በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ይህ የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ነዉ follow በማድረግ መረጃዎችን ያግኙ!!

 #የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት በዛሬው  ዕለት በወረዳ ምክር ቤት በ7ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በአስተዳደር ዘርፍ በ2018 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀም የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝ...
30/08/2026

#የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት በወረዳ ምክር ቤት በ7ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ በአስተዳደር ዘርፍ በ2018 ዓ.ም እቅድ አፈፃፀም የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ሰርተፍኬት ሽልማት ተበርክቶለታል ።

የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም ገለፁ!በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት...
30/08/2026

የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም ገለፁ!

በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህም የዌራ ዲጆ ወረዳ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 ዓ.ም በጀት አመት ዕቅድ ሪፖርት ለ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ጉባኤ አቅርበዋል።

ይህን ተከትሎ በቀረበው ሪፖርት መሠረት ከምክር ቤት አባላት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው፣ከመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።

ለምክር ቤት አባላቱ በግብርና፣ጤና፣ውሃ፣መንገድ፣ትምህርት ላይ በተነሱ ጥያቄዎች ከጽህፈት ቤቱ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት ተችሏል።

የዌራ ዲጆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም በበኩላቸው እንደተናገሩት..የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

በወረዳው ከለውጡ በኃላ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፣ለአብነት በከተማ፣በግብርና፣በጤና፣በትምህርት እንድሁም በንጹሁ የመጠጥ ዉሃ፣በመንገድና በሌሎች በአስተዳደር፣በኢኮኖሚ፣በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ደረጃ በደረጃ በርካታ ተግባራት ማከናወን መቻሉን አስገንዝበዋል።

በቀጣይ ከምክር ቤት አባላቱ ለተነሱ አንኳር ጥያቄዎች የወረዳ አስተዳደር ምላሽ እንዲያገኙ ለማስቻል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበስ በትኩረት እንደሚሰራ አቶ አብዲ አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የምክር ቤቱ አባላት ለምክር ቤቱ በዋና አስተዳዳሪው አማካኝነት የቀረበውን ሪፖርት በሙሉ ድምፅ ለማጽደቅ ችለዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሐሴ 24/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

በዌራ ዲጆ ወረዳ የምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ከመጀመሩ በፊት የፎቶ ኤግዚቢሽን ምልከታ መርሃግብር ተከናወነ።በወረዳው አስተዳደርና በመንግሥት ኮሚዩ...
30/08/2026

በዌራ ዲጆ ወረዳ የምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ከመጀመሩ በፊት የፎቶ ኤግዚቢሽን ምልከታ መርሃግብር ተከናወነ።

በወረዳው አስተዳደርና በመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አዘጋጅነት በወረዳው በተለያዩ ግዜያት በሁሉም ዘርፍ የተከናወኑ መርሃግብሮች በፎቶ ኤግዚቢሽን ለምክር ቤት አባላት ቀርቧል።

ከጥቂት ደቂቃዎች በኃላ በዌራ ዲጆ ወረዳ የምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የሚጀምር ይሆናል።

የፎቶ ኤግዚብሽኑን የወረዳው መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነስረዲን ሙንድኖ አማካኝነት በሰፊው ተብራርቶ ቀርቧል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 24/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ተጀመረ።በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ መ...
30/08/2026

የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ተጀመረ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል።

የጉባኤ መድረኩን የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ መሐመድ ጃተኖ መክፈቻ ንግግር በማድረግ፣የዕለቱን አጀንዳ በማቅረብ የ2018 ዓ.ም ቃለ ጉባዔ በምክር ቤቱ ሙሉ ድምፅ ጸድቋል።

በጉባኤው መድረክ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አ/ረህማን ጀማል፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ባሙድ ጡሚሶ፣የሀላባ ዞን ምክር ቤት ህግና ፍትህ ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሁሴን ኢብራሂምን ጨምሮ የወረዳ አጠቃላይ አመራሮችና የዞንና የወረዳ ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 24/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የዌራ ዲጆ ወረዳ አስተዳደር ለወረዳው ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የአስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያቀ...
30/08/2026

የዌራ ዲጆ ወረዳ አስተዳደር ለወረዳው ምክር ቤት አባላት የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የአስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ነው።

በወረዳው የ1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ በወረዳው ማዕከል በበሸኖ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህም ለጉባኤው መድረክ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣ለምክር ቤት አባላቱ የአስፈፃሚ ሴክተር መስሪያ ቤቶችን የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛል።

