አረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት Areka City First Instance Court

  • Home
  • Ethiopia
  • Areka
  • አረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት Areka City First Instance Court

አረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት Areka City First Instance Court Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት Areka City First Instance Court, Public Service, Wolaita Zone Areka City Administration, Areka.

በአረካ ከተማ በሁሉም ቀበሊያት የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች ሹሜት ተካዷል።አረካ፦ዛሬ በቀን 25/12/2018 ዓም በሁሉም ቀበሊያት የባህል ሕግ መሠረት በማድረግ አለመግባባቶችን የሚፈቱ የባህላዊ...
31/08/2026

በአረካ ከተማ በሁሉም ቀበሊያት የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች ሹሜት ተካዷል።
አረካ፦ዛሬ በቀን 25/12/2018 ዓም በሁሉም ቀበሊያት የባህል ሕግ መሠረት በማድረግ አለመግባባቶችን የሚፈቱ የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች በአራዳ ክ/ከተማ፣በሠፈረ ሰላም ክ/ከተማ፣በመሀል ክ/ከተማ፣በወይቦ ወጋ ማዘጋጃ፣ዮካራ ቀበሌ፣ዱቦ፣ጣድሳ፣ዶላ፣ወርሙማ፣ባሣ ጎፋራ ቀበሌዎች የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ተመርጧል።በመርሃ ግብሩ መሠረት በምርጫ ሂደት ላይ ቅሬታ ያለው ማንኛውም ቅሬታ አቅራቢ ከቀን 27/12/2018ዓም እስኬ 28/12/2018ዓም ደረስ ለአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቅሬታ መቀበያ ክፍል ቅሬታ ማቅረብ የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን።

31/08/2026
ባህላዊ ፍርድ ቤት መቋቋም ለዘጎች የተቀላጠፈ ፍትህ ለመሰጠት ጉልህ ሚና እንዳለው ተረጋገጠ
29/08/2026

ባህላዊ ፍርድ ቤት መቋቋም ለዘጎች የተቀላጠፈ ፍትህ ለመሰጠት ጉልህ ሚና እንዳለው ተረጋገጠ

የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃፍርድ ቤት የቀበሌ አስተዳደሮች እና የከተማው ባህልና ቱርዝም ሀላፊ ጋር በጋራ በመሆን የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች  አስመራጭ ኮሚቴዎችን የመሰየም መድረክ ተካሄዷ...
28/08/2026

የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃፍርድ ቤት የቀበሌ አስተዳደሮች እና የከተማው ባህልና ቱርዝም ሀላፊ ጋር በጋራ በመሆን የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች አስመራጭ ኮሚቴዎችን የመሰየም መድረክ ተካሄዷል !!!
አረካ ከተማ ነሐሴ 22/2018
የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃፍርድ ቤት የ10 ቀቤለያት አስተዳደሮች እና የከተማውባህል ቱርዝም ሀላፊ ጋር በጋራ በመሆን የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ወይም ሽማግልዎችን አስመራጭ ኮሚቴዎች መሰየም መድረክ ተካሄዷል::
የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕረዚዳንት ክቡር አቶ አክሊሉ አብራሃም እንደገለፁት የባህላዊ ፍርድ ቤት መቋቋም በማህበረሰብ ዉስጥ የሚፈጠረዉን አለመግባባቶችን በባህል ህግ ላይ ተመስርቶ እውነት እና እሴቶችን መሠረት በማድረግ ፍትህን በማስፈን ረገድ እንድሁም ለማህበረሰብ ተደራሽ የሆነ ወጪ ቆጣብና ቀለል ያለ ስርዓትን የሚከተል የፍትህ አገልግሎት እንድያገኙ የማይተካ ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም የባህላዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ወይም ሽማግልዎችን አስመራጭ ኮሚቴዎች መሰየም ጋር ተያይዞ በየቀቤለያት ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በምርጫ ወቅት መገኘት እንዳለባቸዉ አቅጣጫ ተቀምጧል።በተጨማሪም በአዋጁ ላይ የጋራ ግንዛቤ እንድኖርና በሁሉም ቀበሌ በምርጫ ሰዓት ከህብረተሰቡ የግንዛቤ ጥያቄ ቢነሰ ምላሽና ማብራሪያ ለመሰጠት እንድቻል ከፍርድ ቤቱ ለአንድ ቀበሌ ሥልጠና የወሰደ አንዳንድ ዳኛ የዳኛ ዕጥረት ባለቤት ቀበሌ ሥልጠና የወሰደ አንዳንድ የማኔጅሜንት አባላት ተመድበዋል በሰብሰባውና በሥልጠናው ሁሉም የጋራ ግንዛቤ ላይ ደረሰው ወደሥራው ገብቷል
‎በመድረኩ የአረካ ከተማ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕረዚዳንት ክቡር አቶ አክሊሉ አብራሃም ፣ የከተማው ባህልና ቱርዝም ፅ/ቤት ሓላፍ አቶ ዘላለም አድሱ፣የከተማ ፍርድ ቤት መስማትና መወሰን ዋና ስራ ሂደት አሰተባባሪ አቶ ወንድሙ ወናጎ፣ የከተማውፍርድ ቤት ማኔጀመንት አባላት እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት ተሳትፈዋል ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍርድ ቤቶች መዋቅራዊና አስተዳደራዊ ጥናት ሰነድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ ። ​ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም  የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍርድ ቤቶች መዋቅራ...
27/08/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፍርድ ቤቶች መዋቅራዊና አስተዳደራዊ ጥናት ሰነድ ዙሪያ ውይይት ተካሄደ ።

​ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፍርድ ቤቶች መዋቅራዊ እና አስተዳደራዊ የጥናት ሰነድ ለአስተዳደር ሰራተኞች ቦርድ ቀርቦ ከመፅደቁ በፊት ከሁሉም ዞኖችና ሪጅዮፖሊስ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች ጋር በበይነ-መረብ ውይይት አካሄደ።

​የጥናት ሰነዱ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የፕሬዝዳንት አማካሪ በክቡር ዳኛ አቶ አማረ ማንጆ እና በሰው ሀብት ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ መሠለች ብዙነህ የቀረበ ሲሆን የሁሉም ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች ለጥናቱ ግብዓት የሚሆኑ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን እንደግብዓት አንስተዋል።

ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ቦጋለ ፈይሳና በምክትል ፕሬዝዳንቱ ክቡር አቶ አንዱዓለም አምባዬ እንዲሁም በጥናት ቡድኑ አባላት ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቷል።

​በመጨረሻም የተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች በግብዓትነት ተካተው ሰነዱ በአስተዳደር ሰራተኞች ቦርድ ቀርቦ እንደሚፀድቅ በመድረኩ ተመላክቷል።

🖍🖍🖍🙏👇👇👇🖍🖍
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት / Wolaita S**o City High Court

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋምና ዕውቅና ለመስጠት በአዋጅ ቁ. 63/2017 ዙሪያ ከፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች ጋር ውይይት አደረገነሐሴ 19/2018 ዓ.ም | የ...
25/08/2026

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋምና ዕውቅና ለመስጠት በአዋጅ ቁ. 63/2017 ዙሪያ ከፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች ጋር ውይይት አደረገ

ነሐሴ 19/2018 ዓ.ም | የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በስሩ ከሚገኙ ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች ጋር ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን ለማቋቋምና ዕውቅና ለመስጠት በወጣው አዋጅ ቁ. 63/2017 ዙሪያ የጋራ ውይይት አካሂዷል።

ለውይይቱ መነሻ የሆነውን ሰነድ ያቀረቡት የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፍቅሬ አካለወልድ ሲሆኑ፣ በቀረበው ሰነድ ዙሪያም ሰፊና ገንቢ የሆነ የጋራ ውይይት ተካሂዷል።

የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባህላዊ ፍርድ ቤቶችን የማቋቋምና ዕውቅና የመስጠት ሥራን ከዚህ በፊት በሦስት ወረዳዎች፣ በቦሎሶ ቦምቤ፣ በአባላ አባያ እና በዳሞት ፑላሳ ወረዳዎች ጀምሯል።

በውይይቱም ይህንን ተግባር በማስፋት በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የባህላዊ ፍርድ ቤቶችን የማቋቋምና ዕውቅና የመስጠት ሥራ ለመጀመር በጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።

ስብሰባውን የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ምህረቱ ኩኬ ከምክትል ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፍቅሬ አካለወልድ ጋር በጋራ መርተዋል።

ዘገባው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ኮሚዩኒኬሽን ነው

24/08/2026
የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ሪፖርት ለምክር ቤቱ አቀረበ። አረካ፤ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍር...
21/08/2026

የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዕቅድ ሪፖርት ለምክር ቤቱ አቀረበ።

አረካ፤ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም የአረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዕቅድ የፍርድ ቤቱ ፕረዝዳንት አቶ አክሊሉ አብርሃም ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።

በክቡር ፕሬዝዳንቱ በቀረበው ሪፖርት መነሻ ውይይት በማድረግ ም/ቤቱ ሪፖርቱን መርምሮ በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

Address

Wolaita Zone Areka City Administration
Areka

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አረካ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት Areka City First Instance Court posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category