የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Asosa
  • የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ Benishangul-Gumuz Region Government Communication Affairs Bureau. It is a government organization You can follow us on: telegram: https://t.me/Bgcommn

This is the official Benishangul gumuz region communication affairs office page - where you can get all the latest news in Amharic.

ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ለርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ዕድል እንደፈጠረ የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ***********(አሶሳ፣ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም...
06/09/2026

ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ለርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ዕድል እንደፈጠረ የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ
***********

(አሶሳ፣ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም) በክልሉ በአሶሳ ከተማ የተካሄደው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ለማስተዋወቅ ዕድል እንደፈጠረ የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ገለጸ።

ከነሐሴ 27 እስከ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ የነበረው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ተጠናቋል።

የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ አመንቴ ገሺ እንደገለጹት፣ ከለውጡ ወዲህ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚያጋጥሙ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ዋና እሳቤው የአምራች እንዱስትሪውን ማስተዋወቅና የክልሉን እምቅ አቅም ማስተዋወቅ እንደሆነም አቶ አመንቴ ተናግረዋል።

ተጨባጭ ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚቻለው ኢንዱስትሪዎች በሙሉ አቅማቸው ወደ ምርት በማስገባት ለሀገር እድገት አስተዋጽኦ እንድያበረክቱ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ክልሉ ለኢንቨስትመንትና ለኢንዱስትሪ ምቹ አቅም ያለው መሆኑን የተናገሩት አቶ አመንቴ፣ ይህንን ለመጠቀም የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

ያሉንን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎቻችንን በአግባቡ በማልማትና ወደ ውጤት በመቀየር የህብረተሰቡን ህይወት በዘላቂነት ለመቀየር የጋራ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ አቶ አመንቴ ጠቁመዋል።

ቢሮው ለኤክስፖ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱት ተቋማት፣ ድርጅቶች እና የሚዲያ አካላት የእውቅናና ምስጋና መርሃ-ግብር አካሂዷል።

የኢትዮጵያ የማንሠራራት ጉዞ እና የማዕድን ዘርፉ በተኪ ምርቶች ላይ እየተጫወተ ያለው ስትራቴጂካዊ ሚና*********************ኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ሁለንተናዊ የማንሠራራት ጉዞ መ...
06/09/2026

የኢትዮጵያ የማንሠራራት ጉዞ እና የማዕድን ዘርፉ በተኪ ምርቶች ላይ እየተጫወተ ያለው ስትራቴጂካዊ ሚና
*********************

ኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ሁለንተናዊ የማንሠራራት ጉዞ መጀመሯን በተጨባጭ እያሳየች ትገኛለች። በተለይም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የኮሪደር ልማት ሥራዎች እንዲሁም እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት ኢትዮጵያ ወደ አዲስ የብልጽግና ምዕራፍ እየተሸጋገረች መሆኗን የሚያረጋግጡ ማሳያዎች ናቸው።

በዚህ ሁለንተናዊ የለውጥ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ለበርካታ አሥርተ ዓመታት በቂ አቅም፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና የተቀናጀ የመረጃ ሥርዓት ሳይገነባለት የቆየው የማዕድን ዘርፍ ዛሬ ላይ የዚህ የማንሠራራት ጉዞ ቁልፍ አካል ሆኗል።

በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ውስጥ ማዕድን ከግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ ጋር በመሆን ከአምስቱ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኖ ተለይቷል።

ይህ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ዘርፉን ከጥሬ ሀብት አቅራቢነት ወደ ጠንካራ የኢኮኖሚ ሞተርነት እያሸጋገረው ይገኛል። በተለይም በውጭ ምንዛሪ ግኝት ረገድ እየታየ ያለው ታሪካዊ እመርታ የዚሁ ሪፎርም ትሩፋት ነው።

የ2018 በጀት ዓመት ብቻ ኩባንያዎች እና ባህላዊ የወርቅ አምራቾች ከ44 ቶን በላይ የወርቅ ምርት በማምረት ወደ ገበያ በማቅረብ 5.7 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ ተገኝቷል።

