07/09/2026
በጋሞ በገረሴ ዙሪያ ወረዳ ግብርና ጽሕፈት ቤት በዋና ኃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት ዶ/ር አዳነ ደስታ የወረዳችን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግኑኝነት ዘርፍ ዋና ኃላፊ ሆነው በመሾማቸው ለተቋሙ አዲስ ዋና ኃላፊ ሆነው ለተሾሙት ለኢንጂነር ለገሰ ጮቆ የሥራ ርክብክብ ፈጽመዋል።
ዶ/ር አዳነ ደስታ፡ በተቋማችን ላበረከቱት አስተዋጽኦ እያመሰገንን፣ ለላቀ የሕዝብና የመንግሥት ኃላፊነት የተመደቡ በመሆንም ውጤታማ የሥራ ጊዜ እንድሆን ከልብ እንመኛለን።
ኢንጂነር ለገሰ ጮቆ፡ ወደ ተቋማችን እንኳን በደህና መጡ እያልን፤ አዲሱ የኃላፊነት ዘመንዎ የላቀ ስኬት፣ ልማትና መልካም ውጤት የሚመዘገብበት እንዲሆንልዎ እንመኛለን!