Asosa Town Administration Revenues Department

Asosa Town Administration Revenues Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Asosa Town Administration Revenues Department, Government Organization, Asosa.

09/08/2026

ማስታወቂያ ለአሶሳ ከተማ ደረጃ ''ሀ'' ግብር ከፋዮች (ለተጨማሪ እሴት ታክስ) ተመዝጋቢዎች በሙሉ:-
******
ነባሩ ደረሰኝ እንደ ክልላችን ከሰኔ 30/2018 ዓ.ም ጀምሮ መጠቀም እንደማይቻል በማስታወቂያ መግለፃችን ይታወቃል። ስለዚህም QR code የሌለው ደረሰኝ እና ካሽ እሪጅስተር ማሽን መጠቀም እንደለበችሁ በጥብቅ እያሳሰብን ለተከታታይ 3 ቀን ማለትም ከቀን 04/11/2018 ---06/11/2018 ዓ.ም ድረስ የካሽ እሪጅስተር ማሽን በመግዛት እንድትጠቀሙ ስንል እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ :-በተባለው ቀን መጥተው የሸያጭ ማሽን ግዢ የማይፈጽም ግብር ከፋይ ህጋዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን በድጋሜ እናሳውቃለን ።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

የአሶሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ በ2019 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን አስታወቀ። ጽ/ቤቱ በ2018 የግብር ዘመን ላቅ ያለ አፈጻጸም ላስመዘ...
28/07/2026

የአሶሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ በ2019 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማሰብሰብ አቅዶ ወደ ተግባር መግባቱን አስታወቀ። ጽ/ቤቱ በ2018 የግብር ዘመን ላቅ ያለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ባለሙያዎች እና ታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና መድረክ አካሂዷል።

በእውቅና መድረኩ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አብዱልከሪም አብዱራሂም እንዳሉት የሀገር ልማትና እድገት የሚረጋገጠው በሚሰበሰብው ገቢ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ በተሰማራበት የሥራ ዘርፍ ግብርን በታማኝነት በመክፈል ሀገራዊ ግዴታውን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ለአሶሳ ከተማ ማህበረሰብ የተሻሉ የመንገድ፣ የመብራት፣ የመዝናኛና የገበያ ማዕከላት እንዲሁም ሌሎች የመሰረተ ልማት አቅርቦቶችን ለማሟላት በከተማዋ ያሉትን የገቢ አማራጮች አሙጦ በመጠቀም በቀጣይ ከዚህ የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዋር አሲር በበኩላቸው በከተማዋ በ2018 በጀት ዓመት ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ የተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ መቻሉን ገልፀዋል።

የተገኘውን ስኬት መነሻ በማድረግም በ2019 የግብር ዘመን 2ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን አብራርተዋል።

አስተያየታቸውን የሰጡን የከተማዋ ግብር ከፋዮች እንዳሉት ደግሞ በከተማዋ የመሰረተ ልማት ፍላጎቶች ተሟልተው ለማህበረሰቡ አግልግሎት የሚሰጡት በምንከፍለው ግብር በመሆኑ ያኮራናል ብለዋል።

የተበረከተላቸው የእውቅና ምስክር ወረቀትም በቀጣይ ግብራቸውን በታማኝነትና በወቅቱ እንዲከፍሉ የበለጠ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ገቢዎች ፅ/ቤት በቀን 16/11/18ዓ.ም የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ለእቅዳቸው መሳካትና ለመጣው የገቢ መሻሻል ላይ ለተደረገላቸውን ድጋፍና...
23/07/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ገቢዎች ፅ/ቤት በቀን 16/11/18ዓ.ም የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ለእቅዳቸው መሳካትና ለመጣው የገቢ መሻሻል ላይ ለተደረገላቸውን ድጋፍና ክትትል በማመስገን ለአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ሃላፊ አቶ አንዋር አስር ለተሰጣቸው እውቅናና ሽልማት ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

