14/08/2026
በአርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እየተሰጠ ያለዉ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሐ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ፡፡
አርባ ምንጭ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ/ም (አርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ)
በአርባ ምንጭ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እየተሰጠ ያለዉ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሐ ግብር ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ፡፡
ኮሌጁ ከዚህ ቀደም በመደበኛነት ለማህበረሰቡ እየሰጠ የቆየዉን ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ልየታ አገልግሎት በማጠናክር እና ከክረምት የበጎ ፍቃድ መርሐ ግብር ጋር በማቀናጀት አገልግሎቱን እየሰጠ ይገኛል፡፡
በመርሃ ግብሩ የደም ግፊት ምርመራ፤ የደም ስኳር መጠን ልኬት፤ የዉፍረት መጠን ልኬት ከዚህም በተጨማሪ የኤች አይ ቪ ምርመራ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በሰፊዉ እየተሰጠ ይገኛል፡፡