Ataye City Government Communication office

Ataye City Government Communication office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ataye City Government Communication office, Government Organization, Ataya, Shewa, Ataya.

በአጣዬ ከተማ የመንግስት ሰራተኛ አባላት "ውጫዊ የወረራ ስጋትንና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ "ላይ ውይይት ተካሄደ።አጣዬ፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ....
20/08/2026

በአጣዬ ከተማ የመንግስት ሰራተኛ አባላት "ውጫዊ የወረራ ስጋትንና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን ማረጋገጥ "ላይ ውይይት ተካሄደ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) —

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከመንግስት ሰራተኞች የብልፅግና ፓርቲ አባላት ጋር “ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ውይይት ተካሄደ።

የውይይቱን መድረክ በንግግር የከፈቱት የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ፣ የዕለቱ የውይይት መድረክ በሰነዱ ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ እንዲመካከሩና ሀሳብ እንዲለዋወጡ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

በመቀጠልም የ“ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” የውይይት ሰነድ የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ዘቡራ ከድር ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።

በሰነዱ ላይም ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት ሰጥተዋል።

ውይይቱ በተለይም የሰላምን መሠረት ማጠናከር፣ የውጫዊ ወረራ ስጋቶችንና የውስጣዊ ፅንፈኝነት አደጋዎችን በጋራ መመከት፣ ዘላቂ ሰላምን ማረጋገጥና የከተማዋን ልማት ማፋጠን በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኮረ ነበር።

በመድረኩ ከቀረበው የውይይት ሰነድ መነሻነት ተሳታፊዎች የሰላምን ሁኔታ ለማስጠበቅ፣ የከተማዋን ልማት ለማስቀጠልና ህብረተሰቡን ለማጠናከር የሚያስፈልጉ የጋራ እርምጃዎችን በተመለከተ ሀሳቦችን አንስተዋል።

በመጨረሻም የተሳታፊዎችን ጥያቄዎችና አስተያየቶች በተመለከተ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ እና የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ከድር እንድሪስ ናቸው።

በማጠቃለያውም የመንግስት ሰራተኞች የሰላምና የልማት ሂደቱን በማጠናከር፣ ህግንና ሰላምን በመጠበቅ እና በተሰጣቸው ሙያዊ ኃላፊነት በብቃት በመወጣት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲወጡ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

ህውሃት በአማራ ክልል ላይ የጦርነት እሳቤ መቀልበስ፣ የኢኮኖሚ ወድቀት እንዳይከሰት መቀልበስ ፣ ህውሃት በተለያዩ ተቋማት ውድመት እንዳይከሰት መመከት እና የህብረተሰብ መሰተጋብር እንዳይቋረጥ መስራት፣ ከውጪ ጠላት ጋር በመሆን በክልሉ ጥቃት እንዳይፈፁሙ መመከት በሚሉት ላይ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በመጨረሻም ዘላቂ ሰላም ለልማት ወሳኝ መሠረት መሆኑን በመገንዘብ፣ አመራሩ፣ መንግስት ሰራተኞችና ህብረተሰቡ በጋራ በመስራት ለከተማዋ ሰላም፣ ደህንነትና ልማት የሚጠበቅባቸውን ሚና ለመወጣት በመግባባት ውይይቱ ተጠናቋል።

"ፅንፈኝነት በማክሸፍ ወረራን በመመከት ሰላማችንና ልማታችንን እናረጋግጣለን!"

የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ በተመረጡ ትም/ቤቶች ፓይለት ምዝገባው እየተከናወነ ይገኛል።አጣዬ፦ ነሀሴ 14/2018 ዓ.ም. (አጣዬ  ኮሙኒኬሽን)በኤፍራታና ግድም ወረዳ  በ20...
20/08/2026

የ2019 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ በተመረጡ ትም/ቤቶች ፓይለት ምዝገባው እየተከናወነ ይገኛል።

አጣዬ፦ ነሀሴ 14/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)

በኤፍራታና ግድም ወረዳ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የሚማሩ ተማሪዎች ከቅድመ 1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች ፓይለት ምዝገባ እየተከናወነ ይገኛል።

በምዝገባ የትምህርት ተቋማትም የኤፍራታናግድም ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሰዓዳ ይማም፣ የወረዳው ትም/ት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ታደሠ ጥላዬ ፣የጤና ፅ /ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ውብርስት አስፋው፣የመንግስት ኮሙንኬሽን ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አለም የሺዳኛ ፣የትም/ት ፅ ቤት ም /ሀላፊ ዘየደ ገ/የስ ተገኝተዋል።

