Mamush Zerfu

Mamush Zerfu Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mamush Zerfu, Public & Government Service, Addis Ababa, Awassa.

30/04/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mekonnen Zeleke, Desalegn Dagne, Melkamu Muleta Hayela, Shege Ye Egizabher, one Love, Esmael Nerpo, Eyesus Feraj New, Sgmaw Ye Abatu, Amarech Katena, Buzayehu Siyum, Matiyos Mekuriya, Zelalem Sabako, Abinat Almu, Wubalem Kaleb

10/04/2026
05/03/2026

በመራጭነት ለመመዝገብ የሚቀርቡ ማስረጃዎች፡-

ሀ) ማንነትን የሚገልፅ የቀበሌ መታወቂያ ካርድ ወይም ፓስፖርት፣

ለ) የቀበሌ መታወቂያ ካርዱ ወይም ፓስፖርቱ ያልታደሰ ቢሆንም እንኳን ለምዝገባ ሊያገለግል ይችላል፡፡ ነገር ግን የካርዱ ዕድሳት ጊዜ ከአምስት አመት በላይ ያለፈው ከሆነ ሌላ ማረጋገጫ ማቅረብ ይጠበቃል፡፡

ሐ) የቀበሌ መታወቂያ ካርድ ወይም ፓስፖርት ማቅረብ ካልተቻለ የቅርብ ፎቶግራፍ ተደርጎበት የተሰጠ እንደ መንጃ ፈቃድ፣ የመኖሪያ የምስክር ወረቀት፣ ከውትድርና የተገለሉበት ሰነድ፣ የትምህርት ቤት መታወቂያ፣ የሰራተኛነት መታወቂያ የመሳሰሉ የመለያ ማስረጃዎች በመራጭነት ለመመዝገብ የሚያስችሉ ሰነዶች ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡

👉 ነገር ግን ከዚህ በላይ የተጠቀሱት ማስረጃዎች በማይኖሩበት ወቅት፡-

ሀ) ከምርጫ አስፈጻሚዎቹ ሁለቱ መራጩን ለይተው የሚያውቁ ከሆነ በአስፈጻሚዎቹ ምስክርነት ወይም፣

ለ) በገጠር አካባቢ ሲሆን በባሕላዊና በልማዳዊ ዘዴ ተመዝጋቢውን ለመለየት የሚቻልበት ሁኔታ ካለ ባሕሉን የሚያውቁ ሁለት ሰዎች ለምርጫ ጣቢያው ሰብሳቢ በሚሰጡት ምስክርነት ቃለ ጉባኤ ተይዞ እና በቃለ ጉባዔው ላይ የምርጫ ጣቢያው አስፈጻሚዎች ተፈራርመውበት ምዝገባው ይከናወናል፡፡

ሐ) የተመዝጋቢ እድሜ 18 ዓመት ስለመሆኑ የሚቀርብ ማስረጃ ሳይኖርና ወይም ጥርጣሬ ሲኖር በተመዝጋቢ ቤተሰብ አንጋፋ አባል ወይም ዘመድ፣ እነሱ ከሌሉ ስለግለሰቡ የሚያውቁ ሁለት ሰዎች ለምርጫ ጣቢያው ሰብሳቢ በሚሰጡት የምስክርነት ቃል በማረጋገጥ ሂደቱ በቃለ ጉባዔ ተይዞ ሊመዘገብ ይችላል፡፡

መ) የሚሰጠውን ምስክርነት የምርጫ ጣቢያው ሃላፊ ይሰማል፤ በቃለ ጉባዔው ላይ የምርጫ ጣቢያው አስፈጻሚዎች ይፈራረሙበታል፡፡

የምርጫ ጣቢያው በተቋቋመበት ቀበሌ ለረዥም ጊዜ በመደበኛነት መኖራቸው በሰነድ የተረጋገጠ ሦስት ግለሰቦች በሚሰጡት ምስክርነት የሰነድ ማስረጃ አልባውን ተመዝጋቢ ለመለየት ከተቻለ ሂደቱ ቦርዱ በሚያዘጋጀው የቃለ ጉባዔ ላይ የምርጫ ጣቢያው አስፈጻሚዎች ተፈራርመውበት ምዝገባው ሊከናወን ይችላል፡፡

