህብረቶች፣ለምሁራን ግን...
13/08/2026

"ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ "በሚል መሪ ቃል በ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ላይ በፓርቲ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለከተማና ለአርሶአደሩ ግንባር ህብረቶች፣ለምሁራን ግንባር፣ለኢንተርፕራይዝ ግንባር፣ለሴቶች የእውቅና መርሃግብር ተካሂዷል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ " በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ላይ በፓርቲ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለፐብሊ...
13/08/2026

በዌራ ዲጆ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ " በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ላይ በፓርቲ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለፐብሊክ ሰርቫንት ማህበራዊ መሠረት ህብረቶች የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተ።

በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት "ሁሉ አቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ " በሚል መሪ ቃል የ2018 በጀት አመት ማጠቃለያ ላይ በፓርቲ ስራዎች የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ለፐብሊክ ሰርቫንት ማህበራዊ መሠረት ህብረቶች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።

በዚህም መሠረት፦
1ኛ የኢኮኖሚ ዘርፍ ቁ.1 ብልጽግና ህብረት
2ኛ የአስተዳደር ዘርፍ ብልጽግና ህብረት
3ኛ የኢኮኖሚ ዘርፍ ቁ.2 ብልጽግና ህብረት
4ኛ የማህበራዊ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት በመሆን የዋንጫና የሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሐሴ 7/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በሲንቢጣ ቀበሌ በአርሶአደሩ ማሳ በመልማት ላይ የሚገኙ የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎች ምልከታ ተደረገ።በዌራ ዲጆ ወረዳ በሲንቢጣ ቀበሌ...
09/08/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ በሲንቢጣ ቀበሌ በአርሶአደሩ ማሳ በመልማት ላይ የሚገኙ የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎች ምልከታ ተደረገ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ በሲንቢጣ ቀበሌ በ2018 ዓ.ም ምርት ዘመን በአርሶአደሩ ማሳ በመልማት ላይ የሚገኙ የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎች ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው የቲማቲም ማሳ፣ሙዝ፣ፓፓያና ሌሎች የግብርና ልማት ተግባራት ያለበት ደረጃ የወረዳ አስተባባሪዎች ተዟዙረው ምልከታ ለማድረግ ችለዋል።

በምልከታው ላይ የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አ/ረህማን ጀማል፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ባሙድ ጠሚሶ፣የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትልና የተፈጥሮ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አ/ሐይ ሙንድኖ በጋራ ምልከታ አድርጓል።

ነሐሴ 3/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)
➭ዘውትር ወቅታዊና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት፦

➭የፌስቡክ Link፦ https://www.facebook.com/WeradijocommunictionBesheno

➭የቴሌግራም Link፦
https://t.me/+1qmn32XrZXNhMDM0

➭ቲክቶክ፦https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8zP0q4a1eRa&_r=1

➪ዩቲዩብ፦https://youtube.com/?si=EVzVU4h-1n1N9iVR

➪ኢንስታግራም፦https://www.instagram.com/weeraadijo?igsh=MWxrdjhnbzd6Z2I4Zw==

➪ዋትሳፕ፦https://whatsapp.com/channel/0029Vb3NQPGCMY0PHtXFtQ2E

➪ቲውተር፦https://x.com/WeraDijo44731?t=If2s1TQpGrel3lNyUr75kg&s=09

➡ አስደማሚ የልማት ጉዞ በሀላባ፦በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በለውጡ መንግሥት በተሰጠው ብስለት የተሞላ የአመራር ሚና በየዘርፉ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማሳለጥ አመርቂ ውጤቶች...
09/08/2026

➡ አስደማሚ የልማት ጉዞ በሀላባ፦
በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በለውጡ መንግሥት በተሰጠው ብስለት የተሞላ የአመራር ሚና በየዘርፉ የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተግባራትን በማሳለጥ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግቧል።

በዚህም በለውጡ መንግሥት በተለይም የአመራር አንድነትን ከመገንባት ጀምሮ የተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ በማረጋገጥ በየዘርፉ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ተግባራትን መከናወን ተችሏል።

የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ሙህዲን ሁሴን ባለፉት አመታት በዞኑ ህዝብ ተሳትፎ በቅንጅትና በአንድነት በሁሉም ዘርፍ ዘመን ተሻጋሪና ለቀጣይ ትውልድ ለመውረስ የሚያስችሉና ተጨባጭ በርካታ ግዙፍ ልማት ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።

ለአብነት በዞኑ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ከመገንባትና የህዝብን ተጠቃሚነት በውል ከማረጋገጥ አንጻር የተመዘገቡ ስኬቶችን አቶ ሙህዲን ሲገልጹ፦
በዞኑ በህዝብ ተሳትፎ በሶስት ፌዝ እየተገነባ ያለው የሀላባ ኢንተርናሽናል ስታዲየም የመጀመሪያ ፌዝ ተመርቆ ሀገር አቀፍ ጨዋታዎች መስተናገድ ጀምረዋል።

በተጨማሪም ግዙፉ የሀላባ ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ህንጻ፣የሀላባ ቁሊቶ መሶብ ተመርቀው የመንግሥትን አገልግሎት በአንድ ማዕከል መስጠት ተችሏል።
ይህ ብቻም ሳይሆን በየዘርፉ በማህበራዊ ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ
በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችለናል።
የሀላባ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ፣
ነሀሴ 3/2018 ዓ.ም

Address

ሀላባ ዞን በሸኖ ከተማ
Alaba K'ulito

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን በዌራ ዲጆ ወረዳ የበሸኖ ከተማ ማዘጋጃ ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share