የወረዳው ትም/ት ፅቤት ሀላፊ አቶ ታደሠ ጥላዬ በዛሬው ዕለት በ2 አንደኛ ደረጃና በአንድሁለተኛ ደረጃ ከፍተኛ ትምህርት ቤት የሙከራ ምዝገባው እየተከናወነ እንደሚገኝ በትምህርት ዘመኑም 51241 ተማሪዎችን በመመዝገብ የመማር ማስተማር ስራው ን ለማካሄድ በዕቅድ መያዙን ገልፀዋል።የምዝገባ ሁኔታውም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ሀላፊው ገልፀዋል።

ለምዝገባ ከተመረጠው የላይኛው አጣዬ 1ኛ ደረጃ ትም/ቤትም የአካባቢው ተወላጆች ለተቋሙ የአጋዥ መፅሀፍ ድጋፍ አድርገዋል።

ኤፍራታ ኮሙኒኬሽን

የአጣዬ የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ከደ/ብረሃን ዩኒቨርስቲ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ጋር  በመተባበር በአጣዬ የክረምት በጎ ፈቃድ የቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ።አጣዬ፦ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ....
19/08/2026

የአጣዬ የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ከደ/ብረሃን ዩኒቨርስቲ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ጋር በመተባበር በአጣዬ የክረምት በጎ ፈቃድ የቀዶ ሕክምና ዘመቻ ተጀመረ።

አጣዬ፦ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) —

በአጣዬ ከተማ የሚገኘው የአጣዬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ግዛው ሆስፒታል ጋር በመተባበር የክረምት በጎ ፈቃድ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ዘመቻ ዛሬ ጀምሯል።

በዘመቻው ላይ በዘመቻው ላይ የተገኙት የሀኪሞች የሉካን ቡድን የተገኙት የጠቅላላ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት እና የቡድኑ መሪ ዶ/ር ዮሴፍ ተመስገን ፣ ዶ/ር አሰፋ ፋንታሁን የጠቅላላ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ፣ሲ/ር እመቤትና መልካም የአንስቴዥያ ባለሞያ እንዲሁም ሲ/ር ቅድስት የሻው እና ባለሙያ አቶ አብዱ የነርሲንግ ተገኙተዋል።

የአጣዬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ አቶ መስፍን አስፋው እንደገለጹት፣ በዘመቻው የተለያዩ የቀዶ ሕክምና አገልግሎቶች ይሰጣሉ።

በመቀጠልም የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት የእንቅርትና የአንገት አካባቢ እጢዎች፣ የሐሞት ጠጠር፣ የአንጀትና የፊንጢጣ አካባቢ ችግሮች እንደ ፊስቱላና ኪንታሮት፣ በተለያዩ የሰውነት አካባቢዎች የሚከሰቱ እብጠቶች፣ የጡት ካንሰርና መሰል የጡት ችግሮች፣ የትርፍ አንጀት ችግሮች፣ የድንገተኛ ሕክምና ጉዳዮች፣ በእግር ላይ የሚታዩ የደም ሥር ችግሮች እና የሽንት ቱቦ እጢዎችና መሰል ችግሮች ይገኙበታል።

የሕክምና ቡድኑ ከነሐሴ 13 እስከ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ለተከታታይ 7 ቀናት በአጣዬ የሚቆይ ሲሆን፣ የቀዶ ሕክምና አገልግሎት የሚፈልጉ ወገኖች በሆስፒታሉ በመገኘት ሕክምናውን እንዲያገኙ ጥሪ ቀርቧል።

ስራ አስካጅም በመጨረሻም ዘመቻው በክረምት በጎ ፈቃድ እንቅስቃሴ የሕክምና ባለሙያዎች ዕውቀትና ሙያዊ አቅምን በማጋራት ለማኅበረሰቡ የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማዳረስ የሚያግዝ መሆኑን ገልፀዋል።

በአጣዬ ከተማ የደብረ ታቦር (ቡሄ) ዓመታዊ በዓል በድምቀት ተከበረ።አጣዬ፦ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) — በአጣዬ ከተማ የደብረ ታቦር (ቡሄ) ዓመታዊ በዓል በተለያዩ...
19/08/2026

በአጣዬ ከተማ የደብረ ታቦር (ቡሄ) ዓመታዊ በዓል በድምቀት ተከበረ።

አጣዬ፦ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) —

በአጣዬ ከተማ የደብረ ታቦር (ቡሄ) ዓመታዊ በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊና ባህላዊ መርሃ ግብሮች በድምቀት ተከብሯል።

