13/08/2026
ኮሚሽኑ በየደረጃው ጠንካራ የፓርቲ ተቋም እንዲፈጠርና የአባላት መብትና ግዴታ እንዲከበር ጠንካራ ስራዎች እየሰራ ነው፦አቶ ጀማል መሀመድ
የዌራ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን
" ሁሉአቀፍ እምርታ ለሁለንተናዊ ከፍታ" በምል መሪህ በተካሃደው ወረዳዊ ኮንፍረንስ መድረክ ላይ የ2018 በጀት ዓመት የኮሚሽን አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ኦሬንቴሽን የቀረባ ስሆን ፤፦
መድረኩ ብልጽግና ፓርቲ የሚመራበትን የመደመር እሳቤ፣እሴቶችና መርሆዎች እንዲሁም የፖለቲካ ፕሮግራሞች ለአባላትና ለአመራሩ ግልጸኝነት የመፍጠር ጠንካራ ስራ መስራቱን አመለከተ።
ኮሚሽን ጽህፈት ቤቱ በሁሉም አደረጃጀት ተቋሙን የመገንባት፣ የአባላትንና የአመራሩን መብትና ጥቅሞች እንዲሁም የፓርቲውን ሀብትና ንብረት የማስጠበቅ ስራዎች መስራቱንም ገልጿል።
የኮሚሽን ጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ጀማል መሀመድ በወረዳ ደረጃ በተካሄደ የወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የዕቅድ አፈጻጸም መጠቃለያና ፈጻሚ ዝግጅት መድረክ ላይ የጽህፈት ቤታቸውን አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።
ጽህፈት ቤቱ ጠንካራ ፓርቲ በየደረጃው እንዲገነባ ጠንካራ የክትትልና የድጋፍ ስራዎች መስራቱን የገለጹት አቶ ጀማል መሀመድ የተሻለ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት ብርቱ ርብርብ መደረጉንም አመላክተዋል።
ኮሚሽን ጽህፈት ቤቱ በየደረጃው የተቀናጀና ውጤታማ የድጋፍና ክትትል ስራዎች ማድረጉንም ገልጸው፣በእነዚህ ጥረቶችም የፓርቲውን ህዝባዊ አላማዎች ማስረጽና ማስገንዘብ ስለመቻሉም አብራርተዋል።
[ ] ሆኖም የፓርቲ መተዳደሪያ ደንቦችና መመሪያዎችን ለአባላት ለማስገንዘብ በበቂ ደረጃና ጥራት ከመስራት አኳያ፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአንዳንድ መዋቅሮች ስራ ላይ መዋላቸውን ያለማረጋገጥ ችግር፣የሚቀርቡ ቅሬታዎችን አጣርቶ ቶሎ ምላሽ የተሰጠበት ፈይለ አደራጅቶ ከማስቀመጥ አኳያ ውስንነቶች እንዳሉም አቶ ጀማል መሀመድገልጸዋል።
በአዲሱ በጀት ዓመት በየደረጃው ጠንካራ ፓርቲ በመገንባት የበለጸገ ወረዳ ዞንና ሀገር ለመገንባት ተቀናጅቶና ተናቦ ለመስራት ኮሚሽኑ ዝግጁ መሆኑንም አቶ ጀማል መሀመድ አረጋግጠዋል።
!!