በ2018 በጀት ዓመት ከ374 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የአሶሳ ከተማ አስተዳድር ወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የተመገበውን ስኬታማ የገቢ አሰባሰብን ...
23/07/2026

በ2018 በጀት ዓመት ከ374 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የአሶሳ ከተማ አስተዳድር ወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የተመገበውን ስኬታማ የገቢ አሰባሰብን አስመልክቶ የምስጋናና እዉቅና መርሀ-ግብር አካሂዷል።

በምስጋናና እዉቅና መርሀ-ግብሩ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ዋና አስተዳዳሪ አቶ በድረዲን አህመድ እንዳሉት ግብር የአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ምሶሶ መሠረት በመሆኑ የገቢ አቅምን ማሳደግና ገቢን ለልማት ማዋል አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል ።

በበጀት ዓመቱ ለተገኘው የተሻለ ገቢ የጽ/ቤቱ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የግብር ከፋይ ማህበረሰብና የባለድርሻ አካላት በሰሩት ቅንጅታዊ ስራ ውጤት ነው ብለዋል፡፡

የግብር ከፋይ ማህበረሰብን ግንዛቤ በማሳደግ የግብር ክፍያ ባህልን ማጠናከር ይገባልም ብለዋል፡፡

አዳዲስ የገቢ አማራጮችን በመለዬትና ዘመናዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን በመከተል ከአሁኑ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ ሥራ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡

ህገ-ወጥ ንግድና ኮንትሮባንድን ለመከላከል ባለድርሻ አካላት በቅንጅት እንዲሰሩም ጥሪ አቅርበዋል።

የወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ መሀመድ በበኩላቸው ወረዳው በ2018 በጀት ዓመት 228 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ገቢ ግብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ374 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቀዋል፡፡

በግብር ከፋዮች ላይ የተሰራው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ፣ የገቢ ምንጮችን በአግባቡ መለየትና የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ማሻሻል ለተገኘው ውጤት አስተዋጽኦ ማድረጉ የጽ/ቤቱ ሀላፊ ገልፀዋል።

በቀጣይም የገቢ አሰባሰብ ሥራውን በማጠናከር የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰሩም አሳውቀዋል።

ለወረዳው ለገቢ ግብር የተሻለ አበርክቶ ለነበራቸው ሠራተኞች፣ ባለድርሻ አካላትና የወረዳው አመራሮች ምስጋናና እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በቋሚ ኮሚቴ   አስገመገመ።ሃምሌ ቀን 15/11/18 ዓ.ም************ በበጀት ዓመቱ 1,489,...
22/07/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በቋሚ ኮሚቴ አስገመገመ።

ሃምሌ ቀን 15/11/18 ዓ.ም
************

በበጀት ዓመቱ 1,489,030,886 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1,495,578,836.45 ብር በመሰብሰብ የተቻለ ሲሆን እቅዱን ከ100% በላይ ማሳካት መቻሉን የአሶሳ ከተማ ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ አንዋር አሲር የዕቅድ አፈፃፀሙን ሪፖርት ለቋሚ ኮሚቴው ባቀረቡበት ወቅት አሳውቀዋል።

በግምገማው ላይ የነበሩ ቋሚ ኮሚቴዎች እቅዱን ማሳካት መቻሉን ያመሰገኑ ሲሆን ለቀጣይም የገቢ አማራጮችን በመጠቀም የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ተስፋ ሰጭ ስለሆነ የተሻለ እቅድ የተሻለ አፈፃፀም እንጠብቃለን ሲሉ አስተያየታቸውን በመስጠት አጠናቀዋል።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የምስጋናና የእውቅና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበረከተለት​አሶሳ፦ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ገቢዎች መም...
18/07/2026

የከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች መምሪያ ከአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የምስጋናና የእውቅና ሰርተፊኬት ሽልማት ተበረከተለት

​አሶሳ፦ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ገቢዎች መምሪያ)

​የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽህፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለመሰብሰብ ካቀደው 353 ሚሊዮን ብር ውስጥ 362 ሚሊዮን ብር (የዕቅዱን 102%) በመሰብሰብ ያስመዘገበውን የላቀ አፈጻጸም ምክንያት በማድረግ የእውቅና እና የምስጋና መርሃ-ግብር አካሂዷል።

​ጽሕፈት ቤቱ ለተመዘገበው የላቀ የገቢ አፈጻጸም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት፣ ለታማኝ ግብር ከፋዮች፣ ለመንግሥትና ለግል ተቋማት እንዲሁም ለጽሕፈት ቤቱ ሠራተኞች የዕውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጅቷል።

​በዕለቱ በተካሄደው የእውቅና እና የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ለወረዳው ገቢዎች ጽሕፈት ቤት ላደረገው ሁለንተናዊ ድጋፍና ቀጣይነት ያለው ክትትል የተዘጋጀውን የምስጋና ሰርተፊኬትና ዋንጫ የተበረከተ ሲሆን ሽልማቱንም የመምሪያችን ሃላፊ አቶ አንዋር አስር የተቀበሉ ሲሆን ለተደረገላቸው እውቅናና ሽልማት ላቅ ያለ ምስጋናቸውንም አስተላልፈዋል።

''የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ''

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 95 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ። መምሪያው የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል። የአ...
16/07/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ በበጀት ዓመቱ ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 95 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ። መምሪያው የበጀት ዓመቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዋር አስር እንደገለጹት መምሪያው በበጀት ዓመቱ 1 ቢሊዮን 4 መቶ 89 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ከ1 ቢሊዮን 4 መቶ 95 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ ተችሏል ብለዋል።

የተመዘገበው ገቢ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ116 በመቶ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።

ለተመዘገበው ውጤት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የመምሪያው ባለሙያዎችና ሠራተኞች፣ ታማኝ የከተማዋ ነጋዴዎች፣ የጸጥታ አካላት እና የደንብ አስከባሪዎች ኃላፊው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በተጨማሪም የነበረውን የባለሙያ እጥረት በመቅረፍ እና ብቁ ባለሙያዎችን በማፍራት የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ ከፍተኛ ሥራ መሠራቱን አብራርተዋል።

በቀረበው የግምገማ ሪፖርት በበጀት ዓመቱ የገቢ ግብር አሰባሰብ ወቅት ለተነሱ ቅሬታዎች አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠት አኳያ የተሻለ አፈጻጸም ታይቷልም ብለዋል።

በሌላ በኩል በበጀት ዓመቱ 152 የኦዲት ግኝቶች መደረጋቸውን የገለፀ ሲሆን በቀጣይ በግብር አከፋፈል ወቅት የሚስተዋሉ የደረሰኝ አቆራረጥ ችግሮችን ለመፍታት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተመላክቷል።

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ362 ሚሊየን ብር  በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ለዕቅዱ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የእው...
16/07/2026

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ከ362 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡

ለዕቅዱ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሀ-ግብር ተካሂዷል፡፡

በዕውቅናና ምስጋና መርሀግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳ አንድ አስተዳዳሪ ወ/ሮ አሙና አብዱልዋሂድ እንዳሉት የገቢ ስራ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ የጀርባ አጥንት መሆኑን በጥልቀት ተረድተው ስኬታማ ስራ ለሰሩ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

አፈጻጸሙ በ2019 በጀት ዓመት ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ መነሳሳትን የሚፈጥር በመሆኑ ቅንጅታዊ ስራን ማጠናከር እንደሚገባም ነው ዋና አስተዳዳሪዋ ያስገነዘቡት፡፡

በ2018 በጀት ዓመት የወረዳው አንድ ገቢዎች ጽሕፈት ቤት 353 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ቢሆንም፣ በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ 362 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን የገለጹት ደግሞ የጽ/ቤቱ ሀላፊ አቶ አብዱረቡ አብዱረሂም ናቸው።