በዓሉ በአጣዬ ከተማ አስተዳደር እና በኤፍራታና ግድም ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት አዘጋጅነት የተከበረ ሲሆን፣ በዕለቱ የሃይማኖታዊ ትምህርት፣ የሙልሙል ቆረሳ እና የሕፃናት የጅራፍ ተኩስ መርሃ ግብሮች ተካሂደዋል።

በዝግጅቱ ላይ የተጋበዙት የኤፍራታና ግድም ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደሰ ጥላዬ፣ ለበዓሉ ተሳታፊዎች “እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን” በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዕለቱ በተሰጠው ሃይማኖታዊ ትምህርትም፣ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱንና ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ቀን በዓሉ እንደሚከበር ተገልጿል።

“ቡሄ” የሚለው ቃል “ገላጣ” ማለት ሲሆን፣ በሀገራችን የክረምቱ ጭጋግና ደመና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታይበትን ወቅት የሚያመለክት በዓል መሆኑም ተምሯል።

በመጨረሻም የአጣዬ ከተማ አስተዳደር እና የኤፍራታና ግድም ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች አቶ አበባው ገረመው እና ወ/ሮ ትለፍ ወንደሰን የችቦ ማብራት ሥነ-ሥርዓት በማካሄድ የዕለቱን መርሃ ግብር እና የመዝጊያ ንግግር በማድረግ በድምቀት ተጠናቋል።
አጣዬ

በአጣዬ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰበሰበ የምግብ እህልና ሌሎች የቤት ፍጆታዎች ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ተደረገ።አጣዬ፣ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) — በአጣዬ ከተማ አስ...
19/08/2026

በአጣዬ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰበሰበ የምግብ እህልና ሌሎች የቤት ፍጆታዎች ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ተደረገ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) —

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በክረምት በጎ ፈቃድ ተግባር የተሰበሰቡ የምግብ ነክ ድጋፎች ለ44 አቅመ ደካሞች ተረከቡ።

የድጋፍ ርክክቡ በአጣዬ ከተማ አስተዳደር ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት፣ ከዩኒቨርሲቲ በመጡ ተማሪዎች እና በበጎ ፈቃድ ተሳታፊ ግለሰቦች በጋራ ባሰባሰቡት ድጋፍ መሠረት ለሦስቱም ቀበሌዎች አቅመ ደካሞች ተካሂዷል።

በድጋፉ የእንጀራ እህል፣ የምግብ ዘይት፣ ሽሮ፣ በርበሬ እና የልብስ ሳሙና ለአረጋዊያን ፣ አካል ጉዳተኛ እና አቅመ ደካማ ለሆኑ ተሰጥቷል።

በርክክቡ ላይ የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስ፣ የአጣዬ ከተማ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ጌጤነሽ ማሞ እና የብልፅግና ፓርቲ የሴት ክንፍ ኃላፊ ወ/ሪት ብርቄ አራጋው ተገኝተዋል።

ድጋፍ የተደረገላቸው አቅመ ደካሞች ስለተደረገላቸው ድጋፍ አመስግነው ተረክበዋል።

ኃላፊዎቹ እንደገለጹት፣ በክረምት በጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበው ድጋፍ አነስተኛ ቢሆንም በቀጣይ የበጎ ፈቃድ እና የድጋፍ ሥራዎችን በማጠናከር ተጨማሪ አቅመ ደካሞችን ለመደገፍ ሥራው በተጠናከረ መልኩ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” — የበጎነት ተግባር ለተቸገሩ ወገኖች የተስፋ ብርሃን!

19/08/2026
18/08/2026
በአጣዬ ከተማ  የቤሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት እና የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ለማድረግ  እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ ።አጣዬ፣ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)  በአጣዬ ከተ...
18/08/2026

በአጣዬ ከተማ የቤሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት እና የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር የቤሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) አገልግሎት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የቤሔራዊ ዲጅታል ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ መሆኑ የከተማው የፓርቲ ኃላፊ ገልፀዋል።

የቤሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) አገልግሎት አሰጣጥ እና አስፈላጊነት የተናገሩት የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስ የከተማዋን ነዋሪዎች የቤሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ ማድረግ ከዘመናዊ የዲጂታል አሰራር ስርዓት ጋር ህብረተሰቡን ለማስተሳሰር ትኩረት ከተሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ከድር እንድሪስ ህብረተሰቡ የፋይዳ መታወቂያ በማውጣት ከዘመናዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ጋር እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል።