ይህ ስኬት መንግሥት የወሰደው የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ዝውውርን በመግታት እና ባህላዊ አምራቾችን ወደ ህጋዊ የባንክ ሥርዓት በማስገባት ያመጣው ተጨባጭ ውጤት ነው።

ይህ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ግኝት የብሔራዊ ባንክን ክምችት ከማሳደግ ባለፈ፣ የጥቁር ገበያን ጫና በማቃለል እና የኢትዮጵያን የብድር አስተማማኝነት በማሻሻል አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ደግፏል።

በተጨማሪም ሌሎች አምራች ዘርፎች የካፒታል ዕቃዎችን ከውጭ ለማስገባት የሚፈልጉትን የፋይናንስ አቅም በመፍጠር ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ነው።

ከውጭ ምንዛሪ ግኝት በተጓዳኝ፣ ዘርፉ በተኪ ምርቶች አቅርቦት እና በእሴት ጭመራ እያስመዘገበ ያለው ለውጥ ሌላው የሪፎርሙ ትልቅ ስኬት ነው።

ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቷን በጥሬው ወደ ውጭ ከሚላክበት አሠራር በማላቀቅ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎችን በግብዓት ለማስተሳሰር ሰፊ እንቅስቃሴ ጀምራለች።

ለዚህም የወርቅ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች፣ የሴራሚክ እና የሲሚንቶ ፋብሪካዎች፣ የተፈጥሮ ጋዝ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ እና የማዳበሪያ ፋብሪካ የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጦላቸው ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛል።

እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የማዕድን ሀብትን እሴት ወደተጨመረበት ምርት በመቀየር፣ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት፣ ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እና የኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማጠናከር የላቀ ፋይዳ አላቸው።

06/09/2026

‎ጳጉሜ 1 የእመርታ ቀን

‎በመደመር መንግሥት በሀገራችንም ሆነ በክልላችን ያሉንን ጸጋዎች ወደልማት በመቀየር በከተማም እና በገጠር ትልልቅ ስኬቶችን ማስመዝገብ ተችሏል።

‎ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን

‎"ጓንዷ" - ለጉሙዝ ብሔረሰብ አዲሱን ዓመት በብሩህ ተስፋ የሚቀበልበት ትልቅ እሴቱ ነው፦ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ‎**********‎‎(አሶሳ፣ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም)...
06/09/2026

‎"ጓንዷ" - ለጉሙዝ ብሔረሰብ አዲሱን ዓመት በብሩህ ተስፋ የሚቀበልበት ትልቅ እሴቱ ነው፦ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ
‎**********

‎(አሶሳ፣ ጳጉሜ 1/2018 ዓ.ም) "ጓንዷ" - ለጉሙዝ ብሔረሰብ አዲሱን ዓመት በብሩህ ተስፋ የሚቀበልበት ትልቅ እሴቱ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ተናገሩ።

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዘንድሮው የጓንዷ በዓል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት የጽዳት፣ የችግኝ ተከላ እና እንክብካቤ መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

‎በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ ጓንዷ ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት መሸጋገሪያ በመሆኑ በብሔረሰቡ ዘንድ በተስፋ፣ በእርቅ፣ በአብሮነት የሚከር በዓል ነው ብለዋል።

‎ጓንዷ የምስጋና መግለጫ በዓል መሆኑን ጠቁመው፣ የጉሙዝ ብሔረሰብ አብሮ በመብላት እና በመጠጣት በፍቅር የሚያከበረው በዓል መሆኑን ተናግረዋል።

‎"ጓንዷ" - ለጉሙዝ ብሔረሰብ የተጠናቀቀውን ዓመት በምስጋና እና በይቅርታ በማለፍ አዲሱን ዓመት በብሩህ ተስፋ የሚቀበልበት ትልቅ እሴቱ መሆኑን አቶ ጌታሁን ገልጸዋል።

