የጋሞ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Mintch
  • የጋሞ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት

የጋሞ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት ''We make a living by what we get, but we make a life by what we give." — Winston Churchill

በጋሞ ዞን   የሚገኙ  #ወጣቶች የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር መነሻ በማድረግ የልማት ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ።‎‎በወረዳው የሚገኙ ወጣቶች በበጎ ፈቃደኝነት የወቅቱን የመኸር...
20/08/2026

በጋሞ ዞን የሚገኙ #ወጣቶች የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር መነሻ በማድረግ የልማት ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ።

‎በወረዳው የሚገኙ ወጣቶች በበጎ ፈቃደኝነት የወቅቱን የመኸር እርሻ በመደጋገፍ ስሜት ለአቅመ ደካማና አረጋውያን በነፃ እያረሱ ይገኛሉ።

‎ወጣቶቹ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ለአካባቢያቸው ልማትና ለወገኖቻቸው ደጋፊነት ማዋላቸው ትልቅ የውስጥ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ገልጸዋል።



በጋሞ ዞን ብርብር ከተማ አስተዳደር በአልጌ ቀበሌ የክረምቱ በጎ ተግባር መስክ አንዱ በሆነው ትምህርት ቤቶችን ለ2019 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ምቹ የማድረግ በህ/ሰብ ተሳትፎ የተገነባ;
17/08/2026

በጋሞ ዞን ብርብር ከተማ አስተዳደር በአልጌ ቀበሌ የክረምቱ በጎ ተግባር መስክ አንዱ በሆነው ትምህርት ቤቶችን ለ2019 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ምቹ የማድረግ በህ/ሰብ ተሳትፎ የተገነባ;

‎በጋሞ ዞን ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶርዜ ክላስተር የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነዉ 2ኛው ዙር «ሻዬ ዳና ዋንጫ» የእግር ኳስ ውድድር መካሄድ ጀመረ፤
16/08/2026

‎በጋሞ ዞን ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ በዶርዜ ክላስተር የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነዉ 2ኛው ዙር «ሻዬ ዳና ዋንጫ» የእግር ኳስ ውድድር መካሄድ ጀመረ፤

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች የ12.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ምየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋ...
15/08/2026

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች የ12.5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ

ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በጋሞ ዞን ጋጮ ባባ ወረዳ የማዞ ዶይሳ ቀበሌ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች በ12.5 ሚሊዮን ብር ወጪ የመኖሪያ ቤቶችን እንደሚገነባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ ገለጹ።

አምባሳደር ብርሃኑ ይህንን ያወሱት የተፈናቀሉ ዜጎችን በቋሚነት ለማቋቋም የሚከናወኑ ሥራዎችን ለመደገፍ በብርብር ከተማ አስተዳደር ደልቦ ቀበሌ በተገኙበት ወቅት ነው።

​በድጋፍ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ የጥበብ፣ የምክርና የተግሳጽ ምድር በሆነችው እንዲሁም መከባበርና ፍቅር በሰፈነባት የጋሞ ምድር ተገኝተው ይህንን ሰብአዊ ድጋፍ በማድረጋቸው የተሰማቸውን ላቅ ያለ ደስታ ገልጸዋል።

​አምባሳደር ብርሃኑ አክለውም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አጋር አካላትን በማስተባበር በአደጋው ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚሆኑ የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት የተገኘ መሆኑን ጠቁመው፤ ይህ ድጋፍ ከቤት ግንባታው ባሻገር የተጎዱ ወገኖቻችንን ለማበርታት፣ አብሮነትን ለማጠናከር እና ተስፋ ለመስጠት ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

በተጨማሪም በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስተባባሪነት በአደጋው ለተፈናቀሉ ሕፃናትና የህብረተሰብ ክፍሎች የአልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፣ በቦታው የአረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሃ ግብርም ተካሂዷል።

አምባሳደር ብርሃኑ የመርሃ ግብሩ እንዲሳካ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

​በመድረኩ የተገኙት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የጋሞ ዞን በተፈጥሮ ጸጋዎች፣ በፍራፍሬ፣ በማዕድን፣ በቱሪዝምና በሌሎችም ዘርፎች የታደለች አካባቢ መሆኗን ገልጸዋል።

ባለፈው መጋቢት ወር በደረሰው ድገተኛ የተፈጥሮ አደጋ በሰው ህይወት፣ አካልና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ያስታወሱት ዋና አስተዳዳሪው፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ላይ በወሳኝ ሰዓት በመድረሱ በዞኑ አስተዳደርና በተጎጂዎች ስም ምስጋና አቅርበዋል።

​በስፍራው የትምህርት ቤት፣ የጤና ጣቢያና ሌሎች መሠረታዊ ልማቶችን ሙሉ በሙሉ መልሶ ለማሟላት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ያቀረቡት ደምሴ አድማሱ (ዶ/ር)፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ ላበረከቱት ወንድማማችነትና አለኝታነታዊ አስተዋጽኦ የላቀ አክብሮታቸውን ገልጸዋል።

​የዞኑ አስተዳደር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ላደረገው የላቀ ድጋፍ በማመስገን የተደረገው የቤት ግንባታና የቁሳቁስ ድጋፍ የተፈናቀሉ ወገኖችን በዘላቂነት ለማቋቋም ከማገዙ ባሻገር ለተጎጂዎች ትልቅ ስነ-ልቦናዊ ብርታት እንደሚሆን በመግለጽ የተጀመረው የተቀናጀ የድጋፍ አጋርነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስቧል።