የፋይዳ መታወቂያ አገልግሎት መስጫ ጣቢያው ተገኝተው አገልግሎት ሲሰጡ ያገኛናቸው አቶ እሸቱ ምንዳ በበኩሉ፣ የከተማው ማህበረሰብ በብዛት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጾ፣ የፋይዳ አስፈላጊነቱን ተረድቶ ነዋሪዎቹ በእጃቸው እንዲይዙ አሳስቧል።

የፓርቲው ኃላፊ አቶ ከድር በመጨረሻም ቤሔራዊ ዲጅታል መታወቅያ የፓርቲያችን እንሼትቭ ከሆኑት አንዱ ሲሆን የፋይዳ ተጠቃሚ መሆን የመንግስትን አሰራር ምቹና ቀላል ከማድረግ ባሻገር ህብረተሰቡ የሚያጋጥመውን የተለያዩ አገልግሎት ድካምና እንግልቶችን እንደሚቀንስ ገልጸዋል። በተጨማሪም የዲጂታል መታወቂያ ስርዓቱ የወንጀል መስፋፋትን ለመቀነስ ጠቃሚ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል።

ስለሆነም የአጣዬ ከተማ ነዋሪዎች የፋይዳ መታወቂያን በማውጣት የዲጂታል አገልግሎቶችን ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

በአጣዬ ከተማ  “ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ከአመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ።አጣዬ፣ ነሐሴ 12/2...
18/08/2026

በአጣዬ ከተማ “ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ከአመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 12/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን) —

በአጣዬ ከተማ አስተዳደር “ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን” በሚል መሪ ሀሳብ ለከተማና ለቀበሌ አመራሮች የውይይት መድረክ ተካሄደ።

የውይይቱ ዓላማ የሰላምን መሠረት በማጠናከር፣ ውጫዊ የወረራ ስጋቶችንና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋዎችን በጋራ በመመከት ዘላቂ ሰላምና የከተማዋን ልማት ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ የከተማና የቀበሌ አመራሮች በጉዳዩ ላይ ውይይት ተካሄዷል።

መድረኩን የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ተመስገን ተስፋ እና የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር እንድሪስ መርተዋል።

በመቀጠልም የአጣዬ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ ዘቡራ ከድር የመወያያ ሰነድ አቅርበው ከተሰብሳቢ ሀሳብ እና አስታዬት ተሰጥቶበት በኃላፊዎች ማጠቃልያ ተሰጥቶበታል።

በመጨረሻም በውይይቱም የሰላም ዘላቂነት ለልማት ወሳኝ መሠረት መሆኑን በመገንዘብ፣ አመራሩና ህብረተሰቡ በጋራ በመስራት ለከተማዋ ሰላም፣ ደህንነትና ልማት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ በመግባባት ውይይቱ የተጠናቀቀ እና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል።

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአረጋውያንና ሚስኪኖች ማዕድ አጋራ።አጣዬ፣ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)በአጣዬ ከተማ የሚገኘው አጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍ...
17/08/2026

የአጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአረጋውያንና ሚስኪኖች ማዕድ አጋራ።

አጣዬ፣ ነሐሴ 11/2018 ዓ.ም. (አጣዬ ኮሙኒኬሽን)

በአጣዬ ከተማ የሚገኘው አጣዬ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ “በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ለአጣዬ አረጋውያንና ሚስኪኖች መርጃ ማዕከል ማዕድ አጋርቷል።

በማዕድ ማጋራቱ ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ እንድሪስ ሰይድ፣ ም/ዲኑ አቶ አረጋኸኝ ጌታቸው፣ ወ/ሮ ባንችአምላክ አዳነ እና የተቋሙ ሰራተኞች ተገኝተው ማዕድ አጋርተዋል። ከምሳ ማጋራቱ በተጨማሪ የንፁህና መጠበቅያ 16 ሊትር ላርጎ እና እሽግ ውሃ ድጋፍ ተደርጓል።

በመርጃ ማዕከሉ የሚኖሩ አረጋውያንም ለተደረገላቸው የማዕድ ማጋራትና ድጋፍ የኮሌጁን አመራርና ሰራተኞች አመስግነው፣ መልካም ምኞታቸውን ገልጸው ጸሎት አድርገዋል።
የኮሌጁ ዲን በመጨረሻም የበጎ ፈቃድ ተሳትፎ በማህበረሰቡ ውስጥ የበጎነት ባህልን በማጠናከር የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ ተግባሩ በቀጣይም እንደሚጠናከር አመልክተዋል።

Address

Ataya, Shewa
Ataya
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ataye City Government Communication office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share