👉 ስለመራጭ ማንነት፣ ነዋሪነት ወይም ሌላ ሁኔታ ማንኛውም ዓይነት ምሥክርነት የሚሰጥ ሰው፡-

ሀ) በመራጭነት የተመዘገበ፣

ለ) እጩ ተወዳዳሪ ወይም የእጩ ተወካይ ያልሆነ መሆን ይኖርበታል፡፡

👉 ከላይ ከተመለከቱት ማረጋገጫዎች በአንዱ ብቻ የመራጩን ማንነትና የነዋሪነት ቆይታ ማረጋገጥ ያልተቻለ እንደሆነ መዝጋቢዎች ከአንድ በላይ መስፈርቶችን በመጠቀም ያረጋግጣሉ፡፡

05/03/2026
ይገባታል
19/01/2026

ይገባታል

19/01/2026

ቴዎድሮስ ተሾመ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ግልጽ ደብዳቤ ላከ፦

📌 " የጂኦ-ፖለቲካ ፍላጎት ማሟያ መሆን የለበትም"

| ታዋቂው የፊልም ባለሙያ ቴዎድሮስ ተሾመ፣ በአባይ ወንዝ እና በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያለውን የኢትዮጵያን ጽኑ አቋም የሚገልጽ ግልጽ ደብዳቤ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሰራጨ። ቴዎድሮስ በደብዳቤው ፕሬዝዳንቱ ስለ አባይ ጉዳይ ያለውን እውነታ እንዲረዱ አሳስቧል።
በደብዳቤው ላይ የተጠቀሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

* ተፈጥሮአዊ መብት፦ አባይ ከኢትዮጵያ ምድር የሚመነጭ የፈጣሪ ስጦታ እንጂ በማንኛውም ስምምነት የተፈጠረ አለመሆኑንና ኢትዮጵያም በዓለም አቀፍ የውሃ ሕግ መሠረት ፍትሐዊ የመጠቀም መብት እንዳላት ገልጿል።

* የቅኝ ግዛት ውሎችን ውድቅ ማድረግ፦ ኢትዮጵያ ያልፈረመችባቸውና ግብፅን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርጉት የ1929 እና የ1959 ውሎች በኢትዮጵያ ላይ ምንም ዓይነት ተፈጻሚነት እንደሌላቸው አብራርቷል።

* የታሪክ ማስታወሻ፦ ግብፅ ኢትዮጵያን ደካማ ለማድረግና የባሕር በር እንድታጣ ስታደርገው የነበረውን የታሪክ ሴራ ያስታወሰው ቴዎድሮስ፣ አሁንም ግድቡ ለዜጎች ብርሃን ለመስጠት እንጂ ውሃን ለመግታት የታለመ አለመሆኑን አስገንዝቧል።

* የመፍትሔ አቅጣጫ፦ የአባይ ጉዳይ የፖለቲካ ፍላጎት ማሟያ መሆን እንደሌለበትና በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ ሊፈታ የሚገባው "የወንድማማቾች ጉዳይ" መሆኑን ለፕሬዝዳንቱ አሳውቋል።

ቴዎድሮስ ተሾመ ደብዳቤውን ሲያጠቃልል፤ ኢትዮጵያ የገዛ ቤቷን ለማብራት ያላትን መብት ለማንም አሳልፋ እንደማትሰጥ በጽኑ አቋም ገልጿል።

​ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

19/01/2026
07/01/2026

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Cheri Dechasa, Melkamu Bashura, Selam Mekuriya, Eyasu Ewunetu, Belaneh Baruda, Dabara Darchu

17/12/2025

Address

Addis Ababa
Awassa

Telephone

+251926318683

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mamush Zerfu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share