Gamo Zone Government Communication Affairs Department

  በጋሞ ዞን   የጭልአሼ ከተማ ወጣቶች የጭልአሼ ከተማ ብልጽግና  ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት  ድንበር የለሽ የክረምት በጎ ስራን ለመስራት ወደ ጎቾ ከተማ ገብተዋል።ነሐሴ 6/2018...
12/08/2026


በጋሞ ዞን የጭልአሼ ከተማ ወጣቶች
የጭልአሼ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ድንበር የለሽ የክረምት በጎ ስራን ለመስራት ወደ ጎቾ ከተማ ገብተዋል።

ነሐሴ 6/2018ዓ.ም

በቦረዳ ወረዳ የጭልአሼ ከተማ ወጣቶች በጭልአሼ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አስተባባሪነት ድንበር የለሽ የክረምት በጎ ስራን ለመስራት ወደ ጎቾ ከተማ ስገቡ የጎቾ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ አባላትና የጎቾ ከተማ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል ።

በጋሞ ዞን   የወጣቶች ስዕብና  እና የህወት ክህሎት ስልጠና በወረዳ ማዕከል በወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት  ሰው-ለሰው ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት  ጋር በጋራ በመሆ...
12/08/2026

በጋሞ ዞን የወጣቶች ስዕብና እና የህወት ክህሎት ስልጠና በወረዳ ማዕከል በወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት ሰው-ለሰው ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን በሁለንተናዊ ስብዕና ግንባታ ሥልጠና በወረዳ ማዕከል ለወጣቶች እየተሠጠ ይገኛል።

የገረሴ ወጣቶች በዝሎ ቀጠና  አቅመ ደካማ የአቶ ትሊንቴ ሙልአታ ቤት ስገነቡ;
12/08/2026

የገረሴ ወጣቶች በዝሎ ቀጠና አቅመ ደካማ የአቶ ትሊንቴ ሙልአታ ቤት ስገነቡ;

የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለሚገኙ ሴት ታራሚዎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገየጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለሚ...
10/08/2026

የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለሚገኙ ሴት ታራሚዎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ለሚገኙ ሴቶችና ልጆቻቸው ከ110 ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።

የጋሞ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ምህረት ኩንታ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት፣ መምሪያው በተለያዩ ጊዜያት በማረሚያ ተቋሙ በመገኘት ለሴቶችና ሕፃናት አስፈላጊውን ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል።

የዘንድሮውን የክረምት በጎ አገልግሎት በማስመልከት በጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም በመገኘት በሕግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ሴቶችና ሕፃናት ከ110 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ የንጽህና መጠበቂያዎች፣ የሕፃናት ወተት፣ የትምህርት ቁሳቁሶችና መሰል ድጋፎችን ማድረጉን ወ/ሮ ምህረት አብራርተዋል።

ኃላፊዋ አክለውም፣ መምሪያው ከቁሳቁስ ድጋፍ ባሻገር በተቋሙ ለሚገኙ ሴቶች የሥራ ዕድል እንዲፈጠርላቸውና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህም ሴቶቹ በተለያዩ የሥራ መስኮች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን አስረድተዋል።

ለሕፃናት አማራጭ ድጋፍና እንክብካቤ መፍጠር የመምሪያው ዋነኛ ዓላማ መሆኑን የጠቆሙት ወ/ሮ ምህረት፣ ወላጆቻቸው በሕግ ጥላ ሥር በመገኘታቸው ምክንያት በሜሪ ጆይ አረጋውያንና ሕፃናት ማቆያ የሚገኙ ሕፃናትን ከወላጆቻቸው ጋር የማገናኘት ሥራም እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

በማረሚያ ተቋም የሚገኙ ሴቶችና ልጆቻቸው የተለያዩ ድጋፎች የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት የድርሻቸውን እንዲወጡ ወ/ሮ ምህረት ጥሪ አቅርበዋል።

የጨንቻ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አዛዥ ም/ኮሚሽነር አጥናፉ አሰፋ በበኩላቸው፣ መምሪያው በተደጋጋሚ በሕግ ጥላ ሥር ለሚገኙ ታራሚ ሴቶች፣ እናቶችና ሕፃናት የተለያዩ ቁሳቁስ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል። ድጋፉም አንዱ ለሌላው የምንደጋገፍበት መሆናችንን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

በመጨረሻም የመምሪያው ኃላፊና ባለሙያዎች በተቋሙ የሚገኘውን የእናቶችና ሕፃናት ማቆያ በመዘዋወር ጎብኝተዋል።

በኮሚንስት ታደሰ

በጋሞ ዞን   የሚገኙ  #ወጣቶች የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር መነሻ በማድረግ የልማት ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ።‎‎በቀበሌው የሚገኙ ወጣቶች በበጎ ፈቃደኝነት የወቅቱን የመኸር...
10/08/2026

በጋሞ ዞን የሚገኙ #ወጣቶች የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር መነሻ በማድረግ የልማት ስራ እያከናወኑ ይገኛሉ።

‎በቀበሌው የሚገኙ ወጣቶች በበጎ ፈቃደኝነት የወቅቱን የመኸር እርሻ በመደጋገፍ ስሜት ለወ/ሮ በጎ ፈቃደኞች እያረሱ ይገኛሉ።

‎ወጣቶቹ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ለአካባቢያቸው ልማትና ለወገኖቻቸው ደጋፊነት ማዋላቸው ትልቅ የውስጥ እርካታ እንደፈጠረላቸውም ገልጸዋል።

Address

Arba Mintch
485882

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጋሞ ዞን ወጣቶች ጉዳይና በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share