‎የዘንድሮው የጓንዷ በዓል "ጓንዷ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ዕድገት" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የልማት፣ የበጎ ፈቃድ ሥራዎች እና ባሕላዊ ሁነቶች እየተከበረ እንደሚገኝ የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ዛሬ በጸዳት ዘመቻ፣ ችግኝ በመትከል እና በመንከባከብም እየተከበረ ነው ብለዋል።

‎የጓንዷ በዓል አከባበር ሁነቶች እስከ ጷጉሜ 4/2018 ዓ.ም እንደሚቀጥሉ ገልጸው፣ ጳጉሜ 4 በተለያዩ ሁነቶች የበዓሉ የማጠቃለያ ዝግጅት እንደሚካሄድ አንስተዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡-የእመርታ ቀን አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነ...
06/09/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፡-

የእመርታ ቀን

አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል። በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!

የስኬትና የተስፋ ብስራት ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል  ***********የዓባይን ወንዝ ታላቅነት፣ የጉባ ተራሮች ብስራት፣ የክልሉ ሰፊና ለም መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብቶች እምቅ ጸጋ የክልላችን ልዩ...
06/09/2026

የስኬትና የተስፋ ብስራት ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
***********

የዓባይን ወንዝ ታላቅነት፣ የጉባ ተራሮች ብስራት፣ የክልሉ ሰፊና ለም መሬት፣ የተፈጥሮ ሀብቶች እምቅ ጸጋ የክልላችን ልዩ ተፈጥሮ ነው።

ይህች ምድር ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መገኛነት ባሻገር፣ የታታሪ ህዝቦች የለውጥ ተስፋ መኖሪያም ናት።

ከዓመታት ያልተቋረጡ የብርቱ እጆች ጥረት በኋላ የዚሁ ለውጥ ፍሬዎች በክልላችን መጎምራትና ማበብ ጀምረዋል።

ባለፈው የ2018 በጀት ዓመት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን በስኬት በማጠናቀቅ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን አስታውቀዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በ2018 ዓ.ም በተከናወኑ ተግባራትና በ2019 ዓ.ም የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ክልሉ በከተማና በገጠር ልማት፣ በአገልግሎት አሰጣጥና በኢንቨስትመንት መስኮች አዳዲስ ስኬቶችን ማብሰሩን ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ ከተመዘገቡት ታሪካዊ፣ አገራዊና ክልላዊ ድሎች መካከል የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ድልና የብሔራዊ አንድነት ማሳያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በስኬት ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ የዓመቱ መጀመሪያ ታላቅ የብስራት ዜና ነበርም ብለዋል።

ይህን ተከትሎም በጉባ ብስራቶች ኢትዮጵያ ለማዳበሪያ ግዢ የምታወጣውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የውጭ ምንዛሪ የሚታደገውና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አይነተኛ ሚና የሚጫወተው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ለአርሶ አደሩ ትልቅ ተስፋ ሆኗል ሲሉም ጠቁመዋል።

ሰው ተኮር በሆኑ ተግባራት ከተሞችን ዘመናዊ፣ ፅዱና ለነዋሪዎች ምቹ የማድረግ ኢንሼቲቭም በስኬት ተከናውኗል።

ይህ የከተሞች ኮሪደር ልማት አሁን ላይ ወደ ገጠር ማዕከላት በመስፋፋት የአርሶና አርብቶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ እያዘመነ እንደሚገኝም ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን አብራርተዋል።

የሕዝብ አገልግሎትን ለማዘመንና የተገልጋዮችን እንግልት ለማስቀረት አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል ያሰባሰበው የሞሶብ የአንድ ማዕከላት ተገንብተው ሥራ መጀመሩ ሌላኛው ተጠቃሽ ውጤት መሆኑም ተገልጿል።

በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች 1መቶ 60 አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን መፍጠር ተችሏል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ እሴት የሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎችን በክልሉ ለማስፍፍት እየተሰራ ስለመሆኑም በአጽንኦት ገልጸዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሰፊ የተፈጥሮ ሀብት፣ እጅግ ለም መሬትና ከፍተኛ የኢንቨስትመንት አማራጮች ያሉት በመሆኑ ለሀገር ውስጥና ለውጭ አልሚ ባለሀብቶች የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ አሻድሊ አረጋግጠዋል።

በ2019 አዲስ በጀት ዓመት የተጀመሩ የልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅና አዳዲስ አቅጣጫዎችን በመቀየስ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራም አስታውቀዋል ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ (BGM)

የፕሬስ መግለጫእመርታ ለዘላቂ ከፍታ!እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል...
06/09/2026

የፕሬስ መግለጫ

እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!

እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡

የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡

ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡

ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡

እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡

እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!

ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ

‎በክልሉ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማስፋት የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ‎**********‎‎(አሶሳ፣ ነሐሴ 30/2...
05/09/2026

‎በክልሉ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማስፋት የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ
‎**********

‎(አሶሳ፣ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን በማስፋት የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ እየተሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።

‎የቤጉ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ምስረታ አንደኛ ዓመትን አስመልክቶ የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የተቋሙ ሰራተኞች የእውቅናና የምስጋና መርሃ-ግብር ተካሂዷል።

‎በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደገለጹት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማስጀመር መቻሉ የተበታተነ አገልግሎትን በአንድ ለመስጠት አስችሏል ብለዋል።

‎በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ በተያዘው ግብ እስካሁን በአራት ማዕከላት ዜጎች የዲጂታል አገልግሎት እያገኙ እንደሚገኝ አቶ አሻድሊ ተናግረዋል።

‎የመደመር መንግስት ብልፅግናን በተጨባጭ ለማረጋገጥ የዜጎችን አገልግሎት ማዘመን ተቀዳሚ አጀንዳው አድርጎ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

‎የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በተዘረጋው የአሰራር ስርዓት ከወረቀት ንኪኪ ነፃ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎በዚህ አሰራር የመንግስት አገልግሎት ፍትሃዊ፣ አካታችና ብዝሃነትን ያማከለ በማድረግ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ስርዓት መዘርጋቱንም አቶ ጌታሁን ገልጸዋል።

‎የቤጉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዋና ዳደይሬክተር ኢንጅነር ሰመረ ጅራታ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ በ11 ተቋማት 52 የተለያዩ የዲጂታል አገልግሎቶችን እየሰጠ መሆኑን ተናግግረዋል።

‎ማዕከሉ ባለፈው አንድ ዓመት ለ45 ሺህ 239 ዜጎች አገልግሎት ሰጥቷል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ የዜጎች የእርካታ ደረጃ 99.9 መድረሱን አስታውቀዋል።

‎በመርሃ ግብሩ ላይ ለማዕከሉ ውጤታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማትና የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የማዕከሉ ሰራተኞች የእውቅናና የምስጋና ሰርቲፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

ነገን ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት መገለጫው ሆኗል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት*************************የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚሻገር አገራዊ ወረት...
05/09/2026

ነገን ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት መገለጫው ሆኗል - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
*************************

የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚሻገር አገራዊ ወረት እያኖረ፤ በተጨባጭ ውጤቶችም እየተገለጸ ቀጥሏል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት ከባንዳ እስከ ባዳ በቅንጅት የተወረወሩበትን እያንዳንዷን ጠጠር በጥበብና በጽናት እየለቀመ የአገር ግንባታ ጡብ አድርጓቸዋል፤ ከጸኑ ፈተናዎች የሰሉ ዕድሎች ተፈልቅቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ “ኢትዮጵያዊ ጽናት እና አርቆ አስተዋይነት የታየበት” ሲሉ ያረጋገጡት እና መንግሥት ይፋ ያደረጋቸው የጉባ ብስራቶች የሀገራችን እምቅ አቅም በተግባር የሚገለጥባቸው ግዙፍ ማሳያዎች ናቸው። ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚፈጀው ይህ ማዕቀፍ የኢትዮጵያን የነገ ዕጣ ፈንታ በሰፊው የሚቀይር ታሪካዊ የጋራ ስኬት ነው።