ለጉባኤው መድረክ በቀረበው ሪፖርት መነሻ ከምክር ቤቱ አባላት ሀሳብና አስተያየት ተሰጥቶ በሰፊው ውይይት በማድረግ ሪፖርቱ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 24/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛ...
29/08/2026

የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ነው።

በዚህም በቁሉቢ ቀበሌ በአርሶአደሩ ማሳ በመደበኛ በልግ አዝመራ በክላስተር በመልማት ላይ የሚገኝ የበቆሎ ክላስተር ምልከታ አድርጓል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 23/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

የወረዳው ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።በዌራ...
29/08/2026

የወረዳው ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ነው።

በዚህም በአጆና ጢጣሊ-ብጦራ ቀበሌዎች ላይ ለተረጂዎች መጠባበቂያ የተዘራው የስንዴ ሰብል የደረሰበት ደረጃ የዞኑና የወረዳ ምክር ቤት አባላት ምልከታ አድርገዋል።

በምልከታው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ባሙድ ጡሚሶ፣የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ መሐመድ ጃተኖን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳ አመራሮችና የምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 23/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ ማ...
29/08/2026

በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ ማድረግ ጀመሩ።

በዌራ ዲጆ ወረዳ ምክር ቤት አባላት 1ኛ ዙር 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ምክንያት በማድረግ በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የግብርና ልማት ስራዎች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ነው።

በዚህም በሲንቢጣ ቀበሌ በትምህርት ቤት ማሳ ለውስጥ ገቢ የተዘራው የቺያ-ሲድ ሰብል በምክር ቤቱ አባላት ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዲ አደም፣የወረዳው የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሱራጅ ጎድሶ፣የወረዳው ምክትል አስተዳዳና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጎበና ሰማን፣የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ባሙድ ጡሚሶ፣የወረዳው ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ የተከበሩ መሐመድ ጃተኖን ጨምሮ ሌሎች የወረዳ አመራሮችና የምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 23/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

28/08/2026
‎በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ‎የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ወረዳ አቀፍ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።‎‎በዌራ ዲጆ ወረዳ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በሕጋዊና ...
28/08/2026

‎በሀላባ ዞን ዌራ ዲጆ ወረዳ ‎የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ወረዳ አቀፍ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።

‎በዌራ ዲጆ ወረዳ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በሕጋዊና አስተማማኝ መንገድ ማካሄድ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን መከላከልና ሕብረተሰቡን በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ ዓላማ ያደረገ ወረዳ አቀፍ የንቅናቄ መድረክ ተካሄዷል።

ለመድረኩ የተዘጋጀ ሰነድ በወረዳው ኢንተርፕራይዝና ስራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሀራርሶ፤የወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጽ/ቤት ባለሙያ አቶ ባህሉ አማካኝነት በሰፊው ተብራርቶ ቀርቧል።

የማጠቃለያ መድረኩን የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪና ፖለቲካ አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አ/ረህማን ጀማል፣በወረዳው ኢንተርፕራይዝና ስራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር ሀራርሶ፤የወረዳው ሰራተኛና ማህበራዊ ጽ/ቤት ባለሙያ አቶ ባህሉ በጋራ መርተውታል።

በዚህም ወቅት የመድረኩ ዋና አላማ የውጭ ሀገር ሥራ ዕድልን ለመጠቀም የሚፈልጉ ዜጎች በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲሰማሩ ከሕገወጥ የሰዎች ዝውውርና ከተለያዩ የማታለያ ዘዴዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

ለመድረኩ በቀረበው ሰነድ መነሻ ከመድረኩ ተሳታፊዎች በርካታ ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው፣ከመድረኩ ምላሽና ማብራርያ በመስጠት፣ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መግባባት በመቻል ተጠናቋል።

በመድረኩ የወረዳው የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ባሙድ ጡሚሶ፣የወረዳው ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብደላህ ጀማልን ጨምሮ ሌሎች የወረዳው አመራሮችና የስራ ዕድል ፈጠራና የጸጥታ ተቋማት እንድሁም የሰራተኛ ማህበራዊ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

✍️በደሳለኝ ቱልቻ
ነሃሴ 22/2018 በሸኖ፣(ዌራ ዲጆ ኮሚዩኒኬሽን)

Address

Besheno
Alaba K'ulito
HALABA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to በሀላባ ዞን የዌራ ዲጆ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት:

Shortcuts

Share