02/09/2026
ፕላኑን መሰረት ያደረጉ ከተሞችን ከመፍጠር በሻገር ለነዋሪው ሰብና ማረክ ከተማ ለማድረግ ፕላኑን ማስጠበቅና የማስዋብ ስራ መስራት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ፕላኑን መሰረት ያደረጉ ከተሞችን ከመፍጠር በሻገር ለነዋሪው ሰብና ማረክ ከተማ ለማድረግ ፕላኑን ማስጠበቅና የማስዋብ ስራ መስራት ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር እንደሆነ ተገለፀ።
በመሆኑም በወረዳው ማዕከል በበሸኖ ከተማ ፕላኑን መሰረት በማድረግ ከዚህ ቀደም በተላይ በዋና ዋና መንገዶች ላይ ተነሺ የሆኑ ቤቶችን በመንሳት ፕላኑን የማስጠበቅ ስራ መሰረቱ ይታወቃል በመሆኑም ቀሪ ስራዎችን በመጠናቀቅ መልሶ ለማልማትና ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ ለመከናወን በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
በዚህም በዛሬው ቀን የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ኢ/ር ማህድ አህመድና የከተማው ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ኤልያስ ሱራጅ በተገኙበት ቀሪ የሆኑ ስራዎችን የመስራትና በቀጣይ ለሚከናወኑ ተግባራት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን መከናወን ተችሏል።
ዘገባው የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ነው።