በቀጣይም የገቢ አማራጮችን በማሳደግ የተሸለ ገቢ ለመሰብሰብ ጽ/ቤቱ በልዩ ትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡

በመድረኩ የተሳተፉ የተቋሙ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው ገቢ ለሀገር ዕድገት መሰረት መሆኑን ተገንዝበውና ቅንጅታዊ ስራዎችን አጠናከረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

በምስጋናና ዕውቅና መርሀ-ግብሩም የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ አንድ ዋና አስተዳዳሪ ወ/ሮ አሙና አብደልዋሂድ፣ የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ አብዱረቡ አብዱረሂም ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩና የወረዳው ዓመራሮችም የተገኙ ሲሆን ለዘርፉ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረኩተ አመራሮች፣ ባለሙያዎች እንደሚሁም ባለድርሻ አካላት የዕውቅናና ምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቷል፡፡
የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ገቢዎች ፅ/ቤት

የወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት በጀት ዓመቱ አጠቃላይ 374,551,745 (ሦስት መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ ሰባት መቶ አርባ አምስት ብር)  ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ...
13/07/2026

የወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት በጀት ዓመቱ አጠቃላይ 374,551,745 (ሦስት መቶ ሰባ አራት ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ ሰባት መቶ አርባ አምስት ብር) ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ።
___________
(ሰኞ ሐምሌ 6/2018 ዓ.ም አሶሳ)
በአሶሳ ከተማ አስተዳደር የወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት ከማናጅመንቱ ጋር በመሆን የ2018 ዓ.ም በጀት አመት የአራተኛ ሩብ አመት እና የ12 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ አካሄደ።

የወረዳዉ ገቢዎች ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙስጠፋ ማህሙድ እንዳሉት በበጀት አመቱ የተመዘገበዉ ዉጤት የሁላችንም የጋራ ጥረትና ትብብር ፍሬ በመሆኑ ለማናጅመንቱ እና ለአጠቃላይ የእስታፍ ሰራተኞች ምስጋና አቀርቧል።

የወረዳ ሁለት ገቢዎች ጽ/ቤት
አሶሳ፣

የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በማኔጅመንት አባላት በጥልቀ...
10/07/2026

የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄደ።

የወረዳ አንድ ገቢዎች ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በማኔጅመንት አባላት በጥልቀት አካሂዷል።

በግምገማው ወቅት የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አብዱራቡ አብዱራሂም እንደገለጹት፣ ጽ/ቤቱ ለ2018 ዓ.ም 353 ሚሊዮን ብር የገቢ ዕቅድ በማቀድ በዓመቱ ውስጥ 362 ሚሊዮን ብር በመሰብሰብ 102 % በመቶ አፈጻጸም በማስመዝገብ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል።

በተጨማሪም በዓመቱ ውስጥ ከተለዩና ከተያዙ የገቢ ምንጮች በተገኘው ተጨማሪ አፈጻጸም ከዕቅዱ በላይ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ በጽ/ቤቱ ታሪክ ውስጥ እንደ ልዩ ስኬት ተመዝግቧል።

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አብዱራቡ አብዱራሂም ለዚህ ከፍተኛ ስኬት አስተዋፅኦ ያበረከቱ የመንግሥት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ አካላት፣ ግብር ከፋዮች፣ የተለያዩ ግለሰቦች እና በትጋትና በታማኝነት የሠሩ የጽ/ቤቱ ባለሙያዎችን ከልብ አመስግነዋል።

በመጨረሻም የተመዘገበው ስኬት የጋራ ጥረት፣ የታማኝነት ሥራ እና የቅን ትብብር ውጤት ነው። በቀጣይም ይህንን ስኬት በማስቀጠል የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጽ/ቤቱ በቁርጠኝነት ይሠራል በማለት መልዕክታቸውን አቶ አብዱራቡ አስተላልፈዋል።

Address

Asosa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Asosa Town Administration Revenues Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share