ለመደመር መንግሥት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የብልጽግናው ዋና መለኪያ ነው። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ መጀመሩ የአርሶ አደራችንን ምርታማነት በብዙ እጥፍ ያሳድጋል። እንደ ሀገርም በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላርን እናተርፍበታለን።

በአፍሪካ ግዙፉ የሆነው አዲሱ የቢሾፍቱ አየር ማረፊያ ግንባታም እውን እየሆነ ነው። ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የአህጉሪቱ ዋንኛ የሎጂስቲክስ፣ የንግድ እና የዲፕሎማሲ መገናኛ በማድረግ የጂኦ-ኢኮኖሚ አቅማችንን ወደ ታላቅ ከፍታ ያሸጋግረዋል። ብዙዎች በሀገራቸው እውን እንዲሆን የሚመኙትን ይህን ታላቅ ፕሮጀክት ኢትዮጵያውያን በጽናት ጀምረነዋል፤ እንፈጽመዋለን።

የመደመር መንግሥት የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የነገው ትውልድ ዕድል የሚቀየር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን በአጽኖት ተልሟል። የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት ያለ ኢነርጂ ሉዓላዊነት የሚታሰብ አይደለም። ለዚህም ነው መንግሥት የኢነርጂ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የኢኮኖሚ ነጻነታችን ማዕዘን ድንጋይ ነው በሚል ስትራቴጂያዊ ትኩረት የሰጠው።

ከታላቁ የህዳሴ ግድባችን ቀጥሎ የኢትዮጵያ ማንሰራራት ምልክት የሆነው የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካችን ተመርቋል፤ ሁለተኛውም እየተገነባ ነው። የነዚህና ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ እና ሥራ መጀመር ከውጭ የሚገባውን የኢነርጂ ፍላጎት በማሟላት ጥገኝነት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል፤ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ማበብም ጽኑ መሠረት ይጥላል።

የልማት እውነተኛ ልክ የዜጎች ክብርና ማኅበራዊ ፍትህ መረጋገጥ ነው። መንግሥት ለዚህ አብላጫ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል። በመላው ሀገሪቱ የሚከናወነው የ1.5 ሚሊዮን ቤቶች ግንባታ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጀምሯል። ፕሮጀክቱ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሚሊዮኖችን የቤት ባለቤት ያደርጋል። የከተሞችን ገጽታ በመቀየር ማኅበራዊ ፍትህን ያረጋግጣል።

መደመር ማለት አብሮ ማደግ እና ሀብትን መጋራት ማለት ነው። እነዚህ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ለሚሊዮን ወጣቶች ቀጥተኛ እና ቀጥተኛ ያልሆኑ የሥራ ዕድሎችን ይፈጥራሉ። በዚህ ረገድ ገና ከጅምሩ ውጤቶች መመዝገብ ጀምረዋል።

የመደመር መንግሥት ለትውልድ የሚያሻግረው ዕዳን ሳይሆን ምንዳን ነው። አዲሱን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፤ ነገን ዛሬ ተልሞ ለትውልድ መቅረጽ የመደመር መንግሥት ልዩ መገለጫ ሆኗል። ወገባችንን አስረን፣ መቀነታችንን አጥብቀን በላባችን ወዝ የምናኖራቸው ወረቶች ለነገው ትውልድ የሚቀሩ የብልጽግና ውርስ ይሆናሉ። በላባችን ጥረት ኢትዮጵያን በጸና መሠረት ላይ እናቆማለን።

05/09/2026

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በቡልዲግሉ ወረዳ የአቅመ ደካማ ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ፣ የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ እና የማዕድ ማጋራት መርኃ ግብር አካሂደዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሚዲያ

Address

Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ:

Shortcuts

Share